Ethiopian Public Service University
الذهاب إلى القناة على Telegram
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Ethiopian Public Service University
تُعد قناة Ethiopian Public Service University (@epsutelegram) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 12 732 مشتركاً، محتلاً المرتبة 15 748 في فئة التعليم والمرتبة 2 643 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 12 732 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 12 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 112، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 6، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 34.77%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.09% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 428 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 049 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 27.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 13 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.
12 732
المشتركون
+624 ساعات
+237 أيام
+11230 أيام
أرشيف المشاركات
በኢፐሰዩ የማኔጅመንት ድጋፍ ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት የ2ኛ መንፈቅ ዓመት እቅድ ውይይት ተካሄደ፤
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት ድጋፍ ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት የ2ኛ መንፈቅ ዓመት የሪፎርም እና መደበኛ ስራዎች እቅድ ላይ፣ በስሩ ከሚገኙ ስራ አስፈጻሚዎች እና ሰራተኞች ጋር፣ ጥር 21 ቀን 2018 ዓ/ም፣ በህዳሴ አዳራሽ ውይይት አካሄደ ፡፡
ውይቱን የመሩት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) ሲሆኑ፣ የውይይቱ ዓላማ፣ በአጠቃላይ በዩኒቨርሲቲ ደረጃ ያለው የለውጥ ስራ ምን እንደሚመስል እና ምን ደረጃ ላይ እንደደረሰ ለማብራራት፣ እንዲሁም በቀሪው ስድስት ወር እያንዳንዱ የስራ ክፍል ምን መስራት እንዳለበት ለማስገንዘብ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አስከትለውም፣ በዩኒቨርሲቲ ደረጃ ውጤታማ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸው፣ “ቢሆንም እንዳንዱ ክፍል በእኩል ደረጃ እየተንቀሳቀሰ አይደለም፤ አንዳንዱ የስራ ክፍል እያለ የለም፤ አንዳንዱ በጥቂቱም ቢሆን እንቅስቃሴ ያደርጋል፤ አንዳንዱ የስራ ክፍል ዋና ተዋናይ ሆኖ እያገዘ ነው፡፡” በማለት የስራ ክፍሎች ያሉበትን የአፈጻጸም ደረጃ አመላክተዋል፡፡ ድክመት ያሳዩ የስራ ክፍሎችን ለስራ እንዲነሳሱ ለማድረግ ባለመው ንግግራቸው፣ “መኖራችንን የምናረጋግጠው በመስራታችን ነው፡፡” ሲሉ በአጽንኦት ማሳሰቢያ ሰጥተዋል፡፡
በመቀጠልም ፕሬዝደንቱ፣ በዩኒቨርሲቲው እየተካሄዱ ያሉ ሪፎርሞችን ዘርዝረው፣ እያንዳንዱ ሪፎርም ምን ምን ገጽታዎች እንዳሉት ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ሪፎርሞቹ የራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ሪፎርም፣ የተግባር ዩኒቨርሲቲ ሪፎርም እና ሀገራዊ ሪፎርም የሚሉ ሶስት ዓይነት ሪፎርሞች መሆናቸውን አመላክተው፣ ሀገራዊ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ሪፎርሙን ተከትሎ፣ በዩኒቨርሲቲው እየተሰራ ባለው ሪፎርም መሰረት፣ የኢንደስትሪ እና የሙያ ምድብ ዝርዝር ተሰርቶ ማለቁን፣ መዋቅሩም እስከ ጥር 30 ቀን 2018 ዓ/ም ተሰርቶ እንደሚጠናቀቅ ገልጸዋል፤ በቀጣይም የስራ ዝርዝር እና የቴክኒካል ብቃት ሰነዶች ተዘጋጅተው፣ የሙያተኛ ምዘና እንደሚደረግ በሰፊው አብራርተዋል፡፡
በመጨረሻም፣ በቀጣዩ ስድስት ወር እያንዳንዱ የስራ ክፍል በምን ተግባር ላይ ማተኮር እንዳለበት አቅጣጫ ሰጥተው እና ከቤቱ ለቀረበላቸው አስተያየት ጥያቄ ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተው ውይይቱ ተጠናቋል፡፡
Visit our website: http://www.epsu.edu.et/
Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
Follow us on LinkedIn: https://www.linkedin.com/.../ethiopian-public.../about/
Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt
ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት at EPSU
PR call: 0945746405
EPSU at Ethiopian University Students Sport Festival
Ethiopian Public Service University (EPSU) participated in the Ethiopian University Students Sport Festival, hosted by Jimma University. The university was represented by a 19-member sports delegation—including 16 male and 3 female participants—who competed in volleyball, chess, and table tennis events.
EPSU’s participation was limited due to a scheduling overlap with the final examination period for undergraduate students. As the university recently began admitting students directly through the Ministry of Education, the majority of first-year students were engaged in exams during the festival. This overlap restricted broader participation and resulted in EPSU competing in only a few sports disciplines.
The Ethiopian University Students Sport Festival aims to promote national unity, encourage cultural exchange, and strengthen shared values among students through sports. Despite these constraints, EPSU’s delegation actively contributed to the festival’s objectives and demonstrated strong commitment and teamwork.
The university extends its appreciation to the sports team members for representing Ethiopian Public Service University with professionalism and pride at the national level.
Visit our website: http://www.epsu.edu.et/
Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
Follow us on LinkedIn: https://www.linkedin.com/.../ethiopian-public.../about/
Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt
ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት at EPSU
PR call: 0945746405
ኢፐሰዩ በእድሳት ላይ የቆየውን የተማሪዎች ካፍቴሪያ አስመርቆ አገልግሎት አስጀመረ፤
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በእርጅና ምክንያት አገልግሎቱ ተዳክሞ የነበረውን የተማሪዎች ካፍቴሪያ፤ ሙሉ እድሳት ተደርጎለት፣ በአዲስ መልክ አገልግሎት እንዲሰጥ ጥር 18 ቀን 2018 ዓ/ም አስመረቀ፡፡
በምረቃ መርሃ - ግብሩ ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) በዩኒቨርሲቲው ውስጥ እድሳት ብቻ የሚፈልጉ በርካታ ህንጻዎች መኖራቸውን ገልፀው፣ “ዩኒቨርሲቲው ያጣው ነገር እይታ ብቻ ነው፡፡” ብለዋል፡፡ በማስከተልም ካፍቴሪያው ያለበት ስፍራ ለአገልግሎት ምቹ መሆኑ፣ ለተማሪዎች አማራጭ አገልግሎት መስጫ በማስፈለጉ እና የተሸለ አገልግሎት ማግኘት ለሚፈልግ ሁሉ የሚሰጠው ጠቀሜታ ከፍ ያለ መሆኑን በመገንዘብ የእድሳቱ መከናወኑን አብራርተዋል፡፡
ፕሬዝዳንቱ ዶ/ር ንጉስ የዩኒቨርሲቲውን ግቢ አጠቃላይ ገጽታ በገለጹበት ንግግራቸው፣ “ይሄ ግቢ ሁሉ ነገር ያለው ግቢ ነው፤ ይሄ ግቢ የጎደለው እይታ ነው፤ ይሄ ግቢ የጎደለው መስራት ነው፡፡ አዲስ ነገር ሳንጨምር ባለው ነገር ላይ ብንሰራ፣ ልናሻግረው እንችላለን፡፡ ይሄ ግቢ ሰው አለው፤ ከሞላ ጎደል የሚታደሱ ህንጻዎች አሉት፤ ስለዚህ ባለው ነገር ላይ ትንሽ ብንጨምር፣ ብዙ ለውጥ እናመጣለን፤ ይሄ ካፍቴሪያ የዚህ ዓይነቱ አስተሳሰብ ውጤት ነው፡፡” በማለት ባለው ነገር ላይ በመስራት ብዙ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል አስገንዝበዋል፡፡
በመግቢያው ላይ የስልጠና ፋሲሊቲ መስተንግዶ አገልግሎት ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ፍሬሕይወት አበራ፣ ከእድሳት በፊት ካፍቴሪያው የነበረበትን ተስፋ አስቆራጭ ሁኔታ አስታውሰው፣ ለዛሬው ውጤት እና ስኬት ትልቁን ሚና የተጫወቱት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ መሆናቸውን ገልጸው አመስግነዋቸዋል፡፡ ቀጥለውም፣ “ለሁሉም የስራ ክፍሎች የምሰጠው ምክር፣ በስራ ክፍላችሁ ለመስራት የምትመኙት፣ ለስራው ውሳኔ ሰጪ አጥታችሁ የተቆጫችሁበትን ስራ ካለ፣ አፋጣኝ ውሳኔ የሚሰጥ አመራር ያለው አሁን ስለሆነ ጊዜውን ተጠቀሙበት፡፡” በማለት አሳስበው፣ አሁን ያለው የዩኒቨርሲቲው አመራር ለውሳኔ አሰጣጥ ያለውን ቁርጠኛነት አድንቀዋል፡፡
Visit our website: http://www.epsu.edu.et/
Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
Follow us on LinkedIn: https://www.linkedin.com/.../ethiopian-public.../about/
Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt
ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት at EPSU
PR call: 0945746405
PhD Candidates Showcase Dissertation Progress at EPSU Review Session
Today, third-year PhD students in the Public Policy program presented updates on the status of their dissertation progress in the presence of their respective academic advisors, the EPSU Postgraduate Program Director, Dr. Amsalu Bedemo, and the College of Leadership, Management and Governance’s Postgraduate Program Coordinator, Dr. Rahmeto Negash. The session was organized and coordinated by Dr. Tewodros Abuhay, PhD in Public Policy Program Coordinator at Department of Policy Studies.
The presentations offered a structured overview of each student’s progress in relation to their approved dissertations, agreed research timelines, and the level of supervisory engagement. The session also served as an important academic platform for reflection, feedback, and alignment with program expectations. Based on the discussions and evaluations, it was noted that some students are progressing more slowly than the program’s established milestones for this stage of doctoral study. In response, emphasis was placed on the importance of strengthened supervisory follow-up, with respective advisors expected to closely monitor student progress, provide timely academic guidance, and offer continuous technical support to help address identified gaps and support steady advancement toward completion.
Visit our website: http://www.epsu.edu.et/
Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
Follow us on LinkedIn: https://www.linkedin.com/.../ethiopian-public.../about/
Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt
ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት at EPSU
PR call: 0945746405
Ethiopian Public Service University
Launches Comprehensive Institutional Reform
Ethiopian Public Service University (EPSU) is undertaking a comprehensive reform across all its sectors to strengthen its role in producing competent, professional, and internationally competitive public servants. This deep reform reflects the University’s strong commitment to modernizing public service education and aligning it with global standards.
As part of this transformation, the University has officially revised its Vision, Mission, and Motto to better respond to the evolving needs of the public sector and to support Ethiopia’s national development agenda. These revisions provide a clear strategic direction and reaffirm EPSU’s dedication to excellence, innovation, and public sector leadership.
The University is pleased to share these important updates with its academic community, partners, alumni, and stakeholders, and encourages everyone to embrace and apply them in their respective roles.
Mission of the university
To deliver quality and specialized Education, Research, training, consultancy, and community engagement programs to produce competent public servants and leaders, thereby, contributing towards he development of technology driven, innovative, and modern public sector.
Vision of the university
To become Africa’s leading university for public service excellence and innovation by 2035
Motto
We are for the public sector.
Visit our website: http://www.epsu.edu.et/
Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
Follow us on LinkedIn: https://www.linkedin.com/.../ethiopian-public.../about/
Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt
ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት at EPSU
PR call: 0945746405
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የ2018 በጀት ዓመት በሁለተኛ መንፈቅ ዓመት ትኩረት በሚሹ የመደበኛ እና የለውጥ ስራዎች ላይ ውይይት አካሄደ፡፡
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣ ጥር 14 ቀን የ2018 ዓ.ም በአባይ አዳራሽ፣ መላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በተሳተፉበት ስብሰባ፣ በሁለተኛ መንፈቅ ዓመት በሚከናወኑ ትኩረት በሚሹ የመደበኛ እና የለውጥ ስራዎች ላይ ውይይት አካሄደ፡፡
ስብሰባው ላይ ተገኝተው ከሰራተኞቹ ጋር ውይይት ያካሄዱት፣ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር)፣ በበጀት ዓመቱ ሁለተኛ መንፈቅ ዓመት፣ ትኩረት የሚሹ የመደበኛ እና የለውጥ ስራዎችን ዘርዝረው፣ የአፈጻጸም አቅጣጫዎችንም አብራርተዋል፡፡ በማብራሪያቸው እንደተናገሩት፣ በአንደኛው መንፈቅ ዓመት የነበረው የመደበኛ እና የለውጥ የስራዎች አፈጻጸም ሪፖርት፣ በዩኒቨርቲው ካውንስል ተገምግሞ እና በማናጅመንት ኮሚቴ ጸድቆ፣ በስራ አመራር ቦርዱ ውሳኔ ለሚመለከታቸው አካላት የተላከ መሆኑን አስታውሰዋል፤ እንዲሁም የሁለተኛው መንፈቅ ዓመት የመደበኛ እና የለውጥ ስራዎች እቅድ፣ በስራ አመራር ቦርዱ የአፈጻጸም አቅጣጫ ተሰጥቶበት፣ ወደ ትግበራ የተገባ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በማስከተልም፣ ሁሉም ሰራተኛ በእቅዱ ላይ እንዲወያይ የመደረጉን አስፈላጊነት ሲናገሩ፡- “የለውጥ ስራ በባህሪው ሁሉም ሰራተኛ እንዲሳተፍበት ይጋብዛል፤ በመሆኑም፣ ቁጭ ብለን ተመካክረን፣ ከየት ተነስተን የት እንደምንደርስ ግልጽ የሆነ መግባባት ላይ ካልደረስን እና ጉዞውን የጋራ ካላደረግነው፣ የተወሰነ አካል የሚመኘው፣ የተወሰነው ደግሞ መዳረሻውን ያልተገነዘበው ጉዞ ይሆንብናል፡፡” በማለት ለውይይቱ አስፈላጊነት አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
በመቀጠልም፣ ከዩኒቨርሲቲው የለውጥ ስራዎች አንዱ የሆነው “የተቋማዊ ጥራት እስታንዳርድ መመሪያ” ረቂቅ ሰነድ፣ የትምህርት እና ስልጠና ጥራት ማሻሻያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር እና የዚሁ ኮሚቴ ሰብሳቢ በሆኑት፣ በዶ/ር አድማሱ ቴሶ አማካኝነት ቀርቦ፣ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡ ረቂቅ ሰነዱ የተዘጋጀበትን ገፊ ምክንያት ዶ/ር አድማሱ ቴሶ ሲያብራሩ፣ የዩኒቨርሲቲው ተቆጣጣሪ መስሪያ ቤት የሆነው፣ የኢፌዲሪ የትምህርት እና ስልጠና ባለስልጣን፣ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የሚያወጣቸውን የተለያዩ ስታንዳርዶች ተቋማዊ አድርጎ ለመተግበር፣ ለዩኒቨርሲቲያችን የተሰጠውን ልዩ ተልዕኮ ወደ ማህበረሰቡ ለማድረስ እና ለዩኒቨርሲቲው የራስገዝነት ጉዞ መደላድል ለመፍጠር ታስቦ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በማስከተልም “የተግባር ዩኒቨርሲቲ ከምርምር ዩኒቨርሲቲ ይልቅ ስታንዳርዳይዝ እና ዩኒፎርሚቲ መሆንን ስለሚጠይቅ፣ በእነዚህ እና በሌሎች ገፊ ምክንያቶች ሰነዱ ሊዘጋጅ ችሏል፡፡” በማለት የሰነዱን ፋይዳ አብራርተዋል፡፡
በመጨረሻም ከተሰብሳቢዎቹ ለቀረቡት ጥያቄዎች እና አስተያየቶች በፕሬዘዳንቱ ምላሽ እና ማብራሪያ ተሰጥቶ ውይይቱ ተጠናቋል፡፡
Visit our website: http://www.epsu.edu.et/
Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
Follow us on LinkedIn: https://www.linkedin.com/.../ethiopian-public.../about/
Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt
ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት at EPSU
PR call: 0945746405
በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የቃል-ኪዳን ቤተሰብ ትስስር ፕሮጀክት ለአንደኛ ዓመት ተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ፤
በኢፐሰዩ የተማሪዎች አገልግሎት ዲን በአዲስ ምእራፍ ተልእኮ ለዩኒቨርሲቲው ከትምህርት ሚኒስቴር ለተመደቡለት የመጀመሪያ ዲግሪ አንደኛ አመት ተማሪዎች፣ ጥር 4 ቀን 2018 ዓ.ም በኦሞ አዳራሽ ስለ ቃል-ኪዳን ቤተሰብ ትስስር የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ፡፡
መርሃ ግቡሩን በ“እንኳን ደህና መጣችሁ” መልእክት የከፈቱት፣ የአስተዳደር እና ልማት ምክትል ፕሬዘዳንት ተሸመ ዱላ (ዶ/ር) ሲሆኑ፣ የቃል-ኪዳን ቤተሰብ ትስስር ለተማሪዎች ያለውን ፋይዳ ሲያስረዱ፣ “የቃል-ኪዳን ቤተሰብ ትስስር፣ ከቤተሰባችሁ ርቃችሁ በመምጣታችሁ፣ የሚፈጠርባችሁን ባይተዋርነት አስወግዶ፣ ላላችሁበት ማህበረሰብ ስነ-ልቦናዊ ቅርበት እንዲኖራችሁ ያደርጋል፤ ይህም በዩኒቨርሲቲ ቆይታችሁ ሊፈጠሩባችሁ የሚችሉ ጫናዎችን በማቃለል፣ የትምህርት ቆይታችሁን በጥሩ ውጤት እንድታጠናቅቁ ያስችላችኋል፡፡” ብለዋል፡፡
ቀጥሎም በተማሪዎች አገልግሎት ዲን አማካኝነት ከተቋቋመው የቃል-ኪዳን ቤተሰብ ኮሚቴ ጋር ትውውቅ ተካሂዶ፣ ስለፕሮጀክቱ ዓላማ ለተማሪዎቹ ገለጻ ተደርጎላቸዋል፤ በሰነዱ ላይ እንደተመላከተው የፕሮጀክቱ ዓላማ፣ ተማሪዎቹ ከአዲስ አበባ ውጪ ካሉ የሀገራችን ክፍሎች የመጡ እንደ መሆናቸው መጠን፣ ከአዲስ አበባ ነዋሪዎች ጋር ጥብቅ ቤተሰባዊ ትስስር እንዲኖራቸው፣ ከሚመሰርቱት የቃል-ኪዳን ቤተሰብ ተገቢውን ፍቅር እንዲያገኙ፣ ቤተሰባዊ እንክብካቤ፣ ክትትል እና ድጋፍ እንዲደረግላቸው፣ እንዲሁም አካባቢውን ለመማር ማስተማር እና ለምርምር ምቹ ለማድረግ ታስቦ የታቀደ ፕሮጀክት መሆኑን ለመረዳት ተችሏል፡፡
የተማሪዎች አገልግሎት ዲን በላከው መግለጫ፣ ይህ ፕሮጀክት በቀጣይነት በሚያከናውናቸው ተግባራት፣ ተማሪዎቹ ባይተዋርነት ሳይሰማቸው የአዲስ አበባን ጉዳይ ጉዳያቸው አድርገው በማህበራዊ; በፖለቲካዊ እና በኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ያደርጋል፤ ሃገራዊ አንድነትን ለማሳደግና የጋራ መግባባት ለመፍጠር የበኩሉን አስተዋጽኦ ያደርጋል፤ እንዲሁም ተማሪዎቹ በመጡበት እና በአዲስ አበባ ማህበረሰብ መካከል መልካም ግንኙነት በመፍጠር መሰረትን ይጥላል ብሏል፡፡
Visit our website: http://www.epsu.edu.et/
Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
Follow us on LinkedIn: https://www.linkedin.com/.../ethiopian-public.../about/
Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt
ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት at EPSU
PR call: 0945746405
