ሰዋስው ☘☘☘☘
الذهاب إلى القناة على Telegram
በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።
إظهار المزيد1 161
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
1 161
#ገብርኤል_ኃያል
#ገብርኤል_ኃያል
ገብርኤል ኃያል መልአከ ሰላም መልአከ ብሥራት
የምታወጣ የእግዚአብሔርን ሕዝብ ከሚነድ እሳት
ፍቅርህ ተስሏል በልባችን
ፊትህ ቆመናል ባርከን ብለን
#አዝ...
የጽናታቸው ዝናው ሲሰማ
ከዛ ባቢሎን ከሞት ከተማ
ህፃናት ሳሉ በራ እምነታቸው
ቆመህ ተገኘህ መሐከላቸው
#አዝ...
ውኃው ሲዘል ቢያስደነገጥም
በጋኖቹ ውስጥ ቢነዋወጥም
ፀንተው ዘመሩ ልጅና እናቱ
አንተ ስትደርስ ከዚያ ከእሳቱ
#አዝ...
ቂርቆስም ፀና ሞተን ሳይፈራ
አንተ ስላለህ ከነርሱ ጋራ
አትፍሪ አላት ስለምን ትፍራ
አምነው ድል ነሱት ያንን ተራራ
#አዝ...
እኔም አምናለሁ አድነኝ ብዬ
ፈጥነህ አማልደኝ ከቸር ጌታዬ
ክፉውን ዘመን የማልፍበት
ፅናቱን ስጠኝ ድል ልንሳበት
ለመቀላቀል_ሰማያዊውን_ይጫኑ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/Eotcw
1 161
#ደቂቀ ልዑል
አናኒያ አዛርያ ወሚሳኤል ደቂቀ ልዑል
ስለፀኑ ነው በእምነታቸው
ከእሳት ነበልባል ያዳናቸው
እንዳዳናቸው ፈጥኖ ደርሶ
በእሳት መካከል ተመላልሶ
መልአከ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል
ያድነናል ከነበልባል
ከነበልባል እንድንድን
የአምላክ ወገኖች እንድንሆን
መፅናት አለብን በሀይማኖት
ፍቅርም ይኑረን በአንድነት
ፍፁም ከፀናን በሀይማኖት
አይለየንም የከምላክ ምሕረት
እስከዘለአለም
ለመቀላቀል_ሰማያዊውን_ይጫኑ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
★ https://t.me/Eotcw
1 161
#ለአናኒያ ወአዛርያ
ለአናኒያ ወአዛርያ ወሚሳኤል(2)
ወሚሳኤል ውእቱ ያድኀነነ(2)
ለመቀላቀል_ሰማያዊውን_ይጫኑ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
★ https://t.me/Eotcw
1 161
#መዝሙር
#ሊቀመላዕክት_ገብርኤል
ሊቀመላዕክት ገብርኤል ዘአብሰራ ለድንግል
#ሀያል_ሀያል*4 #ሰዳዴ_ሳጥናኤል*2 ሀያል መልዐከ ሀይል
ለመቀላቀል_ሰማያዊውን_ይጫኑ___share🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
★ https://t.me/Eotcw
1 161
#የራማው ልዑል
የራማው ልዑል ገብርኤል (2)
ተመላለስ መሐላችን ስምህን ጠርተን ንአ ስንል (2)
ብርሃን ልብሱ እሳታዊ መልአክ
አንተ አማልደን ከመሃሪው አምላክ (2)
#አዝ….
የምስራች ነጋሪ ድንቅ ልደት አብሳሪ
የጽድቅ ፋና የምህረት ጎዳና (2)
#አዝ….
ላመኑብህ ለተማጸኑብህ
ፈጥኖ ደራሽ አለኝታቸው ነህ (2)
#አዝ….
የአናንያ የአዛርያ የሚሳኤል ጠባቂያቸው
ከእሳት ነበልባል ያዳንካቸው (2)
#አዝ….
ምሰሶ አምባችን መጠጊያችን
ቅዱስ ገብርኤል ጠባቂያችን (2)
#አዝ….
ዕለት ዕለት የምንማልድህ
ልጀችህን ይምራን መንፈስህ /2
#ለመቀላቀል #ከታች #ሠማያዊውን #ይጫኑ
#JOIN #OUR #CHANNEL
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
👆👆👆👆👆 https://t.me/Eotcw 👆👆👆👆👆👆👆
1 161
እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል አመታዊ ክብረ በዓል በሠላም አደረሳችሁ!
ታህሳስ 19 ቀን በዚህ ቀን ሰለስቱ ደቂቅ "የምናመልከው አምላካችን ከሚነደው ከእሳቱ እቶኑ ሊያድነን ይችላል" ያሉበት ዕለትና ቅዱስ ገብርኤል ከእሣት ያዳቸው ዕለት መታሰቢያ በዓል ነው።
ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን አባቶቻችን እንዳስተማሩን ነገሩ እንዲህ ነው። ዘመኑ ጣኦት የሚመለክበት ንጉስ ናቡከደነፆር የእግዚአብሔር ሰዎች የቅዱስ ገብርኤል ወዳጆች የነበሩት ወጣቶች ሥም አይጣላልናንያ (ሲድራቅ) ፤ አዛርያ (ሚሣቅ) ፤ ሚሣኤል (አብድናጎ) ነበሩ። ት/ዳንኤል 3፡1-30 ታሪኩ እንደሚግረን ንጉስ የጣኦት ምስል አሰራ በገሊላ አውራጃ ያለውን ሕዝብ ጠርቶ ለጣኦቴ ያልሰገደ ወደ እሣት ውስጥ ብሎ አወጀ።
በዚህ መካከል ሰልስቱ ደቂቅ ነበሩ። የንጉስ ትህዛዝ ነውና ሕዝቡ ሁሉ ለጣኦቱ ሲንበረከክ እነርሱ ግን ቆመው ያዩ ነበር። የእግዚአብሔር የሆነ ሰው ምንም ነገር አያስፈራውምና ናቡከደነፆር እርሱ ላስቆመው ጣኦት አለመስገዳቸውን ሲሰማ ተናደደ ፤ ተበሳጨም እሳቱን 7 እጥፍ እንዲነድ አስደረገ ሦስቱንም አስሮ እሣቱን እያሳየ "ከመቃጠል ወይስ ለእኔ ጣኦት መስገድ የቱ ይሻል?" ባላቸው ጊዜ የምናመልከው አምላካችን ከሚነደው ከእሳቱ እቶን ሊያድነን ይችላል ባያድነንም እንኳን አንተ ለመታመልከው ጣኦት አንሰግድም አሉት።
በዚህ ጊዜ ጉልበት ያላቸው ሠዎች ተፈልገው ሦስቱን ወጣቶች አስረው ወደ እሣት ቶን ውስጥ ጣሏቸው አስረው የጣሉቸው ወታደሮች የእሣቱ ወላፈን አቃጠላቸው ሠልስቱ ደቂቅን ግን መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ እሳቱን አበረደላቸው አጠፋላቸው።
በዚህም ጊዜ ንጉስ ናቡከደነፆር እንዲህ በማለት መሰከረ "እኛ አስረን የጣልናቸው ሦስት ነበሩ አሁን ግን አራተኛው ሰው በእሳቱ ሲመላለስ ይታየኛል እንዲያውም የአማልክትን ልጆች ይመስላል " አለ። የእግዚአብሔር የማዳኑ ስራ ሲገለጥ ቅዱስ ገብርኤል ሲታይ አዋጁ ሁሉ ተሻረ ጉልበት ሁሉ ለጣኦት ተብሎ የነበረው "ጉልበት ሁሉ ለሰልስቱ ደቂቅ አምላክ ይስገድ ይንበርከክ" ተባለ ይህን ሁሉ ታህሳስ 19 ቀን ሆነ በዚህም ምክንያት በታላቅ ደስታ እናከብረዋለን!
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን የመላዕክት የቅዱስ ገብርኤል ጥበቃው ረድኤት በረከቱ አይለየን አሜን!
Join https://t.me/Eotcw
1 161
26/1/2015 ዓ.ም (፳፮/፩/፳፻፲፭ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በቅድመ መላእክቲከ እዜምር ለከ።
ወእሰግድ ውስተ ጽርሐ መቅደስከ።
ወእገኒ ለስምከ፡፡ መዝ 137:1
🕯 ትርጉም
በመላዕክት ፊት እዘምርልሃለሁ።
ወደ ቅድስናህ መቅደስ እሰግዳለሁ።
በስምህ ሁሉ ላይ ቅዱስነትህን ከፍ ከፍ አድርገሃልና፡፡
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
+ + +
❤ "ሰላም ለአእዛኒከ ኆኅ (ያ) ተ ቃለ አብ ሕያው። ወለመላትሒከ ልሑያት አምሳላተ ጽጌ ዘበድው። ኦ ገብርኤል መልአከ አድኅኖ ፍንው። አድኅነኒ ዘአድኀንኮሙ በአክናፊከ ምንትው። አመ ውስተ እሳት ተወድዩ ሠለስቱ ዕደው"። ትርጉም፦ ቅዱስ ገብርኤል ሆይ የአብ አካላዊ ቃል መሳክወ ብርሃን ለሚሆኑ ጆሮችህ ሰላም እላለሁ። የውበታቸው ጸዳል የበረኃ አበባ ለሚመስለውም ጉንጮችህ ሰላም እላለሁ፤ ቅዱስ ገብርኤል ሆይ ከጭንቅና ከመከራ ለማውጣት የተላክህ መልአክ ነህና። ሠለስቱ ደቂቅ በእሳት ጉድጓድ በተጣሉ ጊዜ ሁለቱ ክንፎችህን ጋርደህ ከመቃጠል እንዳዳንሃቸው እኔንም አገልጋይህን በረድኤትህ ኃይል አድነኝ። መልክአ ቅዱስ ገብርኤል።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
+ + +
❤ የዕለቱ ምልጣን ግዕዝ ዜማ፦ ሃሌ ሉያ "ወእንዘ ትፈትል ወርቀ ወሜላተ አስተርአያ ገብርኤል ግብተ ወይቤላ እስመ ረከብኪ ሞገሰ በኀበ እግዚአብሔር ወትቤሎ ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ"፡፡ ትርጉም፦ ሐርና ወርቅን እያስማማች ስትፈትል ድንገት ቅዱስ ገብርኤል ታያት በእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስን (ባለሟልነት) አግኝተሻልና አላት እንደምትለኝ (እንደቃልህ) ይሁንልኝ አለችው።
+ + +
❤ የዕለቱ እግ ነግ ዓራራይ ዜማ፦ "ገብርኤል አብሠራ ለማርያም ተፈሥሒ ይቤላ ኢሳይያስ ይቤላ ሐዳስዩ ጣዕዋ ሰሎሞን ይቤላ ደብተራ"፡፡ ትርጉም፦ ገብርኤል ለማርያም የምስራችን ነገራት ደስ ይበልሽ አላት ኢሳይያስም አዲሲቷ እንቦሳ አላት የሰሎሞን ድንኳን አላት። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ታኅሣሥ ፲፱ (19) ቀን።
❤ እንኳን ለኢትዮጵያውያኑ ጻድቅ ለታላቁ አባት እግዚአብሔር አምላክ ብዙ ቃል ኪዳን ለገባላቸው ለአቡነ አባለ ክርስቶስ ለዕረፍት በዓል፣ ተንቤን ውስጥ የሚገኘውን አስደናቂውን የውቅን ቅዱስ ገብርኤል ፍልፍል ዋሻ ቤተ መቅደስ ለሠሩት ለታላቁ አባት ለአቡነ ዳንኤል ዘተንቤንና መልአከ ሞት ከበራቸው ላይ ለሦስት ወር ላቆሙ ለታላቁ አባት ለአቡነ ስነ ኢየሱስ ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን።
+ + +
❤ አቡነ አባለ ክርስቶስ፦ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ አቡነ አባለ ክርስቶስ ዘደብረ መድኃኒት ጻድቁ አቡነ አባለ ክርስቶስ ከአባታቸው ቅዱስ አቃርዮስ እና ከእናታቸው ቅድስት ታውክልያ በ8ኛው ክፍለ ዘመን በየካቲት 19 810 ዓ.ም በአክሱም ከተማ የተወለዱ ጻድቅ ሲሆኑ ከሰውነታቸው ማሀል ዲካባ፣ ማርትያስ፣ ክስብኤል የሚሉ ኅቡአን የሥላሴ አስማት ተጽፎውላቸው የተወለዱ ጻድቅ ናቸው።
❤ በዚሁ መሰረት ከጻድቁ አቡነ ጰንጠሌዎን በሠላሳ ሁለት ዓመታቸው ሙንኲስናን ከተቀብሉ በኋላ ጽላትን ለ24 ዓመታት ያህል እያጠኑ ከቆዩ እንደ ሌሎቹ ቅዱሳን ዛሬ ገደማቸው በሚገኝበት እና አፅማቸው ካረፈበት ገዳማቸው ተጋድሎን በመፈጸም ከፈጣሪያቸው በታሕሳስ 19 ቀን ቃልኪዳን ተቀብለው በ332 ዕድሜያቸው ያረፉ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ ናቸው።
❤ ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጣቸው ቃል ኪዳን "ዝክርህን የዘከረ ስምህን የጠራ እስከ 24 ትውልድ ምሬልሀለሁ" አላቸው። "ስምህን በመጥራት የተራቡ ያበላ የተጠሙ ያጠጣ የታረዙትን ያለበሰ ለቤተ ክርስቲያንህ የተለያዩ ምፅዋት የሰጠ እስከ 28 ትውልድ አድነዋለሁ" አላቸው። ማየ ጸሎትህም፣ ፀበልህ፣ የተጠመቁ፣ የታጠቡ እስከ 27 ትውልድ አድነዋለሁ" አላቸው። ገዳምህን ለመሳለም፣ ለመሳም፣ አስበው ያልተሳካላቸው 26 ትውልድ አድነዋለሁ" አላቸው። ቤተ ክርስተያንህን የሰራ በመንግስተ ሰማያት እስከ 33 ትውልድ የብርሃን ማደርያ እሰራለታለሁ አላቸው። ዝክርህን፣ መታሰብያህን፣ ሊያደርግ ብሎ ያሰበ ነገር ግን በተለያየ ምክንያት ሳይሳካለት የቀረ እሰከ 25 ትውልድ አድነዋለሁ" አላቸው።
❤ "በገዳምህ በየዓመቱ እና በየወሩ ቅዱስ ቊረባን የተቀበለ እስከ 35 ትውልድ አድነዋለሁ" አላቸው:: መፅሓፍህን የፃፈ፣ ያነበበ፣ የተረጎመ፣ የሰማ እስከ 28 ትውልድ አድነዋለሁ" አላቸው። "ይህች የምታርፍባት የነበርክ ድንጋይ የመካናት ማህፀን ፈትታ ልጅነት ትሰጣለች" አላቸው። ሰውነታቸው በተለያዩ ሕመሞች፣ በሽታዎች የተያዙ አለቱን ቤተክርስቲያኑን በምትፈለፍልባት የነበርክ በትርህ ታሽቶው ይደናሉ" በማለት በማይሻር ቃሉ ይሀንን ቃል ኪዳንገበቶላቸው በክብር ወደ ሰማያት አረገ።
❤ ገዳሙ የምገኘው ከአክሱም ወደ ማሕበረ ጻድቃን ዴጔ 17 ኪሎሜትር ተጉዘው ማሕበረ ጻድቃን ዴጔ ከተማ ላይ እንደደረሱ ወደ ግራ በመንገጠል 25 ኪ.ሜ እንደተጓዙ ጠላዕ በምትባል ትንሽ ከተማ ቀበሌ ሲደርሱገዳሙ አስደናቂ በሆነ አቀማመጥ ከሚያስደንቅ ሸለቆ ከአለት ተፈልፍሎ የተሰራ ጥንታዊ እና ታሪካዊ ባለ ቃል ኪዳንገዳሙ ያገኙታል። በገዳሙ በየዓመቱ ታሕሳስ 19 ቀን የጻድቁ በዓለ ዕረፍት ፥ የካቲት 19 ቀን የጻድቁ በዓለ ልደታቸው ዓበይት በዓላት ብዙ ምእመናን በተሰበሰቡበት በታላቅ ድምቀት ይከበራል። ጻድቁ ገድለኛ እና ታአምረኛ በመሆናቸው በእሳቸው እጅ ከአለት ተፈልፍሎ የተሠራ ቤተ መቅደስ፣ቅኔ ማህሌት፣ ምቋም ሰዓታት እና ቤተ አንድነት በገዳሙ ውስጥ ይገኛል። ያርፉባት የነበረች ድንጋይ እብነ ሕይወት ተብላ እንድትጠራ እና የመካናት ማህፀን ፈትታ ልጅ እንድ ትሰጥ ቃል ኪዳንየተሰጣት ድንጋይ እና ቤተ መቅደሱን የሚፈለፍሉባት የነበረች በትረ ትእምርት ለምስክር ያህል እስከ አሁን ብዙ ህሙማን እና መካናት እየተፈወሱ በገዳሙ ውስጥ ይገኛሉ።
❤ በገዳሙ ካሉ ቅርሳቅርሶች ከ1000 ዓመት በላይ ዕድሜ ያላቸው መዛግብተ እክል፣ ጎተራዎች፣ ሰፍየዶች፣ ከሸክላ የተሰሩ ፅዋዎች እና ጋኖች በአስገራሚ ሁኔታ እስከ አሁን በገዳሙ ውስጥ ተጠብቀው ይገኛሉ። እንዲሁም በገዳሙ ውስጥ የሚገኙሁለት ዓይነት ጠበል ማለትም መጀመርያ ወደ ገዳሙ ሲገቡ በመስቀላቸው ባርከው ከዐለት ያፈለቁት ማየ ጸሎት እና በዕረፍታቸው ቀን ከመቃብራቸው ከቤተ መቅደሱ ውስጥ የሚመነጭ ማየ ጸሎት ብዙ ህሙማን እየተፈወሱበት የሚገኝ ታሪካዊ ገዳም ነው። ከአባታችን ከአቡነ አባለ ክርስቶስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ Tmihrt Fikre Debre Birhan።
+ + +
❤ አቡነ ዳንኤል ዘተንቤን፦ አገራቸው ትግራይ ዘተንቤን ነው። ዳንኤል ሐዲስ በሚል ስያሜም ይታወቃሉ። በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን የነበሩ ሲሆን ለዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ከሰማይ የወረደላቸውን መስቀል ይይዙት ስለነበር ዛሬ ያንን መስቀል። ትግራይ ወስደውት ውቄን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ውስጥ በክብር አስቀምጠውታል። የዐፄ ዘርዐ ያዕቆብንም መጽሐፈ ነገሥት ተርጓሚ ነበሩ። ጻድቁ እህል ሳይበሉ ውኃም ሳይጠጡ 40ቀንና 40ሌሊት ይጾሙ የነበሩ መናኝ ባሕታዊ ናቸው። እንደ ነቢዩ ኤልሳዕም ሁለት ሙት አስነሥተዋል። ከአባታችን አቡነ ዳንኤል እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።
+ + +
❤ ጻድቅ አቡነ ስነ ኢየሱስ፦ መልአከ ሞት መስከረም 19 ቀን መጥቶ "ጊዜ ዕረፍትህ ደርሷል" ቢላቸው "የቅዱስ ገብርኤልን በዓል ሳላከብር አይሆንም" ብለው መልአከ ሞትን ለ3 ወራት ከበራቸው ላይ ያቆሙት አቡነ ስነ ኢየሱስ በደመና ተጭነው በመዘዋወር በሀገራችን ወንጌልን ሰብከዋል፡፡ ገዳማቸው ታች አርማጭሆ ከሳንጃ ከተማ በእግር የ3 ሰዓት መንገድ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡
❤ ጻድቁ ከሽዋ ምድር ተነሥተው ወደ ታች አርማጭሆ በመሄድ በበረሃ ውስጥ በታላቅ ተጋድሎ ኖረዋል፡፡ በዚያም የሰማዕቱ የቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድን ገዳም ገድመዋል፡፡ አቡነ ስነ ኢየሱስ ብዙ መናንያን አርድእትን ያፈሩ ታላቅ አባት ሲሆኑ አስገራሚ ተአምራትን በማድረግም ይታወቃሉ፡፡ የቅዱስ ገብርኤልን በዓል ሳላከብር አይሆንም ብለው መልአከ ሞትን ለ3 ወራት ከበራቸው ላይ ካቆሙትና በዓሉን ካከበሩ በኃላ በዚኽች ዕለት ታሕሳስ 19 ቀን በሰላም ዐርፈዋል፡፡ ከአባታች ከአቡነ ስነ ኢየሱስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ ከገድላት አንደበት።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ታኅሣሥ ፲፱ (19) ቀን።
❤ እንኳን ለመጋቤ ሐዲስ ለሊቀ መላእክት ለቅዱስ ገብርኤል አናንያን አዛርያን ሚሳኤልን (ሠለስቱ ደቂቅን) ከነደደ እሳት ለዳናቸው ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ ከካህናት ወገን ከሆነ ከሀገረ ቡርልስ ኤጲስቆጶስ ከቅዱስ አባት ከአባ ዮሐንስ ዕረፍት ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ በዚች ቀን የመላእክት አለቃ የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው በዚች ቀን በዚህ ወር እግዚአብሔር ወደባቢሎን አገር ላከው የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ሦስቱን ልጆች አናንያን አዛርያንና ሚሳኤልን ከእሳት ማንደጃ ውስጥ በጣላቸው ጊዜ አራተኛ ገጽ ሁኖ ታየ። የእሳቱም ነበልባል አርባ ዘጠኝ ክንድ ያህል ወላይ ከፍ ከፍ አለ የጨመሩአቸውን ሰዎችና እሳት የሚያንዱትን አቃጠላቸው ይህም የከበረ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል የእሳቱን ነበልባል በበትሩ መትቶ ከሠለስቱ ደቂቅ ላይ አጥፍቶ አዳናቸው ምንም አልነካቸውም እንደ ቀዘቀዘ እንደ ጧት ጤዛ አድርጎታልና።
❤ በዚያንም ጊዜ የአባቶቻችን ፈጣሪ እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን እያሉ ስድስት ቃላትን ተናገሩ በዚህም ከስድስት መቶ ዓመት በኋላ ክርስቶስ እንደሚወለድ ትንቢት ተናገሩ። ከዚህም በኋላ የጌታ እግዚአብሔር ሥራዎቹ ሁሉ ያመሰግኑታል እርሱ ለዘላለሙ ምስጉን ልዑልም ነው እያሉ ሠላሳ ሦስት ጊዜ አመሰገኑት በዚህም በምድር ላይ ሠላሳ ሦስት ዓመት ክርስቶስ እንደሚኖር አመለከቱ።
❤ ስለዚህም አባቶቻችን የቤተ ክርስቲያን መምህራን የመላእክት አለቃ የሆነ የቅዱስ ገብርኤልን የበዓሉን መታሰቢያ እንድናደርግ ሥዓትን ሠሩ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ገብርኤል አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ 12 ስንክሳር።
+ + +
❤ የአገረ ቡርልስ ኤጲስቆጶስ አባ ዮሐንስ፦ የዚህም ቅዱስ ወላጅቹ የከበሩ ናቸው እነርሱም ከገንዘባቸው ለድኆችና ለችግረኞች ይሰጡ ነበር ወላጆቹም በአረፉ ጊዜ የተዉለትን ገንዘብ ወስዶ ቤተ ክርስቲያን ሠራ ዳግመኛም የእግዳ ቤት ሠራ በውስጡም መጻተኞችንና በሽተኞችን ሰብስቦ የሚያገለግላቸው ሆነ የሚሹትንም ሁሉ ያቀርብላቸዋል።
❤ በዚያም ወራት ወደርሱ አንድ መነኵሴ መጣ የምንኵስናንም ሥራ አመሰገነለት ክብሩንም ገለጠለት ያ መነኵሴም ከሔደ በኋላ ገንዘቡን ሁሉ ለድኆች ሰጥቶ አባ ዳንኤል ለአስቄጥስ ገዳም አበ ምኔት ሁኖ በነበረበት ወራት ወደ አስቄጥስ ሒዶ በአባ ዳንኤል ዘንድ መነኰሰ በዋሻ ውስጥም ብቻውን ሁኖ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ። ስለ መልካም ተጋድሎውም ሰይጣናት ቀኑበት ብዙ ዘመንም ታሞ ከኖረ በኋላ በደዌ መቅሠፍት ቀሠፉት።
❤ ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፈወሰውና ኃለኛ ጽኑዕ አደረገው በእግዚአብሔርም ፈቃድ ቡርልስ በሚባል አገር ላይ ኤጲስቆጶሰነት ተሾመ በዘመኑም በአገሮች ውስጥ ብዙ ኑፋቄ ነበር እርሱም እንክርዳዱን ከሥንዴ መካከል ይነቅል ዘንድ ብዙ ድካምን ደከመ ከላይኛው ግብጽ የሆነ አንድ ሰው ነበረ ብዙ ነገርንም ይቀርባጥር ነበር የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ምሥጢር ይገልጥልኛል በማለት እርሱ ብዙ ሰዎችን አሳታቸው ይህንንም በአወቀ ጊዜ ይዘው ይገርፋት ዘንድ አዘዘ ስሕተቱንም አመነ ከአገርም አሳደዱት።
❤ ነቢይ ዕንባቆም ይታየኛል ብዙ ምሥጢራትንም ይገልጥልኛ የሚል ሌላ ሰው ነበር ብዙዎችም ተከተሉት እርሱንም አሳደደው ትምህርቱንም አጠፋ መጻሕፍቱንም ቀደደ የሳቱትንም ወደ ቀናች ሃይማኖት መለሳቸው። ይህ አባ ዮሐንስ መሥዋዕት ለማሳረግ በሚቀድስ ጊዜ ፊቱ እሳት ይሆናል ሥጋውም ከእሳት ማንደጃ ውስጥ እንደወጣ ይሆናል ዕንባውም እንደ ዝናብ ይዘንባል የመላእክትን ሠራዊት በመሠዊያው ዙሪያ በመሠዊያው ዙሪያ በግልጥ ያያቸዋልና። ኅብስቱ በሚፈተት ጊዜ ሦስቱን የመፈተቻ ምስጋናዎች አንብቦ ጽዋውን ሲባርከው እንደ ፍም የጋለ ሁኖ ጽዋውን ያገኘዋል።
❤ በኋላ በዘመኑ በቀን ከበሉ በኋላ በአንድ ቀን ሁቸተኛ የሚቆርቡ ክፉዎች ሰዎች ተነሡ አስተምራቸው ገሠጻቸው ባልተመለሱም ዳግመኛ አወገዛቸው ባልተመለሱም ጊዜ ስለርሳቸው ጌታን ለመነው እሳትም ከሰማይ ወርዶ አለቃቸውን አቃጠለው የቀሩትም ይህን አይተው እጅግ ፈሩ ተጸጽተውም ወደ ቀናች ሃይማኖት ተመለሱ።
❤ ከዚህም በኋላ ከዚህ ከኃላፊው ዓለም እግዚአብሔር ሊአሳርፈው በወደደ ጊዜ ቅዱሳን አባ እንጦስና አባ መቃርስን ወደርሱ ላካቸው እነርሱም ዕረፍቱ እንደ ደረሰ አስረዱት ሕዝቡንም ሰብስቦ ሕግና ሥርዓትን እንዲጠብቁ እርስ በርሳቸውም ይፋቀሩ ዘንድ በቀናች ሃይማኖትም እንዲጸኑ አዘዛቸው ከዚህም በኋላ በመኝታው ላይ ጋደም ብሎ ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት በአባ ዮሐንስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ 19 ስንክሳር።
+ + +
❤ "ሰላም ለሠለስቱ ደቂቅ እለ ዐበዩ ሰጊደ ለምስል ዘወርቅ እለ ስሞሙ አናንያ ወአዛርያ ወሚሳኤል እለ ኮኑ ሰማዕተ በዕቶነ ባቢሎን እለ አጥፍዑ ዘእሳት ኃይለ ወለጐሙ ነበልባለ፤ እለ ድኅኑ እሞት ወባረክዎ ለእግዚአ ስብሐት በቡራኬ ኵሉ ፍጥረት"። ትርጉም፦ ለወርቁ ምስል መስገድን እንቢ ላሉ፤ ስማቸውም አናንያ፣ አዛርያና ሚሳኤል ለተባሉ፤ በባቢሎን የእሳት ምድጃ ምስክርን ለኾኑ፤ የእሳትን ኃይል አጥፍተው ነበልባሉን የከለከሉ (የገቱ) ለኾኑ ከሞትም ድነው የክብር ጌታን በፍጥረት ኹሉ ምስጋና ላመሰገኑት ለሦስቱ ሕፃናት ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ።
+ + +
❤ የዕለቱ ማኅሌት ምስባክ፦ "ባርክዎ ለእግዚአብሔር ኵሎሙ መላእክቲሁ። ጽኑዓን ወኃያላን እለ ትገብሩ ቃሎ። ወእለ ትሰምዑ ቃለ ነገሩ። መዝ 102፥20-21። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 12፥29-34።
+ + +
❤የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "በቅድመ መላእክቲከ እዜምር ለከ። ወእሰግድ ውስተ ጽርሐ መቅደስከ። ወእገኒ ለስምከ"። መዝ 137፥1-2። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ተሰ 1፥6-ፍ.ም፣ ይሁ 1፥20-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 7፥30-35። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 1፥11-21። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው።መልካም የቅዱስ ገብርኤል በዓልና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት።
https://t.me/Eotcw
