ar
Feedback
ሰዋስው ☘☘☘☘

ሰዋስው ☘☘☘☘

الذهاب إلى القناة على Telegram

በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።

إظهار المزيد
1 161
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
#ጥምቀት መጣልን ደሞ እንደ #ኮኮብ ልናበራ ነው በጉጉት የምንጠብቀዉ ጥምቀት ደረሰ ማን ነዉ የጥምቀት እልልታው ፣ የእጣኑ ሽታ ፣ የህፃናት ሳይደክሙ እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑበት ድምፃቸው ገልበታቸ
+1
#ጥምቀት መጣልን ደሞ እንደ #ኮኮብ ልናበራ ነው በጉጉት የምንጠብቀዉ ጥምቀት ደረሰ ማን ነዉ የጥምቀት እልልታው ፣ የእጣኑ ሽታ ፣ የህፃናት ሳይደክሙ እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑበት ድምፃቸው ገልበታቸው የናፈቀው ? እረ እንደውም ግፊያዉም እኮ ሲናፍቅ 🙏

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 ሥርዓተ ማኅሌት ዘሥላሴ 'ጥር ፯ 🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂 የማንኛውም ወርኃ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ "ሥርዓተ ነግሥ" ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል። @EOTCW @EOTCW ነግሥ ሰላም ለአብ ዘእምቅድመ ዓለም ነጋሢ፤ ለወልድ ሰላም ሥጋ ማርያም ለባሲ፤ ለመንፈስ ቅዱስ ሰላም ኃጢአተ ዓለም ደምሳሲ፤ ኃይልየ ሥላሴ ወጸወንየ ሥላሴ፤ በስመ ሥላሴ እቀጠቅጥ ከይሴ። @EOTCW @EOTCW ዚቅ ዘለብሰ ስብሐተ፤ ሀሎ ሰማያተ፤ እምድንግል ቃል ሥጋ ኮነ፤ በቤተ ልሔም ተወልደ። ወረብ፦ ዘለብሰ ስብሐተ ዘለብሰ ስብሐተ ሀሎ ሰማያተ፤ እምድንግል ቃል ሥጋ ኮነእምድንግል ቃል። @EOTCW @EOTCW መልክአ ሚካኤል ሰላም ለአጽፋረ እግርከ ፍናዋተ ረድኤት በተኃልፎ፤ ዘኢተዳደቆን እብነ አዕቅፎ፤ ሚካኤል ቀዳሲ ትሥልስተ አካላት በኢያዕርፎ፤ ኢትኅድገኒ በዓለም እስመ ኪያከ እሴፎ፤ አልቦ ብእሲ ዘየኀድግ ሱታፎ። @EOTCW @EOTCW ዚቅ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር፤ ዘበተዋሕዶ ይሤለስ፤ እምኀበ ትጉሃን ይትቄደስ፤ እሳተ ሕይወት ዘኢይትገሠሥ፤ ወዘኢይጤየቅ ለዓይን ረቂቅ መንፈስ፤ ንሰግድ ለትሥልስቱ አሐተ ስግደተ፤ ወሎቱ ናቄርብ ስብሐታተ። @EOTCW ማኅሌተ ጽጌ ተፈሥሒ ማርያም እንተ ኢተአምሪ ብእሴ፤ ዘጸገይኪ ለነ አሐደ እምነ ሥላሴ፤ እንዘ ትዘብጥ ከበሮ ቅድመ አዕላፈ ኤፍሬም ወምናሴ፤ ለተአምርኪ ትነግር ውዳሴ፤ ማርያም እኅቱ ለሙሴ። @EOTCW ዚቅ በፈቃደ አቡሁ ወረደ ኀበ ማርያም ተአንገደ፤ በድንግልናሃ ንጹሕ እግዚአብሔር ተወልደ። @EOTCW @EOTCW ወረብ፦ በፈቃደ አቡሁ ወረደ ተአንገደ በደብረ ብርሀን ፤ በድንግልናሃ ንጹሕ በድንግልናሃ ንጹሕ እግዚአብሔር ተወልደ። @EOTCW @EOTCW መልክአ ሥላሴ ሰላም ለህላዌክሙ ዘይመውዕ ህላውያተ፤ ለረኪበ ስሙ ኅቡዕ አመ ወጠንኩ ተምኔተ፤ እምግብርክሙ ሥላሴ ሶበ ረከብኩ አስማተ፤ መለኮተ ለለአሐዱ ዘዚአክሙ ገጻተ፤ እንበለ ትድምርት እሰሚ ወእሁብ ትድምርተ። @EOTCW @EOTCW ዚቅ ነአምን በአብ ወነአምን በወልድ፤ ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ፤ ነአምን ዘንተ ሥላሴ ፩ ውእቱ አምላክ ፍጹም፤ ዘእምኔሁ ለአብ ወልድ ተወልደ፤ በአምሳለ ዚአሁ፤ ኅቡር ኅላዌሁ፤ ነአምን ንሕነ ነአምን። @EOTCW ወረብ ነአምን በአብ ወነአምን በወልድ ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ/፪/ ፩ ውእቱ አምላክ ፍጹም ፩ ውእቱ/፪/ @EOTCW መልክአ ሥላሴ ሰላም ለአጻብኢክሙ እለ እምአጽፋር ኢይትሌለዩ፤ ለቤትክሙ ሥላሴ ዘኢየኃልቅ ንዋዩ፤ አመ አብዓልክሙ ሰብአ ድኅረ አንደዩ ጌጋዩ፤ ዘኢርእዩ እምቅድመ ዮም መላእክተ ሰማይ ርእዩ፤ ወአግብርተ ሰብእ መላእክት ተሰምዩ። @EOTCW @EOTCW ዚቅ ርእይዎ ኖሎት አእኮትዎ መላእክት፤ ለዘተወልደ እማርያም እምቅድስት ድንግል፤ ዮም ሰማያዊ በጎል ሰከበ። @EOTCW @EOTCW ወረብ ርእይዎ 'ኖሎት'/፪/ ርእይዎ አእኮትዎ/፪/ ለዘተወልደ እማርያም እምቅድስት ድንግል/፪/ @EOTCW መልክአ ሥላሴ ለዘበነጊድ አቅረብኩ መካልየ ልሳን ስብሐታተ፤ መጠነ ራብዕ ዐሥር እንዘ አተሉ ሰብዓተ፤ ህየንተ አሐዱ ሥላሴ እለ ትፈድዩ ምዕተ፤ ጸግዉኒ እምገጽክሙ ንዋየ ገጽ ትፍሥሕተ፤ ወዲበ ዐሠርቱ አህጉር ሀቡኒ ሢመተ። @EOTCW @EOTCW ወረብ ጸግዉኒ አጋዕዝትየ እምገጽክሙ ንዋየ ገጽ/፪/ ወዲበ ዐሠርቱ አህጉር ሀቡኒ ሢመተ/፪/ @EOTCW ዚቅ ስብሐት ለከ ስብሐት ለዘወለደከ፤ ስብሐት ለዘሠረፀ እምአቡከ፤ ዘዕሩይ ምስሌሁ ወምስሌከ፤ በከዊነ ዘሀሎ ወይሄሉ፤ ለዓለመ ዓለም። @EOTCW ወረብ ስብሐት ለከ ስብሐት ለዘወለደከ ስብሐት ለዘሠረፀ እምአቡከ/፪/ ዘሀሎ ወይሄሉ ዘዕሩይ ምስሌሁ/፪/ @EOTCW @EOTCW አንገርጋሪ ኲሉ ይሰግድ ለሥላሴ፤ ወይትቀነይ ኲሉ ለመንግሥተ ሥላሴ፤ እስመ ኮነ ዘይነብር ዲበ ኪሩቤል፤ ወበዓይኑ ይኔጽር ቀላያተ። @EOTCW @EOTCW አመላለስ እስመ ኮነ ዘይነብር ዲበ ኪሩቤል እስመ ኮነ/፪/ ወበዓይኑ 'ይኔጽር'/፪/ ቀላያተ/፪/ @EOTCW @EOTCW ወረብ ኲሉ ይሰግድ 'ለሥላሴ'/፪/ ኲሉ ይሰግድ/፪/ ወይትቀነይ ኲሉ ለመንግሥተ 'ሥላሴ'/፪/ ኲሉ ይሰግድ/፪/ @EOTCW @EOTCW እስመ ለዓለም ዘሰንበት፦ ዘዲበ ኪሩቤል ይነብር ወበአርያም ይሴባሕ፤እምሰማያት እምልዑላን ወረደ፤አምላክ ያድኅን ዓለመ መጽአ ይክሥት ብርሐነ ይቤዙ ዓለመ፤ ወልድ ተወልደ ለነ፤ ሠርዓ ሰንበት ለሰብአ ዕረፍት ፤ወልድ ዋህድ ውእቱ 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 መዝሙር 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 (በ፪/ሩ) ንጉሥኪ ጽዮን ለትውልደ ትውልድ መጽአ ኀቤነ ዘኪያሁ ይሴፈዉ ሰማያት ወምድር ዕበይ ለነገሥት ብርሃኖሙ ለእለ ይጸመድዎ አክሊለ ሰማዕት ሠያሜ ካህናት ዓምዳ ወድዳ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን በቤተ ልሔም ተወልደ ወበናዝሬት ተሐፅነ ኢተዘኪሮ አበሳነ ኢኀደገነ ፍሥሐ ኮነ ዘውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ። ምልጣን፦ ኢተዘኪሮ አበሳነ ኢኀደገነ ዘውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ። ለነገሥት ብርሃኖሙ ለእለ ይጸመድዎ አክሊለ ሰማዕት ሠያሜ ካህናት ዓምዳ ወድዳ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን በቤተ ልሔም ተወልደ ወበናዝሬት ተሐፅነ ኢተዘኪሮ አበሳነ ኢኀደገነ ፍሥሐ ኮነ ዘውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘውእቱ ኢየሱስ https://t.me/Eotcw #Join & share

ያሬዳውያን: 🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵 ሥርዓተ ዋዜማ ዘሥላሴ 'ጥር ፮' 💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠 ዋዜማ ሃሌ ሉያ ፈቂዶ ይርዳዕ ወይቤዙ ወልደ አብ ውስተ ማኅፀነ ድንግል ኀደረ፤ ተኀቢዖ ለኲሉ ኃይል፤ ለእለ በሰማይ ማኅደሮሙ በኢያእምሮ ሠወሮሙ፤ መጽአ ኀቤነ ወለብሰ ሥጋነ፤ ዘምስለ ኖኅ ተካየዳ፤ ወምስለ አብርሃም ተዓረከ ወምስለ ያዕቆብ ነገደ፤ መጽአ ኀቤነ ወለብሰ ሥጋነ፤ ምስለ ሙሴ ተናገረ ወምስለ ዳዊት ዘመረ፤ ዕንባቆም ነቢይ ዘአንከረ ግብሮ፤ መጽአ ኀቤነ ወለብሰ ሥጋነ፤ ስምዖን ተወክፎ ወዮሐንስ አንጸሮ፤ ሐዋርያት ተለዉ አሠሮ፤ መጽአ ኀቤነ ወለብሰ ሥጋነ፤ ኢኃሠሠ አበ በዲበ ምድር፤ ወኢ አመ በሰማያት፤ አሀዱ ውእቱ እግዚአብሔር፤ አብ ወወልድ፤ ወመንፈስ ቅዱስ። @EOTCW @EOTCW አመላለስ፦ አሀዱ ውእቱ እግዚአብሔር፤ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ። @EOTCW ወቦ ዘይቤ ይቤሎ አብ ለወልዱ፤ ነዓ ረድ እምሰማይ ዲበ ምድር፤ ከመ ትኩን በኲረ በላዕለ ብዙኃን፤ ዜናዊ ሰማያዊ፤ እምዘርዓ ዳዊት ዘመጽአ። @EOTCW አመላለስ፦ ዜናዊ ሰማያዊ እምዘርዓ ዳዊት ዘመጽአ፤ ዜናዊ ሰማያዊ እምዘርዓ ዳዊት ዘመጽአ። @EOTCW በ፭ ለእግዚአብሔር ምድር በምልዓ፦ @EOTCW ተወልደ በተድላ መለኮት፤ ብሑተ ልደት እማርያም እምቅድስት ድንግል፤ ተወልደ በተድላ መለኮት። @EOTCW እግዚአብሔር ነግሠ፦ @EOTCW ተወልደ መድኅን ክብረ ቅዱሳን፤ እማርያም ድንግል፤ አስከበቶ እሙ ውስተ ጎለ ዕብን፤ ወትቤ መድኅኑ ለዓለም። @EOTCW ይትባረክ፦ ጸሎተ ፫ቱ ደቂቅ: ፱ ይቤሎ እግዚእ ለእግዚእየ፤ ንበር በየማንየ፤ አንተ ውእቱ ወልድየ፤ ዘአፈቅር ዘሠምረት ነፍስየ። @EOTCW @EOTCW ሰላም፦ ይእዜኒ ንትልዋ ለሰላም፤ እስመ ተወልደ ክርስቶስ ዮም በሀገረ ዳዊት፤ አናህስዮ አበሳነ ወልዱ ለአብ፤ ቀዳሜ በኲሩ ኃይሉ ለአብ፤ መጽአ ኀቤነ ይክሥት ብርሃነ፤ ተመሲሎ ኪያነ፤ ሰብእ ዘይከውን ኲሎ ኮነ፤ ዘእንበለ ኃጢአት ባሕቲታ። @EOTCW @EOTCW አመላለስ፦ መጽአ ኀቤነ ይክሥት ብርሃነ፤[፪] ተመሲሎ ኪያነ ሰብእ ዘይከውን ኲሎ ኮነ ዘእንበለ ኃጢአት ባሕቲታ።[፬] https://t.me/Eotcw #Join & share

20/3/2015 ዓ.ም 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በእለቱ የቅዳሴ የሚባል ምስባክ መዝ ፹፫፥፮ እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ፤ ወየሐውር እምኃይል ውስተ ኃይል፤ ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን። #ትርጕም፦ የሕግ መምህር በረከትን ይሰጣልና፤ ከኃይል ወደኃይል ይሄዳል፤ የአማልክት አምላክ በጽዮን ይታያል። https://t.me/Eotcw

photo content
+1

❤ ከዚህም በኋላ ሊቀ ጳጳሳት አባ ገብርኤል ሲያርፍ ኤጲስቆጶሳቱ በራእይ ተረድተው አባ ማቴዎስን ያለ ፈቃዱ በግድ ሊሾሙት ተስማሙ፡፡ እምቢ ባላቸውም ጊዜ በላዩ ላይ ጠባቂዎችን አኖሩ፡፡ አባ ማቴዎስም እንደማይተውት ዐውቆ ምላሱን ጎትቶ በማውጣት ምላጭ ቆረጣት፡፡ በዚያችም ሌሊት እመቤታችን ወደ እርሱ መጥታ ተገለጠችለትና የሚያድን ቅባትን ቀብታ ምላሱን እንደቀድሞው አድርጋ ፈወሰችለት፡፡ ኤጲስቆጶሳቱም በግዴት ወደ እስክንድርያ ወሰዱትና በእመቤታችን ዓመታዊ በዓሏ ቀን በቅዱስ ማርቆስ መንበር 87ኛ ሊቀጳጳሳት አድርገው ሾሙት፡፡ በዚህም ጊዜ "ይገባዋል ይገባዋል" የሚል ድምጽ ከሰማይ ተሰማ፡፡ በክንዱም ላይ ያደርጉ ዘንድ የወንጌላዊ የቅዱስ ማርቆስን ራስ አመጡ፡፡ እርሷም ተነጥቃ ወደላይ በረረችና የአባ ማቴዎስን አፉን ሳመችው፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ አባ ማቴዎስ ዐርብና ረቡዕ በዓቱን ዘግቶ ሲጸልይ የሚውል ስለሆነ ማንም ወደ እርሱ አይገባም ነበር፡፡ ከራሱ ላይ በሚያደርገው ቀጸላ ብዙ ሕሙማንን ፈወሰበት፡፡ ሙታንንም በማስነሣት ብዙ ድንቅ ተአምራትን አደረገበት፡፡ በወቅቱም በእኛ አገር በኢትዮጵያ ውድም አስፈሬ ነግሦ ሳለ ይህ አባ ማቴዎስ ንጉሥ ዳዊት እንደሚነግሥ ትንቢትን ተናገረ፡፡ እንደትንቢቱም በኋላ ላይ ደገኛው ዐፄ ዳዊት ነግሠዋል፡፡ ❤ በአባ ማቴዎስ ዘመንም በምስር አገር ክፉ ገዥ ተሾመና አባ ማቴዎስን ከአቅሙ በላይ ግብርን ጠየቀው፡፡ የተጠየቀውንም ብዙ ግብር መክፈል እምቢ ባለ ጊዜ ገዥው አባ ማቴዎስን በጽኑ ድብደባ አሠቃየው፡፡ ተሸክመውት ወደ ቤተ ክርስያን ባደረሱት ጊዜ በእመቤታችን ሥዕል ፊት ወድቆ "ምነው እመቤቴ ሆይ ነፍሴን ወስደሻት ከዚህ ክፉ ዓለም ብታሳርፊኝ" ብሎ ተማጸናት፡፡ ክብርት እመቤታችንም ተገለጠችለትና "አይዞህ አትዘን፣ በ8ኛው ቀን በሰላም ታርፋለህ" አለችው፡፡ ወዲያውም ኤጲስቆጶሳቱን፣ ዲያቆናቱንና ምእመኑን ሁሉ ጠርቶ የዕረፍቱን ጊዜ ነገራቸውና እስከ መጨረሻው ድረስ በሃይማኖት እንዲጸኑ መከራቸው፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ ጊዜው ደርሶ ሕማሙ በጸናበት ጊዜ የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ሥዕል አንሥቶ ይዞ ለረጂም ጊዜ ጸለየ ሥዕሊቱም ተሳልሞ ሳማት ፊቱንም በመስቀል ምልክት አማተበ ክርስቶስን የሚያምኑ ምእመናን ያሉበትን አገር ሁሉ ባረከ በእሑድ ጥር5 ቀንም በሰላም ዐረፈ፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ማቴዎስ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ የጥር5 ስንክሳር። + + + ❤ "ሰላም ለአውስግንዮስ ለምሥጢረ መስቀል ዘተርጐሞ። አመ ቈስጠንጢኖስ ርእየ ማዕተበ ከዋክብት ቀዊሞ። እንበለ ያጽዕቆ ልሕቅና ወእንበለ ርሥአን ያድክሞ። ምእተ ወዐሠርተ ዓመተ መዋዕለ ሕይወቱ ፈጽሞ። በእንተ ክርስቶስ ተመትረ ወከዐወ፡ደሞ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የጥር 5። + + + ❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ወተወከልኩከ እንዘ ሀሎኩ ውስተ አጥባተ እምየ። ላዕሌከ ተገደፍኩ እማኅፀን። እምከርሠ እምየ አንተ አምላኪየ"። መዝ 21፥9-10። የሚነበው ወንጌል ዮሐ 11፥25-ፍ.ም ወይም ማቴ 7፥7-13። + + + ❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ። ወየሐውር እምኃይል ውስተ ኃይል። ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን"። መዝ 83፥6-7 ወይም 36፥30-31። የሚነበቡት መልዕክታ ዕብ 2፥11-ፍ.ም፣ ያዕ 3፥5-13 እና የሐዋ ሥራ 7፥55-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 18፥33-38 ወይም ማቴ 5፥1-13። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ጎርጎርዮስ ካልዕ ቅዳሴ ነው። መልካም የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የልደት በዓል ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፭ (5) ቀን። ❤ እንኳን በከሀዲው ዑልያኖስ ዘመነ መንግስት ሰማዕትነት ለተቀበለ ለከበረ ለቅዱስ አውስግንዮስ ለዕረፍቱ በዓልና ለእስክድርያ ሰማንያ ሰባተኛ ሊቀ ጳጳስ ለአባ ማቴዎስ ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ ከያሬውንዮስ ከሌሎችም ከሴቶችና ወንዶች ከሮማዊው ለንጊኖስ፣ ከአባ አርሳኒን ከጐበኘችው ከእስክንድርያና ከአውስያ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ ሰማዕቱ ቅዱስ አውስግንዮስ፦ ይህም ከንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ጭፍሮች ውስጥ ነው እርሱም እግዚአብሔርን የሚያመልከው ለድኆችና ለምስኪኖች የሚመጸውት ነው መስቀልም እንደ ክዋክብት በሰማይ እያበራ ለንጉሥ ቈስጠንጢኖስ በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከማመኑ በፊት በተገለጠለት ጊዜ ይህ ቅዱስ አውስግንዮስ ወደ ንጉሡ ቀርቦ እንዲህ አለው "ይህ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ምልክቱ ነው በዚህም ጠላቶችህን ታሸንፋለህ። ያን ጊዜ ከቈስጠንጢኖስ ሥራዊት ውስጥ ከዚህ ቅዱስ ሰው በቀር የክርስቶስን ስም ይጠራ ዘንድ የደፈረ የለም። ❤ ቈስጠንጢኖስም በከበረ መስቀል ምልክት ጠላቶቹን ድል በአደረገ ጊዜ ዕውነተኛ ክርስቲያን ሆነ የሃይማኖትንም ሥልጣን አቁሞ ከፍ ከፍ አደረገ። ይህም ቅዱስ አውሰሰግንዮስ እድሜው መቶ ዐሥር ዓመት እስከ ሆነው ከቈስጠንጢኖስና ከልጆቹ ዘመነ መንግሥት በኋላ እስከ ከሀዲው ዑልያኖስ ዘመን ኖረ። በአንዲት ዕለትም በአንጾኪያ ከተማ በአደባባይ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ሲመላለስ ሁለት ሰዎች እርስ በርሳቸው ሲጣሉ አግኝቷቸው ሊአስታረሰቃቸው በመካከላቸው ሰላም ሊያደርግ ወዶ አስታረቃቸው በመታረቃቸውም ደስታ አደረጉ እርሱ የከበረ አረጋዊ ሰው ነውና። ❤ ከዚያም አንድ ክፉ ሰው ወደ ንጉሥ ዑልያኖስ ሒዶ ነገር ሠራበት እንዲህም አለው "አውስግንዮስ በራሱ ፈቃድ ገዥና ፈራጅ ዳኛ ሆነ"። ንጉሥም ይህን ቅዱስ ወደርሱ አቅርቦ ገሠጸው "ገዥና ፈራጅ ዳኛ አድርጎ የሾመህ ማነው" አለው። የከበረ አውስግንዮስ መልሶ "ነፍስህ በእጁ የተያዘች የእግዚአብሔርን አምልኮት ትተህ አንተ ለረከሱ ጣዖታት ለምን ሰገድክ ከአንተ በፊት የነበሩ ነገሥታትን ለምን አልተከተልካቸውም እኔም እንዳንተ ወታደር ሁኜ ከቈስጠንጢኖስ ጋር ሃያ ዓመት ኖርኩ ከልጆቹም ጋር ነበርኩ እነርሱ ውስጥ እንዳንተ ያለ ጠባየ ክፉ የለም" አለው። ❤ ዑልያኖስ በቅዱስ አውስግንዮስ ላይ እጅግ ተቆጣ ይሰቅሉት ዘንድ በጐኖቹም ውስጥ መብራቶችን አስገብተው እንዲለበልቡት አዘዘ እነርሱም ስለ ክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይህን ሁሉ ታገሠ። ማሠቃየትም በሰለቸው ጊዜ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡት ዘንድ አዘዘ ወታደሮችም ሊቆርጡት በመጡ ጊዜ እስኪጸልይ ይታገሡት ዘንድ ለመናቸው ጸሎቱንም ሲፈጽም የከበረች ራሱን ቆረጡት ጥር5 ቀን የምስክርነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማይያት ተቀበለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ አውስግንዮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ አባ ማቴዎስ፡- የዚህም የአባ ማቴዎስ ወላጆቹ ከእስራኤል ነገድ የሆኑ ክርስቶስ የሚያምኑ በበጎ ሥራዎችም ፍጹማን የሆኑ ናቸው። የአባቱም ስም ስምዖን የእናቱም በርባራ ይባላል እግዚአብሔርም ሁለት ዘርን ሰጣቸው የታላቁም ስም ያዕቆብ የታናሹም ስም ማቴዎስ ነው፡፡ ይህም ቅዱስ ማቴዎስ ገና በእናቱ ሆድ ውስጥ ሳለ የአቡፌስ አገር ኤጲስቆጶስ የከበረ አባ ጴጥሮስ እናቱን ባገኛት ጊዜ ከበቅሎው ላይ ወርዶ በክብር ሆዷን ሳማትና "አንቺ ሴት የተባረክሽ ነሽ፣ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው፡፡ እነሆ እንደ ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ በትምህርቱ ለሰው ሁሉ የሚያበራ ብሩህ ኮከብ ካንቺ ይወጣል" አላት፡፡ አባ ማቴዎስም ተወለደ፡፡ በ15 ዓመቱ ወላጆቹ ከሞቱ በኋላ ወደ ገዳም ገብቶ ሊመነኩስ ወሰነ፡፡ በቅዱስ አቡፋና ገዳም ገብቶ አባ አብርሃምን "አመንኵሰኝ" ቢለው "ከታላቅ ወንድምህ ተማከረህ ና" አሉት፡፡ ወደቤቱም ተመልሶ ሲሄድ በመንገድ ላይ ሳለ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ተገለጠለትና ሊቀ ጳጳሳት እንደሚሆንና በእጆቹም ብዙ ተአምራትን እንደሚያደርግ ነገረው፡፡ ቅዱስ ማቴዎስም ከታላቅ ወንድሙ ጋር ስለምንኵስና ተማክሮ ተመልሶ በቅዱስ አቡፋና ገዳም መነኮሰና በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመረ፡፡ ❤ ቅዱስ ማቴዎስ አንድ ዓመት በሆነው ጊዜ ኤጲስቆጶሱ አባ ጴጥሮስ ወደ አባ አብርሃም መጣና የቅዱስ ማቴዎስን ረዳት አድርጎ ይሰጠው ዘንድ ለመነው፡፡ እርሱም ፈቀደለትና ወሰደው፡፡ ቅዱስ ማቴዎስም ፀሐይ ስትገባ ጀምሮ እስክትወጣ ድረስ ለኤጲስቆጶሱ ጋር በጸሎት እየተጋ ያድራል፡፡ 15 ዓመትም በሆነው ጊዜ ሳይወድ በግድ ቅስና ሾመው፡፡ በዚህም ጊዜ ሰይጣን በቅናት ተነሳበትና በዝሙት ፈተነው፡፡ ሰይጣንም በአንዲት ባማረች ሴት ልብ አድሮ ብዙ ፈተነው፡፡ ነገር ግን ቅዱስ ማቴዎስ እያለወሰ ወደ እግዚአብሔር ይለምን ነበር፡፡ ኤጲስቆጶሱንም ወደ ገዳሙ መልሶ ይልከው ዘንድ ለመነው፡፡ እርሱም ማሰናበትን እምቢ አለው፡፡ ቅዱስ ማቴዎስም በዚህ ተናዶ የኤጲስቆጶሱን መቀደሻ ልብሶች በምላጭ ይቀድ ጀመር ይህም ኤጲስ ቆጶሱ እንዲበሳጭና እንዲልከው ነው፡፡ ነገር ግን መቶ መቶ እንዲሠግድ ቀኖና ሰጠው እንጂ አላሰናበተውም፡፡ በኋላም ትዕግስቱንና ቅንነቱን አይቶ ፍትሃትና ቡራኬ ሰጠው፡፡ ❤ ከዚህም በኋላም ወንድኑ ወደ ገዳም መጥቶ በመመንኰስ ሰይጣንን ድል እስከያደርገው ድረስ ተጋደለ፡፡ አባ ማቴዎስም ወደ አባ እንጦንስ ገዳም ሄዶ በታላቅ ተጋድሎ ብዙ ዘመን ኖረ፡፡ በገዳሙ ያሉ አባቶችም ቅዱሳን መላእክት ለአባ ማቴዎስ ሲገለጡለትና ሲያከብሩት በራእይ ስላዩ አባ ማቴዎስ ውዳሴ ከንቱን በመጥላት ከአንዱ ገዳም ወደ አንዱ ገዳም የሚዘዋወር ሆነ፡፡ በአንዲት ዕለትም በቅዳሴ ላይ ሲያገለግል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በታናሽ ሕፃን አምሳል በመሠዊያው ላይ ተቀምጦ አየው፡፡ ይህንንም ባየ ጊዜ ከታላቅ ለቅሶ ጋር አገልግሎቱን ፈጸመ እንጂ ለማንም አልተናገረም፡፡ አበ ምኔቱም አባ ማቴዎስን ለረጅም ሰዓት ቆሞ ባየው ጊዜ አንዳች ምሥጢር እንዳቆመው ዐውቆ ይህንን ይገልጥለት ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ለመነ፡፡ በአንዲት ዕለትም አባ ማቴዎስ እንደልማዱ ይቀድስ ዘንድ ገባ፡፡ ጌታችንም በሕፃን አምሳል በጻሕሉ ውስጥ ተኝቶ ኅብስትንም መስሎ በአባ ማቴዎስ እጅ ሲቆረስ ለአበ ምኔቱ ታየው፡፡ እርሱም ይህን በማየቱ እጅግ አደነቀ፡፡ "ለእኛ ለሰው ልጆች ይህን ጸጋ ለሰጠኸን አቤቱ ለአንተ ምስጋና ይገባሃል" አለ፡፡ ❤ አባ ማቴዎስም ይህን ባየጊዜ ታላቅ የብረት ችንካር አምጥቶ ተልቶ ከእርሱ ትል እስኪወጣ ድረስ ችንካሩን በጉልበቱ ውስጥ ቀረቀረው፡፡ ከዚህም በኋላ ወደ ደብረ ቁስቋም ገብቶ በዚያም እየተጋደለ ኖረ፡፡ ወደላይም ቀና ብሎ በተመለከተ ጊዜ የክብርን ባለቤት ጌታችንን በአባቱ ቀኝ ተቀምጦ አየው፡፡ ወደታችም ሲመለከት በውቅያኖስ ጥልቅ ውስጥ በጌትነቱ ክብር የሚያየው ሆነ፡፡ ነቢዩ ቅዱስ ዳዊት "ወደ ሰማይ ብወጣ አንተ በዚያ አለህ፣ ወደ ሲኦልም ብወርድ በዚያ አለህ" እንዳለ፡፡ መዝ 139፥8፡፡

photo content
+3

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፭ (5) ቀን። ❤ እንኳን ለታላቁ አባት ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ልደታቸው አስመልክቶ (ሳሪስ አቦ፣ፈረሳይ አቦ) የለውጥ ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል አደረሰን። + + + ❤ ስለ አባታች አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ልደት፦ ትውልድ አገራቸው ደቡባዊ ግብፅ ከቆላው ልዩ ስሙ ከንሒሳ አካባቢ ነው፡፡ አባታቸው ስም ቅዱስ ስምዖን እናታቸው ስም ቅድስት አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ ወላጆቻቸው በእግዚአብሔር ፊት ደጋጎች የነበሩ ቢሆኑም አቅሌስያ መካን ሆና ልጅ በማጣቷ እያለቀሰች 30 ዘመን ኖራለች፡፡ ❤ ከዕለታትም በአንደኛው ቀን ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብታ የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ሥዕል ካለበት ፊት ለፊት በመቆም እግዚአብሔር ልጅ ይሰጣት ዘንድ አልቅሳ ስትለምን ያንጊዜ ከሥዕሉ ቃል ወጥቶ "ክቡሩ ከሰማይ ከምድር ከፍ ከፍ የሚል፣ከሚካኤል ከገብርኤል ጋር በክብር የሚተካከል ክህነቱ እንደ መልከ ጼዴቅ ንጽሕናው እንደ እንደ ነቢይ ኤልያስ፣ እንደ መጥምቁ ዮሐንስ የሆነ በክብር ከነቢያትና ከሐዋርያት ጋር የሚተካከል ልጅ ትወልጃለሽ" አሏት። ይኸውም ለአንቺ ብቻ አይደለም ለዓለሙ ሁሉ ነው እንጂ። ያን ጊዜ ከሦስቱ አንዱ ተነሥቶ በእጁ ባርኮ በሰላም ወደ ቤትሽ ግቢ አሏት"። እርሷም ደስ እያላት ወደ ቤቷ ገባች፡፡ ❤ ቅድስት አቅሌስያም በመጋቢት 29 ቀን ፀንሳ በታኅሣሥ 29 ቀን ደም ግባቱ እጅግ የሚያምር ወንድ ልጅ እንደወለደች መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰው አምሳል መጥቶ "የዚህ ልጅሽ ስሙ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይሁን" አላት፡፡ ወዲያውም ሕፃኑ ተነሥቶ ከእናቱ ጭን ወርዶ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሦስት ጊዜ ሰገደ፡፡ ዳግመኛም "ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን" አለ፡፡ ምንጭ፦ ገድለ ገብረ መንፈስ ቅዱስ። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw