Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗
الذهاب إلى القناة على Telegram
Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service
إظهار المزيد3 590
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+37 أيام
+4830 أيام
أرشيف المشاركات
✅የአርማታ ሙሌታ (Concrete Compaction) ቁጥጥር
1. የግብአት ጥራትን (Materials Quality)፦ በአርማታ ሙሌት ሥራ ሂደት ውስጥ የሚጠቀማቸውን የማምረቻ ግብአቶች ጥራት በተገለጸው መስፈርት መሰረት የሚያሟሉ መሆኑን ማረጋገጥ አለበት።
ይህ ማለት የቀረበው ሲሚንቶ (Cement) አይነትና የምርጥ ጥራት፣ የአሸዋ (sand or Fine aggregate) እና ጠጠር (Coarse Aggregate)ሳይንሳዊ ምዘናን ማሟላቱን፣ የማቅጠኛ ውሀ (Water) የኮንክሬት ስትራክቸሩን ሊጎዳ የሚችል ኬሚካልና ቆሻሻ የሌለው የጠራ ውሃ መሆኑን እና ሌሎች ተጨማሪ ኬሚካል (Admixture) መለያ አይነት የተሟላ መሆኑን ሳይንሳዊ ማስረጃ ላይ ተደግፎ የማረጋገጥ ሂደትን መተግበር ማለት ነው።
በዚህ ረገድ የግብአት መሐንዲሱ (Materials Engineer) ለሳይቱ በቀረበው የቤተሙከራ ክፍል ውስጥ በመስራት የማረጋገጥ አልያም በቅርቡ በሚገኝ የቤተሙከራ አገልግሎት ሰጪ ተቋማ በማሰራት የግብአቶችን ጸባይ የመለየትና ማረጋገጫ የመስጠት ግዴታ ይኖርበታል።
2. የግብአቶችን ልኬት (Batching of materials):- በተለይ በሀገራችን የግንባታ ልምድ ኮንክሬት በሚመረትበት ሰዓት ያለው የአሸዋ፣ የጠጠር እና የውሃ ልኬት ለችግር የተጋለጠ ነው።
አንድ 1፡2፡3 ምጥጥንን መሰረት አድርጎ ዲዛይን የተሰራ አርማታ አንድ እጅ ሲሚንቶ፣ ሁለት እጅ አሸዋ፣ ሦስት እጅ ጠጠር መጠቀም አለበት ማለት ቢሆንም የመቀላቀያ ማሽኑ ተቆጣጣሪ (Mixer Operator) ይህንን ምጥጥን ጠብቆ አምራታ የማምረት ልምድ ቸልተኝነት የተሞላበት እንደሆነ ይስተዋላል።
ተቆጣጣሪ መሐንዲስ በምጥጥን (Proportion) መሰረት እየተመረት መሆኑን መቆጣጠር የግድ ነው።
3. የማሽን እና መሳሪያ ደህንነት (Equipments Security):- የኮንክሬት ድብልቅ ማምረቻ ማሽኖች (mixers) ደህንነታቸው የተረጋገጠ ወይም በአግባቡ የሚሰሩ መሆናቸውን ማረጋገጥ፣ የኮንክሬት ግብአቶችን መለኪያ ሳጥኖችን (box) ርዝመት ወርድ እና ቀመት (L, W, H) አግባብነት ያለው መሆኑን (ለምሳሌ፦ 18*40*50)፣ የሰው ህይወት እንዳይጠፋ ብሎም የካሳ ሙግትና የሥራ ማቆም መሰናክል እንዳይፈጠር የሰራተኞች ደህንነት መጠበቂያ አልባሳት የተሟሉ መሆኑን ማረጋገጥ አለበት።
4. በአግባቡ መጠቅጠቁን፦ የሚሞላው አርማታ በተለይ ምሰሶ (column) እና የምሰሶ ጫማ (Footing Pad) በክፍልፋይ ላየሮች ከፋፍሎ እያንዳንዱ የላየር ክፍል ጫፍ ላይ ሲደርስ በኤሌክትሪክ መንዘሪያ (Vibrator) በደንብ መጠቅጠቅ መቻል አለበት።
የአርማታ መጠቅጠቅ እያንዳንዱ የግንባታ ግብአት በአግባቡ የተሰራጨ እንዲሆን እና የቀጠነው አርማታ ወደታች ወርዶ ጠጠራማው ወደላይ እንዳይቀር በማድረግ የትኛውም የስትራክቸር ክፍል ተመሳሳይ አይነት ጥንካሬ እንዲኖረው ያደርጋል።
5. የአርማታ ድርቀት እንዳይኖር መቆጣጠር፦ የአርማታ ሙሌት ሂደት ላይ አዲስ የተመረተ አርማታ አላስፈላጊ ደቂቃዎችን ሳይሞላ መቆየት የለበትም።
አርማታ ሳይሞላ ከሚክሰር እንደተገለበጠ የሚቆይ ከሆነ በፎርምወርክ ውስጥ ሆኖ መያዝ ያለበትን የመጀመሪያ ጥንካሬ (Initial Setting) መያዝ ስለሚጀምር ከዚያ በኋላ ሙሌትን ለማከናወን አዳጋች ከመሆኑም በላይ የሚፈለገውን የኮንክሬት ስትራክቸር ጥንካሬ ለማግኘት አዳጋች ይሆናል።
https://t.me/ethioengineers1
+1
የኮንስትራክሽን ሬጉላቶሪ ኢንፎርሜሽን ሲስተም /CRIS/ ማስጀመሪያ መረሀ ግብር ዛሬ መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም
ሚንስትሮች፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የዲጅታል ሬጉላቶሪ ሲስተም ትግበራ ይፋዊ ማስጀመሪያ መርሀ ግብር
በሳይንስ ሙዚየም የመሰብሰቢያ አዳራሽ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
https://t.me/ethioconradio
UPVC ከአልሙኒየም ይልቅ ተመራጭ የሚያደርገው ውበቱ ብቻ ሳይሆን፣ ለረጅም ጊዜ ሳይዝግ፣ ቀለሙ ሳይለቅ፣ ሳያረጅ መቆየቱ እና በዋጋ ተመጣጣኝ መሆኑም ጭምር ነው!
የUPVC ማቴሪያሎችን በመጠቀም በተለያዩ ዲዛይኖች በሮች፣ መስኮቶችና ፓርቲሽኖችን በተመጣጣኝ ዋጋ አምርተን በራሳችን ባለሙያዎች ያሉበት ቦታ ድረስ መጥተን እንገጥማለን!
📍 Location: ጋዜቦ አደባባይ፣ ሙልሙል ዳቦ ቤት አጠገብ
📞 Call us: 0930099146,0930099145
The door is the face of a home; beauty begins there
በ40/60 የጋራ ሕንፃዎች ላይ የሚገኙ የንግድ ቤቶች ጨረታ እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ተራዘመ
➖▭‼️▭➖
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ ክ/ከተሞች ተገንብተው በተጠናቀቁ የ40/60 የጋራ ህንጻዎች ላይ የሚገኙ ንግድ ቤቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ በሽያጭ ለማስተላለፍ ከነሃሴ 16 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የጨረታ ሰነድ በመሸጥ ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡
በመሆኑም ከጨረታ ተሳታፊዎች ፍላጎት በመነሳት እና ለዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ መመለሻ በቂ ጊዜ ለመስጠት ሲባል የጨረታ ሰነድ መሸጫና መመለሻ ጊዜን ማራዘም አስፈላጊ መሆኑ በኮርፖሬሽኑ ስለታመነበት ከመስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአስር/10 ተከታታይ የሥራ ቀናት/ቅዳሜን ሙሉ ቀን ጨምሮ/የተራዘመ መሆኑን እየገለጽን፤ ጨረታው ጥቅምት 07 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ተዘግቶ በጨረታ መመሪያው በተገለጸው ቅደም ተከተል መሠረት ከጥቅምት 08 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የሚከፈት መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን
በ40/60 የጋራ ሕንፃዎች ላይ የሚገኙ የንግድ ቤቶች ጨረታ እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ተራዘመ
➖▭‼️▭➖
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ ክ/ከተሞች ተገንብተው በተጠናቀቁ የ40/60 የጋራ ህንጻዎች ላይ የሚገኙ ንግድ ቤቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ በሽያጭ ለማስተላለፍ ከነሃሴ 16 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የጨረታ ሰነድ በመሸጥ ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡
በመሆኑም ከጨረታ ተሳታፊዎች ፍላጎት በመነሳት እና ለዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ መመለሻ በቂ ጊዜ ለመስጠት ሲባል የጨረታ ሰነድ መሸጫና መመለሻ ጊዜን ማራዘም አስፈላጊ መሆኑ በኮርፖሬሽኑ ስለታመነበት ከመስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአስር/10 ተከታታይ የሥራ ቀናት/ቅዳሜን ሙሉ ቀን ጨምሮ/የተራዘመ መሆኑን እየገለጽን፤ ጨረታው ጥቅምት 07 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ተዘግቶ በጨረታ መመሪያው በተገለጸው ቅደም ተከተል መሠረት ከጥቅምት 08 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የሚከፈት መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን
FIDIC Contracts Reference BOOK.pdf1.94 MB
ድርጅታችን ሚትዮራይት ኮንስትራልሽን ሃ/የተ/የግ/ማህበር ከዚህ በታች በተገለጹት ክፍት የስራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል። ስለሆነም ከዚህ በታች የተገለጸውን መስፈርት የምታሟሉና መወዳደር የምትፈልጉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 7 (ሰባት) ተከታታይ የስራ ቀናት ዉስጥ አዳማ ከተማ በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት በአካል በመቅረብ እንዲሁም በድርጅቱ የኢሜል አድራሻ emnu203@gmail.com ወይንም ደግሞ በተጠቀሱት ቁጥሮች የቴሌግራም አድራሻ በመላክ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
👉ባለስልጣኑ የኮንስትራክሽን ዘርፉን ለማነቃቃት የሀገር ውስጥ ተቋራጮች ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑ አስታወቀ!
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን የኮንስትራክሽን ዘርፉን ለማነቃቃት የሀገር ውስጥ ተቋራጮች ላይ ትኩረት በማድረግ፤ ለግል ኮንስትራክሽን ማኅበራት ቅድሚያ ሰጥቶ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ለአሐዱ አስታውቋል።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር መስፍን ነገዎ (ዶ/ር)፣ "መንግሥት የሕግ ማዕቀፍ በማዘጋጀት ለሀገር ውስጥ ኮንስትራክሽን ማኅበራት ቅድሚያ ሰጥቷል" ሲሉ ለአሐዱ ተናግረዋል።
አንዳንድ የኮንስትራክሽን ተቋማት "መንግሥት ከሀገር ውስጥ ይልቅ ለውጭ ተቋራጮች ቅድሚያ እየሰጠ ነው" የሚል ቅሬታ እንዳላቸው ከአሐዱ ለተነሳላቸው ጥያቄ ዋና ዳይሬክተሩ ሲመልሱ፤ "መንግሥት የሚያሰራቸው ትልልቅ ፕሮጀክቶች የሀገር ውስጥ ተቋራጮች የመፈፀም አቅም በላይ ሲሆኑ ፕሮጀክቱ ለውጭ ኩባንያዎች ይሰጣል" ብለዋል።
አንዳንድ ሥራዎች ላይ የውጭ ኩባንያዎች መሳተፋቸው እና ቅድሚያ ማግኘታቸው አስፈላጊ የሚሆንበት ጊዜ እንዳለም አብራርተዋል።
ፕሮጀክቶች ለውጭ ተቋራጮች ሲሰጡ የኩባንያዎቹ የመፈጸም አቅም እና የመምራት ችሎታ ታይቶ እንደሆነም አጽንኦት ሰጥተውበታል።
አክለውም "መንግሥት የሕግ ማዕቀፍ እያዘጋጀ ቢሆንም በትልልቅ ፕሮጀክቶች ላይ የሀገር ውስጥ ተቋራጮች አቅም ውስንነት አለ። ይህንን ድክመት ከውጭ ከሚመጡ ኩባንያዎች የአሰራር ሂደት፣ የቴክኖሎጂ እና የአፈጻጸም ብቃት በምንወስደው ልምድ አቅማችንን ለማሳደግ ልንጠቀምበት ይገባል” ብለዋል።
የኮንስትራክሽን ዘርፉ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ትልቅ ድርሻ ያለው ቢሆንም፤ ዘርፉ በሚገባው ልክ እንዳያድግ እንቅፋት ከሆኑ ነገሮች መካከል የግሉ ዘርፍ አለመጠናከር፣ የግዢ ሥርዓት ፍትሐዊ አለመሆን፣ ግጭቶችና የበጀት ማነስ፣ ለችግሮች አፋጣን እና ግልጽ የመፍትሄ አለመስጠት በዋነኝነት ተጠቅሰዋል።
ጊዜያዊ የረዥም ጊዜ (የኮንትራት) ቅጥር ማስታወቂያ
በዚህ ሊንክ ገብተው ይመዝገቡ
https://forms.gle/oqbteUcWuRneaMGE6
🔵እንኳን ለኢሬቻ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! Baga ayyaana Irreechaan isingahe!Baga Ayyaana Irreecha Hora Finfinnee Baara 2018 tiin Isin Gahe!🤚 Ayyaana gaarri~ መልካም በዓል! ዩኒቲ-ኮንስትራክሽን ካታሎግ🏗
🔵እንኳን ለኢሬቻ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! Baga ayyaana Irreechaan isingahe!Baga Ayyaana Irreecha Hora Finfinnee Baara 2018 tiin Isin Gahe!🤚 Ayyaana gaarri~ መልካም በዓል! መልካም በዓል! ዩኒቲ-ኮንስትራክሽን ካታሎግ🏗
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
