ar
Feedback
❤❤የኪያ ደብዳቤዎች❤❤

❤❤የኪያ ደብዳቤዎች❤❤

الذهاب إلى القناة على Telegram
6 721
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+317 أيام
+12030 أيام
أرشيف المشاركات
በሲኒማ ታሪክ ውስጥ በጣም ሃያል ከሆኑ ንግግር አንደኛው የዚህን አለም እውነታ ያጠቃልላል። 🎬 The Godfather ዶን ቪቶ ኮርሊኒ ለልጁ ሚካኤል ኮርሊኒ እንዲህ ሲል ይመክረዋል፦ «እኔ ስሞት ካ
በሲኒማ ታሪክ ውስጥ በጣም ሃያል ከሆኑ ንግግር አንደኛው የዚህን አለም እውነታ ያጠቃልላል። 🎬 The Godfather ዶን ቪቶ ኮርሊኒ ለልጁ ሚካኤል ኮርሊኒ እንዲህ ሲል ይመክረዋል«እኔ ስሞት ካንተ ጋር የሰላም ውል ጠይቀው ስምምነት ላይ ይደርሳሉ። የምታምነውን አንድ ሰው ከእኛ ጉባኤ ወይም ከቤተሰብህ መካከል አንዱን መርጠው ወደአንተ ይልኩታል። የተላከው ሰውም ለሰላም ስምምነት እና ለአንተ የበለጠ ሹመት ልታገኝ እንደሆነ በመንገር ስብሰባው መች እንደሚከናወን የቀጠሮ ቀኑን ያሳውቅሃል። በዚህ ስብሰባ ወቅት ግን አንተ ትገደላለህ!። ለዛም ነው ይሄን የምልህ፤ ያ ለሰላም እና ለሹመት የሚልኩት ሰው ማንም ይሁን ማን አስወግደው ከሃዲ ነው!።»                   

"የድሮ ደብተሬን ስገለጥ፣ 'ፍቅር እያደር ወጣት ይሆናል እንጂ እንደ ሰው አያረጅም' የሚል ጽሁፍ አገኘሁ። የኔስ ፍቅር የት ደረሰ? እንደ እድሜ ጠገብ አዛውንት መቋሚያ ተደግፎ ይሆን ወይ? 'ገና አልሞትኩም' እያለ ለማትረፍ የሚታገል... አንዳንዴ በውስጥ ያለን ስሜት አለመናገር፣ ከልብ የማይጠፋ የዘወትር ጠባሳ ሆኖ ይቀራል። እናንተስ? የውስጣቹን ሳትናገሩ ግዜ የሸበለለባቹ ነገር አለ?" አኮብ(121)

ሬድዮ አዳምጬ ማቅባቸው ቀናቶች በጣት የሚቆጠሩ ትንሽ ናችው ዛሬ ግን መክፈት ፈለኩ መስማት ፈለኩ የሆነ ምስሉን የማላየው ድምጽ ፈለኩ እሱነቱን በለበሰው ጨርቅ ሳይሆን በንግግሩ መመዝን ፈለኩ አንዳንዴ ምናለ የዘመኑ social mediaዋች በድምጽ በሆኑ እላለሁ ብቻ ከፈትኩት አንድ ሰው በደስታ ተሞልቶ ዛሬ ታሪካዊ ቀን ነው ሲል ይደመጣል ታሪካዊ ቀን ማለት የማይረሳ በጥሩ ም በመጥፎም የሚታወስ አደል እንዲ ካልን ስንቱ በልቡ ከትቦ የያዘው ታሪካዊ ቀን አለው የማይረሳው. . . የማይዘክረው. . . የማይረግመው. . . ሊፍቀው ቢሞክር የማይፋቅ በልቡ የተነቀሰው ጥቁቁር የጠለሹ የህይወቱ ቅንጥብጣቢዋች ሆነው ለመንቀል ያዳገቱ ብቻ እግዜር መቶ ለሁሉም ብእር ወርቀት የታሪካዊ ቀናቹን ገጠመኝ አስፍሩ ቢል ወረቀቱ ይበቃቸዋል? እንጃ የኔዋ ታሪካዊ ቀን ግን ታሪከ ብዙ ናት ቢጨልፏት የማታልቅ ውቅያኖስ የናተስ? ስንት ታሪካዊ ቀን . . . አላቹ ? አኮብ(121)

አሁንኮ ድንገት ትዝ ብለኸኝ…እንዲሁ በኑሮ በኑሮ መሀል አንዳንዴ አስብሀለሁ።ትዝታ ግን አይገርምህም? . ትዝታ ጎበዝ የሒሳብ ሊቅ ነው። ይሔ ሲደመር ይሔ ..ሲደመር ይሔ…ነው እዚህ ያደረሳችሁ ይለኛል። እሺ እላለሁ። ይሔ ሲቀነስ ይሔ…ሲቀነስ ይሔ ነው…ልብሽን ባዶ ያደረገው ይለኛል። እሺ እላለሁ። ይሔ ሲባዛ ይሔ …ሲደመር ይሔ ..እኩል ይሆናል ይሔ መለያት ይለኛል። እሺ ነው መቼስ ለትዝታ ምን ይመልሱለታል? . ትዝታ የአለም አንደኛ ዲፕሎማትም ነው። ይሔ ሆኗል ይሔም ተደርጓል ቢሆንም ፍቅርን የሚያህል የታል? ይላል። ያኔ ልብም አዕምሮም ለዘብ ረገብ ይሉለታል። የተኩስ አቁም ስምምነት ይፈርሙለታል። እንዲያ እያሞኘ ድል ይረታል። እንጂ እኔ አሁን አንተን ላስብ ይገባል? በፍፁም! . ትዝታ እግዜር የጎበዝ ዕድሜ በደላችንን ያይደል የልጅነት የወተት ጥርሳችን እያሰበ ይቅር እንደሚለን ለማስታወስ በልብ ያስቀመጠው ህቡዕ ቋንቋም ይመስለኛል። ለዛ ነው መሰል ሰው ነፍሱ ስጋውን ስትሰናበት ለሰከንድ በህይወት ሳለ የሰራው ዋና ዋና ነገር summary ይቀርብለታል አሉ። ችግሩ ያኔ ‘take me back to the night we met’ን እየዘፈኑ መመለስ የለም። . ስለዚህ ዛሬ አስብሀለሁ። ስለማስብህም ብዙ አይደብረኝም። ወደተዋወቅንበት ፀደይ ዘመን እየሔድኩ ደግ ደግህን እደግማለሁ። አንተ ግን በቃ እረሳኸኝ እንደዛ የሰው limited edition ነሽ እንዳላልከኝ። እንግዲህ ምን አደርጋለሁ ከቴዲ ታደሰ ጋር ከመጮህ ውጪ ከተስማማህ ከደላህ ምን አለ ከደላህ ከሞላልህ ከደላህ ምን አለ ከደላህ…..🎧 ቤቴልም እንደ ከተበችው

«አንድ ሰው ይህ ያጋጥመዋል፤ ከእንቅልፉ ሲነሳ በጥልቅ ድንጋጤ ራሱን ይጠይቃል፦ እውነት ሃያ ሞላኝ? ሰላሳ፣ አርባ? እናስ ህይወት እንዴት አለፈች?!» ―ኢቫን ቶርጌኔቭ
«አንድ ሰው ይህ ያጋጥመዋል፤ ከእንቅልፉ ሲነሳ በጥልቅ ድንጋጤ ራሱን ይጠይቃል፦ እውነት ሃያ ሞላኝ? ሰላሳ፣ አርባ? እናስ ህይወት እንዴት አለፈች?!»                       ―ኢቫን ቶርጌኔቭ     

°° እኛ የቀትር ህልሞች ነን ቀን የተፋነውን እንቅልፍ ማታ የምናላምጥ 🎈
°°      እኛ የቀትር ህልሞች ነን ቀን የተፋነውን እንቅልፍ ማታ የምናላምጥ 🎈             

በወሬ መሀል እንደቀልድ በዋዛ ፈዛዛ ስምሽን ሲያነሱ ድንገት ነበር ሳቄ ከገፄ ላይ የተራገፈው... ድንገት ነበር ጨዋታ የጠፋብኝ... ድንገት ነበር በዝምታ ባህር ውስጥ የሰጠምኩት... ብቻ ከምሸሸው እኔነቴ ጋር ነው ያላተሙኝ.. አላወቁትም እንጂ ማባርያ ከሌለው ዶፍ ትዝታ ውስጥ ነበር የዘፈቁኝ... "!አንዳንዴ የተዳፈነ ትዝታ ሰው ፊት ሲነቃ አንገት ያስደፋል '' 121

አባት ሁሉ ወታደር ነው. .አንዳንዱ የገዛ ልጁን ሲገድል፤ አንዳንዱ ግን ልጁን ለማኖር እራሱን ያጠፋል!።
አባት ሁሉ ወታደር ነው. .አንዳንዱ የገዛ ልጁን ሲገድል፤ አንዳንዱ ግን ልጁን ለማኖር እራሱን ያጠፋል!።     

«አንድ ሰው ይህ ያጋጥመዋል፤ ከእንቅልፉ ሲነሳ በጥልቅ ድንጋጤ ራሱን ይጠይቃል፦ እውነት ሃያ ሞላኝ? ሰላሳ፣ አርባ? እናስ ህይወት እንዴት አለፈች?!» ―ኢቫን ቶርጌኔቭ
«አንድ ሰው ይህ ያጋጥመዋል፤ ከእንቅልፉ ሲነሳ በጥልቅ ድንጋጤ ራሱን ይጠይቃል፦ እውነት ሃያ ሞላኝ? ሰላሳ፣ አርባ? እናስ ህይወት እንዴት አለፈች?!»                       ―ኢቫን ቶርጌኔቭ      

ራሴን ብሎም ማንነቴን ለምወደው ሰው ከፍቼ ነበር፤ የምወደው ሰው ግን በእኔ ክፍተት ውስጥ በፍጥነት እጁን ሰደደና ህመሜን ቆፈረው!።
ራሴን ብሎም ማንነቴን ለምወደው ሰው ከፍቼ ነበር፤ የምወደው ሰው ግን በእኔ ክፍተት ውስጥ በፍጥነት እጁን ሰደደና ህመሜን ቆፈረው!።          

አንዳንድ ታሪኮችን ከህይወቴ መዝገብ አልሰረዝኳቸውም፤ ይልቅ ከመሃል ቀድጄ ጣልኳቸው!።
አንዳንድ ታሪኮችን ከህይወቴ መዝገብ አልሰረዝኳቸውም፤ ይልቅ ከመሃል ቀድጄ ጣልኳቸው!።                

ስልክ ሲደውልልኝ አለማንሳቴን ለምዶታል። ለፅሁፍ መልዕክቶቹ መልስ መስጠት .. ልክ የታክሲ ረዳት መልስ መመለስ የሚከብደውን ያህል ይከብደኛል። ለኔ የሚሰጠኝ ለራሱ የከለከለውን ፍቅር እንደሆነ ስለማ
ስልክ ሲደውልልኝ አለማንሳቴን ለምዶታል። ለፅሁፍ መልዕክቶቹ መልስ መስጠት .. ልክ የታክሲ ረዳት መልስ መመለስ የሚከብደውን ያህል ይከብደኛል። ለኔ የሚሰጠኝ ለራሱ የከለከለውን ፍቅር እንደሆነ ስለማውቅበት ያሳዝነኛል። ግን ለሀዘኔ ፊት አልሰጠውም። ለሀዘን ያልሆነ ፊት ደሞ ለእዘኑልኝ ባይ አይሆንምና ለሱም ቢሆን ፊት መንሳት እንጂ መስጠት አልችልበትም። ፍግግ እያለ ሲመጣ .. ስኳር ሳይጨመርበት የተማሰለ ግልምጫ ፉት አስብዬ ወደመጣበት እመልሰዋለሁ። መምጫውም መሄጃውም እሩቅ አይደለም። ጎረቤቴ ነው (የቢሮ 😏)። ቡና አንጠራራም ፥ ቁጭ ብለን ሰው አናማም ፥ አብሬው ነጠላ አልቋጭም .. ግን መሀላችን ያልተቋጨ ምስጢር አለ። እሱ .. ከራሱ ቀጥሎ ለሁሉ የነገረው .. እኔደሞ ከሁሉ በፊት ለራሴ የካድኩት። አብርሀም ይባላል። እኔ ግን ከአብርሀምነቱ የአብርሀም በግነቱ ይጎላብኛል። አብርሀም .. አስቦበትም ባይሆን .. አልፎ አልፎ እግረመንገዱን .. የአጉሊ መነፅር ብጉንጅ የሚያህሉ ክብ ብርጭቆዎችን እይታዬን ያግዝልኛል ብሎ ይለብሳል። የማይገርመው ነገር .. 'ትንሽ' ነገር ማጉላት የለመደ መነፅሩ .. እኔም ላይ አልሰነፈም። 'አይታየውም' ብሎ አጎላኝ .. 'ታዛቢ የለም' ብሎ አገዘፈኝ። ድሮም ለታማሚ ሰው ከመነፅሩ በላይ ጠላት የለበትም። አልወደውም። ግን ስህተቴ .. ሲወደኝ ዝም ብዬዋለሁ። አልወደውም። ግን ስህተቴ .. ሲስመኝ መልሼ ስሜዋለሁ (አንዴ ብቻ ቢሆንም)። አልወደውም። ግን ስህተቴ .. 'ልተንፍስሽ' ሲለኝ .. የእግዜር አየር ሳልሆን.. ጥሪት የሚከፈልበት ሰውሰራሽ የኦክሲጅን ታንክ መሆኔን ለመናገር አልደፈርኩም። 'ተንፍስ' አልኩት.. ተነፈሰኝ .. ከሞት መንታ መንገድ ወደኋላ አስፈገፈግኩት። ከሞት አፈግፍጎ ወደሞት። ድሮም ሞት ሲመጣ ዘጠኝ ሆኖ አይደል?😏 አንዱን ላመለጠው ሚስኪን .. የተቀረው ስምንቱ ሞት እኔ ነኝ። እኔን አገኘኋት ብሎ .. ለመገኘት የሚታመመውን 'እራሱን' አጣ። እየተነፈሰም ትንፋሽ እንዳጠረው ሰው ገረጣ። እያኖርኩት .. ብዙ ሞት ሞት የሚሉ ሌሊቶችን ከቤቴ በረንዳ አሳደርኩት። በፍርፋሪ .. በብጫቂ ጨርቅ .. በመሰንበቻ። "አንድ ቀን ትወደኛለች" ብሎ እንደሆነኮ አውቃለሁ .. ምክንያቱም እኔም ሌላ "አንድ ቀን ይወደኛል" የምለው ሰው ነበር። አንድ ቀን የሚባለው ቀን አይመጣም። ለኔም ለሱም አይመጣም። የሚመጣው የሆነ ቀን የሚባለው ቀን ነው የሆነ ቀን .. ከኔ ይለምነው የነበረውን ፍቅር ከራሱ መለመን ይለምዳል። አንድ ቀን .. ምናልባት አንድ ቀን .. አብርሀም አብርሀምን ይወደው ይሆናል። "አብርሽ" አልኩት "አ .. አቤት .. ወይ .. ወዬ" ተርበተበተ "ወዴት እና እመት ቀርተውሀል" አልኩት እየተቃለድኩ (ቀልቤ ተይ ይላል ከኋላ እያንዣበበ። የራስን ጥርስ ለመንከስ እየተገለገሉ .. የተነካሽን ጥርስ ለሳቅ ማንደርደር ልክ አይደለማ።) ኮስተር አልኩ። "ዛሬ ምሳ አብረን እንብላ?" አልኩት ምንም በማይነበብበት ሌጣ አስተያየት ምሳ ሰዐት .. ቤሎን ካፌ .. በጠረጴዛ ገላጋይነት በመተማመን ትይዪ ወንበር ላይ ተቀምጠናል። እያወራሁት እጁን በጨረፍታዎች ቦረሽ እያደረግኩት ነው። አፌ የሚስተውን ጣቴ እንደሚያርም አይነት። ዝም ብሎ እያዳመጠኝ ነው። ትዕግስተኛ ነው። ድሮም አብርሀም ለተባለ ሰው .. አንድን ልጅ 99 አመት ሙሉ መጠበቅ ብርቅ አይደለም። 99 ጊዜ ክብሩን ሸጦ .. ከገበያው ምንጣፉን ብድግ እንኳ ሳያደርግ .. ትርፉ ሁሉ በሆዱ እስኪጠፋ ድረስ ጠብቆኛል። የምነግረውኮ ልብ አንጠልጣይ ልብወለድ አልነበረም። ከአመታት በፊት በጣም አፈቅረው ስለነበር ሰው ነው። እያወራሁት አይኖቹን እመረምራለሁ። ስለሞቴ እየተረኩለት ህያውነቱ ይታወሰው ይሆን ብዬ ደሞ ትክዝ እላለሁም። የምናገረው ሁሉ ሲያሳምመው ወይ ሲያክመው ይታየኛል። ካከምኩት ግን ያሳመምኩት ይበልጣል። ሆኖም ግን አይኖቹ ውስጥ ከህመም ሌላ የማነብበው ደባል ስሜት ነበር። የሚያምር ስሜት ህህ .. መንሰፍሰፍ። አለመወደዱ እያንገበገበው .. አለመወደዴም ሲያንገበግበው። "ፍቅር .. ለልብ ግብር ከፋይ .. ህጋዊ የአዕምሮ በሽታ ነው። እብድ ያገግማል እንዪ አይድንም ሲባል አልሰማህም 😏 " አልኩት የመጨረሻ የሻይ ፉትታዬን እየፎትኩ። "ግን ትወጂኛለሽ?" አለኝ አይኖቹ እንባ እንዳቀረሩ "አንተ ራስህን የምትወደውን ያህል እወድሀለሁ።" አልኩት የተሰባበረ ልቡን ከአምስት የ2 መቶ ብር ኖቶች ጋር ጠረጴዛ ላይ ተወልኝና ወጣ። ድጋሚ አልተመለሰም። ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። እነሆ ባልንጀራህን እንደራስህ ውደድ እንደተባለ ሰምታችኋል ለአንዳንዶች ግን እላለሁ እራሳችሁን እንደባልንጀሮቻችሁ ውደዱ። ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ደር'ሃሲ ከዜሮ

Fight club 📽️ ላይ የምወዳት አንዲት አባባል አለች። በመከራ ላይ የተነገረች እውነተኛ ምክር፦ “ጠባሳው ባንተ ላይ ቢቀርም ህመሙ እንዲወስድህ አታድርግ። ካለስቃይ ካለ መስዋትነት ምንም ነገር
Fight club 📽️ ላይ የምወዳት አንዲት አባባል አለች። በመከራ ላይ የተነገረች እውነተኛ ምክር፦ “ጠባሳው ባንተ ላይ ቢቀርም ህመሙ እንዲወስድህ አታድርግ። ካለስቃይ ካለ መስዋትነት ምንም ነገር አናገኝም ነበር። መጀመርያ ተስፋ መቁረጥ አለብህ። ይህ ፍርሃት አይደለም የሆነ ቀን ትሞታለህ በቃ። ሁሉንም ነገር ካጣን በኋላ ምንም ነገር ለማድረግ ነፃ እንሆናለን።”

የሆነ ቀን ከአልጋ ጨዋታችን ቡኋላ ምርር ብሎት ጠየቀኝ " ለምንድነው ሁልጊዜ አድርገን ስንጨርስ ፊትሽን የምታዞሪው !? ከዛ ቡኋላ አቅፌሽ እንድተኛ የማትፈልጊው? " አለኝ " ከሰው ጋር ተቃቅፎ መተ
የሆነ ቀን ከአልጋ ጨዋታችን ቡኋላ ምርር ብሎት ጠየቀኝ " ለምንድነው ሁልጊዜ አድርገን ስንጨርስ ፊትሽን የምታዞሪው !? ከዛ ቡኋላ አቅፌሽ እንድተኛ የማትፈልጊው? " አለኝ " ከሰው ጋር ተቃቅፎ መተኛት አለመድኩም ። ከልጅነቴ ጀምሮ ሰው አብሮኝ ተኝቶ አያውቅም ። ይጨንቀኛል ለዛ መሰለኝ " አልኩት ። ግን አልነበረም። ይህን ሰው የወደድኩት አልመሰለኝም። ፍቅር ስንጀምር (እኔ አልጀመርኩም ምናልባት እሱ ተሰምቶት ከነበረ ) እንዲሁ እንደቀልድ እንደዋዛ ነው። ዝም ብሎ ወደድኩሽ ወደድኩህ የሌለው አይነት ነገር። በፊት በፊት ስላላከበረኝ በአገኘኝ በ 7ተኛው ቀን አብሮኝ ያደረ ይመስለኝ ነበር( አሁን ነው እሱ ሳይሆን እኔው ራሴን አለማክበሬ የተገለጠልኝ ) ሰዎች እግር ስር በገዛ እጃችን የጣልነውን ክብር አንስተው እንዲሰጡን ስንጠብቅ ነው የምናጠፋው ። ጥፋት 1 ይህ ሰው ደግነቱ ነው የሳበኝ። ትኩረት ስለሰጠኝ ነው ከስሬ አልጠፋም ሲለኝ ዝም ያልኩት። ለጥሩነቱ እና ለየዋህነቱ ሴትነቴን ነበር ያቀረብኩለት ። ሲስመኝ ስሜት ሳይሰጠኝ ዝም ብያለሁ ። (ደስታው ግን ያስደስተኝ ነበር ) ጭኖቼን ለመፈልቀቅ እስኪታገል አላስጠበቅኩትም ። ተው ይሄን ነገር አላልኩትም። የመወደድ ስሜት እንዲሰማው አድርግያለሁ ጥፋት 2 ልወደው ሞክሪያለሁ ። (በርግጥ እወድሃለሁ ያልኩት ከ 2 ጊዜ አይበልጥም) ግን ሞክሪያለሁ ። ለኔ ሲል የማይሆነውን ፤ ያለመደበትን ፤ የማይፈልገውን ሁሉ ሲሆን እያየሁ ዝም ማለት አልቻልኩም ወደራሴ ላቀርበው ጥርያለሁ። የኔን ፈገግታ ለማየት እሱን በማይመጥኑ ሰዎች ፊት ክብሩን ሲጥል እያየሁ ችላ አላልኩትም። አብሬው ለመቆየት ከስሜቴ ታግያለሁ ። ጥፋት 3 ብቻችንን ስንሆን ያለው እሱ ይጨንቀኝ ነበር። ሴትነቴ መሃል ሲገባ ከወንድነቱ ያንስብኛል። ሳቅፈው የስድስት አመት ህፃን ልጄን እያባበልኩ ያለው ይመስለኛል ። እሱ ከላዬ ላይ ሆኖ እየተደሰተ እኔ ምሳ ሰዓት ላይ ስላናደደኝ ሰውዬ አስቤ አውቃለሁ ። "የኔ ፍቅር ጨረስኩ.. ጨረስሽ ?" ሲለኝ ' ምኑን ነው' ብዬ ተደነባብሬ አውቃለሁ ። "አሳፍሬሽ ነው አይደል ? ይቅርታ " ብሎ ግንባሬን ሲሰመኝ በዝምታ ተስሜ አውቃለሁ። ጥፋት 4 እንለያይ አልኩት። አልደበረውም ፤ አልተከፋም ፤ ምንም የተለየ ስሜት አልተሰማውም ። ቀለል አርጎ "እሺ " አለኝ። ምናልባት እሱም እንደኔ ቀን እየጠበቀ የነበረ መሰለኝ። የመለያያ ጊዜያችንን አብሮ ከመፍጀት በቀር ምንም የጋራ ነገር ሳይኖረን እንዲሁ በሰውኛ ባህሪያችን ብቻ እየተሳሳቅን የቆየን መሰለኝ። የመጨረሻ ጥፋት ልክ እንደዚህ እንደፃፍኩት ቀሽም ፅሁፍ ቀሽም የሆነ ትዝታ አልፎ አልፎ እየመጣ ይረብሸኛል....!🖤 ፊያሜታ አፈወርቅ

Repost from እንማር
✅የሄድሽ ቀንኮ አደለም!!! ልትሄጂ እንደሆን ያሰብኩ ቀን ራሱ እጨነቅ ነበር።ስትሄጂ ምን እንደምሆን ሳስብ እፈራ ነበር።ተደግፌሽ እንደቆምኩ ያላንቺ ማንም እንደሌለኝ ስለማስብ ይሆን???እኔንጃ!! ✅
✅የሄድሽ ቀንኮ አደለም!!! ልትሄጂ እንደሆን ያሰብኩ ቀን ራሱ እጨነቅ ነበር።ስትሄጂ ምን እንደምሆን ሳስብ እፈራ ነበር።ተደግፌሽ እንደቆምኩ ያላንቺ ማንም እንደሌለኝ ስለማስብ ይሆን???እኔንጃ!! ✅ብዙ ቀን ግን ስሜቴ ትሄዳለች እያለኝ አልቅሻለሁ ብዙ ቀን ልቆጣሽ ብዬ እንዳትተዪኝ ፈርቼ ትቼዋለሁ ኩርፊያሽ አለም ያኮረፈኝን ያህል እንዲሰማኝ ስለሚያደርግ ኩርፊያሽን እፈራዋለሁ ካንቺ ጋ የተገናኘሁበትን ቀን እስክረግመው ተጨንቄያለሁ ✅የሌላ ሆነሽ አስቤ ብዙ ቀን ብቻዬን አብጃለሁ ምን እያሰበች ይሆን??ደብሬያት ይሆን??እንደድሮ ትወደኝ ይሆን??ልቧ ውስጥ ሌላ ሰው አለ ይሆን እያልኩ ተብሰልስያለሁ.. ፈርቻለሁ ምድር ላይ ሰው እንዳልተፈጠረ ያህል ሁሉን ረስቼ አንቺን ብቻ አስቤሻሁ አንቺን ብቻ አፍቅሬሻለሁ ...ካንቺ ከመለየት ሞቴን መርጫለሁ ግን አንድ ቀን ደወልሽልኝና ፈጥኜ አነሳሁት..ደና እንደሆንኩኝ እንኳ አልጠየቅሺኝም "መለያየት አለብን" አልሺኝ ያን ቀን ፍሪጅ እንደከረመ ውሀ በረዶ ሆንኩኝ እንደሬሳ ቀዘቀዝኩኝ ቀጥሎ የሚፈጠረውን ሳስብ መብራት እንደጨበጠ ደርቄ ቀረሁኝ ለምን?እንዴት?አላልኩሽም።ዝም እንዳልኩሽ ስልኩ ተዘጋ።በቀናት ውስጥ አዲሱ ፍቅረኛሽን እየሳምሽው እኔን እንደተውሺኝ ለማሳበቅ ለህዝቡ አወጅሽ ✅አሁን ሲያይ ምን ይሰማዋል?? አላልሽም!!!ይከፋው ይሆን??አላልሽም!!ለሚጠይቁት ሰወች ያስጨንቁት ይሆን??አላልሽም!!ብዙ በሳሳውልሽ ልክ ጨከንሽብን!!ባከበርኩሽ ልክ አዋረድሺኝ!!የት ሄደች እያሉ የሚጠይቁኝን ለመሸሽ ቤቴን ትቼ ወጣሁ።ሰፈሩ ደበረኝ ።አንድ ቀን ሰበብ ፈልጌ መንገድ ዳር አደርኩኝ ።እኔ ብቻ ሳወራ ደስ አለኝ ..ነፃነቴን ያገኘሁ መሰለኝ... በሁለተኛው ቀን እሳት አነደድኩኝ ሰው ሁሉ እየመጣ ሲያየኝ አብዶ ነው የሚል ስያሜ ተሰጠኝ አልደበረኝም ማህበረሰብ ተስማምቶ ስም ሲለጥፍ በኔ አልተጀመረ እኔም አመንኳቸው መሰል ✅ጥልቅ ፍርሀት እብደት ይወልድ የለ የፈራሁት ሲደርስ ቬሎ ለብሰሽ ስታገቢ እኔ ድሪቶዬን ለብሼ አበድኩልሽ ታድለሽ አንድ እብድ አለሽ 🌐@Enmare1988 🌐@Enmare1988

ልቤ ከድንጋይ የተቀረጸ ይመስለኛል። ፍቅር ወይም ህመም አይሰማኝም። አንዳንዴ ራሴን ያጣሁ ያክል ይሰማኛል ፤ ሰዎች ይስቃሉ፣ ይጮኻሉ እና ይፈራሉ። እኔ ግን ምንም ነገር አልሰማም ለምንም ነገር ፍላጎ
ልቤ ከድንጋይ የተቀረጸ ይመስለኛል። ፍቅር ወይም ህመም አይሰማኝም። አንዳንዴ ራሴን ያጣሁ ያክል ይሰማኛል ፤ ሰዎች ይስቃሉ፣ ይጮኻሉ እና ይፈራሉ። እኔ ግን ምንም ነገር አልሰማም ለምንም ነገር ፍላጎት የለኝም። ከዚህ ዓለም ጋር ያለው የግንኙነት መስመር እየደበዘዘ ነው? ስል ራሴን ጠይቃለሁ። ከሰዎች ጋር ለመነጋገር እሞክራለሁ፣ ነገር ግን አንዳንዴ ቃላቶች ይጎድሉኛል ከአእምሮየ ይጠፋሉ ። ለምን እንደሆነ ማንም ሰው ሊረዳኝ አይችልም። ይህን ማንም የማይረዳውን ህመም በምን እገልጻለሁ? ሰዎች 'እንዴት ነህ?' ብለው ይጠይቁኛል። 'ደህና ነኝ' ብዬ እመልሳለሁ። ምክንያቱም የኔን ህመም ለሰው ልነግረው አልችልም። ቃላቶች እንኳን ሊገልጹት አይችሉም። ስለዚህ በዝምታ መጎዳት እመርጣለሁ።

በድድብናችን ምክንያት መከራ ውስጥ ገብተናል። ነገር ግን ህመሙ አይሰማንም ምክንያቱም ደደብ ነን!🤝🏼☹
በድድብናችን ምክንያት መከራ ውስጥ ገብተናል። ነገር ግን ህመሙ አይሰማንም ምክንያቱም ደደብ ነን!🤝🏼☹

Repost from እንማር
“የሌሎችን ሰቆቃ እና ስብራት ስትመለከት አትሳቅ፤ ቁስል በሚኖርበት ጊዜ መነጋገር መዳኒት ነውና በቁስሎች መካከል ሰው መሆን ወይም ለመሆን እየሞከርህ ሙት..” ፦ሊዮ ቶልስቶይ ✔️@Enmare1988
የሌሎችን ሰቆቃ እና ስብራት ስትመለከት አትሳቅ፤ ቁስል በሚኖርበት ጊዜ መነጋገር መዳኒት ነውና በቁስሎች መካከል ሰው መሆን ወይም ለመሆን እየሞከርህ ሙት..                      ፦ሊዮ ቶልስቶይ                     ✔️@Enmare1988 ✅️@Enmare1988

‹‹My plan was that we sit here for a while. talk about old times. drink some whiskey 🥃. then I was gonna tell you. I hadn't
‹‹My plan was that we sit here for a while. talk about old times. drink some whiskey 🥃. then I was gonna tell you. I hadn't spent a day without thinking about you!.›› “እቅዴ ለትንሽ ግዜ እዚህ መቀመጥ ነው። ጥቂት ውስኪ እየተጎነጨው ስለድሮ ግዜ ማውራት። ከዚያም እነግርሽ ነበር፤ አንድም ቀን ስላንቺ ሳላስብ አልፎ አያውቅም”          📽️ Peaky blinders