ar
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Assaye Derbie

تُعد قناة Assaye Derbie (@asayede) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 368 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 646 في فئة المدوّنات والمرتبة 2 349 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 368 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 18 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -169، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -11، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 37.71‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 11.37‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 419 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 634 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 38.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

وصف القناة غير متوفر.

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 19 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة المدوّنات.

14 368
المشتركون
-1124 ساعات
-237 أيام
-16930 أيام
أرشيف المشاركات
photo content

ብርቱካን ያስተናገደችውና የተናገረችው ግፍ በቪዲዮ ሲደገፍ ይሄንን ይመስላል።

የ7ኛ ቀን "ዘመቻ-አንድነት" መረጃዎችን ይከታተሉ 👇 የኤቢሲ ቴቪ (ABC TV) ሁለተኛ የዩቲብ ገፅ በመቀላቀል የአማራን ትግል መረጃዎችና ልዩ ልዩ መሠናዶዎች ይከታተሉ። https://youtube.com/@abctv2nd?si=WwwRfTaA363v1nbN

#የኦህዴድ እና የኦነግ የእገታ ዶሴ በስሱ ሲገለጥ አሳዬ ደርቤ❗️ ➖➖➖ share የሚደረግ 1.👉ህዳር 25/2012 ዓ. ም 17 የአማራ ብሄር ተወላጅ የሆኑ የደንቢዶሎ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በኦነግ ሸኔ ታጣቂ ቡድን ታግተው ይኑሩ ይሙቱ ሳይለይ ተረሱ። ቤተሰቦቻቸው በተደጋጋሚ" የመንግስት ያለህ የልጆቻችንን ነገር አንድ በሉን"ቢሉም ሰሚ ሳያገኙ ቀሩ። 2.👉ህዳር 29/2015 በእለተ ሀሙስ ከደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ወደ አዲስ አበባ በኦዳ ባስ በሚጓዙበት ወቅት በምእራብ ወለጋዋ የጊምቢ ወረዳ ጉሊሶ ቀበሌ ውስጥ 9 የአማራ ተወላጅ ተማሪዎች ታገቱ። ታጋች ተማሪዎችም 1ኛ. ተማሪ ደጀኔ ያለው - IT department 3ኛ ዓመት ተማሪ 2ኛ. ተማሪ ኪሩቤል መለሰ- Civil department 5ኛ ዓመት ተማሪ 3ኛ. ተማሪ ብርሃኑ አበባው - Civil department 5ኛ ዓመት ተማሪ 4ኛ. ተማሪ ማህሌት ዘላለም - Business management department 3ኛ ዓመት ተማሪ 5ኛ. ተማሪ ሲሳይ ጋሻዬ -psychology department 3ኛ ዓመት ተማሪ 6ኛ. ተማሪ ሰዓዳ ሞሀመድ- Mechanical department 5ኛ ዓመት ተማሪ 7ኛ. ተማሪ ቤዛዊት ተሾመ- Architecture department 5ኛ ዓመት ተማሪ 8ኛ. ተማሪ ብዙአየሁ አረጋ Law department 5ኛ ዓመት ተማሪ መሆናቸው ታውቋል።በተጨማሪም በሥም ያልተጠቀሱ ሌሎች የታገቱ ተማሪዎች እንዳሉ በተለያዩ ሚዲያዎች ተዘገበ። 3👉 ከአማራ ክልል ተነስተው ወደ ዋና ከተማዋ አዲስ አበባ በአውቶብሶች ሲጓዙ የነበሩ ከአንድ መቶ በላይ የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ሰኔ 25/2016 ዓም በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ገርበ ጉራቻ አካባቢ በታጣቂዎች መታገታቸውን ቢቢሲ ዘገበ። 4.👉በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ወረ ጃርሶ ወረዳ ልዩ ስሙ "አሊዶሮ መውጫ' በተባለ ሥፍራ ታጣቂዎች መጋቢት 8/2017 እኩለ ቀን ላይ የአንድ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ውስጥ የነበሩ 60 ተሳፋሪዎችን በሙሉ አፍነው ወሰዱ። ከዚያ በአንድ ሰው 1.5 ሚሊዮን ብር ጠየቁ። ምንጭ ቢቢሲ 5.👉 ከቀናት በፊት በተመሳሳይ መልኩ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አሊዶሮ አካባቢ በቀን 14/7/2017 አንድ ታታ አውቶብስ ሙሉ 60 ሰው ታገተ። ምንጭ ዋዜማ 6.👉በኦሮሚያ ከልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ ከጎርፎ ከተማ ወጣ ብሎ ባለ ሥፍራ፣ ታጣቂዎች ከሶስት ቀን በፊት 10 ሰዓት ገደማ በሁለት ተሽከርካሪዎች ላይ በፈጸሙት እገታ 40 ያህል ተሳፋሪዎችን አፍነው መውሰዳቸውን ዋዜማ ሬዲዮ ዘገበ። 7.👉በደራ ወረዳ (27/12/015) ኦነግ በሚባለው ታጣቂ ከቆሮ ፣ ከግንደበርበሬ፣ ከራቾና ከሮብገበያ ቀበሌዎች ወደ ወረዳው ዋና ከተማ ጉዶመስቀል ለገበያ ይጓዙ የነበሩ ከ300 በላይ ንፁሃን ገበያተኞች እገታ ተፈጸመባቸው ። በአካባቢው ለኦነግ ድጋፍ እንዲያደርግ የተላከው መከላከያ ተብዬውም ለድርጊቱ ሽፋን በመስጠት ተባባሪ እንደነበር የመረጃ ምንጮች ሲናገሩ ነበር። 8. 👉በ26/12/15) ከሰላይሽ ከተማ ቁጥራቸው በውል የማይታወቁ የከተማዋ ነዋሪዎችን ማገቱም በተለያዩ ሚዲያዎች ሲዘገብ ነበር። 9.👉"…ማክሰኞ መስከረም 22/2016 ዓም በኦሮሚያ ክልል አዲስ በተዋቀረው ሸገር ከተማ ሱሉልታ ክፍለ ከተማ በተለምዶ አዲሱ ኬላ ወይም ቆዳ ፋብሪካ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ታጣቂዎች 9 ሰዎችን አግተው መውሰዳቸውንና ለታጋቾቹም ማስለቀቂያ ለእያንዳንዳቸው ታጋቾች በነፍስ ወከፍ 300 ሺህ ብር መጠየቃቸውን አዲስ ማለዳ ጋዜጣ ዘገበ። "…እነዚሁ ታጣቂዎች ከዚህ ቀደም በዚሁ በሱሉልታ ክፍለ ከተማ ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን አካባቢ ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ላይ በመግባት፤ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎችን ወስደው መሰወራቸውን አዲስ ማለዳ መዘገቧ ይታወሳል፡፡ 10.👉. በ08/11/2015 ከቀኑ 6 ሰአት አካባቢ የሼር ኢትዮጵያ መኪና ሾፌር የሆነው መስፍን በኦሮሚያ ክልል በተለምዶ ዱኒ የሚባል አካባቢ በሶደሬ መስመር ወይን ለመጫን ሄዶ በዚያው ታግቶ ቀረ። የሹፌሮች ድምጽ 11.👉 በ12/03/2015 ከቀኑ 10 ሰአት ከወለንጭቲ መተሃራ መንገድ 55 ላይ 1 የህዝብ ሚኒባስ 1ሃይሉኩስ 3 ተሳቢ ታግተው ሹፌሮች፣ ተሳፋሪዎችና ረዳቶች ተወሰዱ። ምንጭ አልአይን 12.👉 በኦሮሚያ ክልል በወሊሶ ዞን አራት ታዳጊዎች በኦነግ ሽኔ ታግተው አራቱንም ለማስለቀቅ ብር ይጠየቅባቸዋል። ከዚያም የተጠየቀውን ብር ይዘው ወደ ስፍራው ያመሩ ቤተሰቦችም መታገታቸው ሲነገር ነበር። 13.👉በኦሮሚያ ክልል በአሩሲ ዞን ፖሊስ ጣቢያ ፊትለፊት 9 ዐማሮች ይገደላሉ። ከዚያም ዘመድ አዝማድ ከሩቅም ከቅርብም ተጠራርቶ እየተላቀሰ መጥቶ ቀብር ዋለ። ከቀብር መልስም መንገድ ላይ ቀባሪዎቹ እንደገና ታግተው ይወሰዳሉ። እናም በወቅቱ አጋቾቹ አንዱን ታጋች ገድለው በ3ቱ ሲደራደሩ እንደነበር በኢሰመጎ ጭምር ሲዘገብ ነበር። 14.👉 "…በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሽዋ ዞን ኩዩ ወረዳ በምትገኘው ምድረ ገነት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን ጥቅምት 19/2015 ዓም ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ በማኅሌተ ጽጌ ላይ ሳሉ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች አንድ ዲያቆን ገድለው ካገቷቸው 11 የቤተ ክርስቲያኒቱ አገልጋዮች መካከል ለሦስቱ በድርድር ገንዘብ ተከፍሎ ሲለቀቁ 8 ካህናት ግን ታግተው ቀርተው ነበር። የሚገርመው ነገር ታዲያ አደራዳሪው የኦሮሚያ ፖሊስ ሲሆን ብሩ የሚገባው ደግሞ በኦሮሚያ ባንክ ነው አሉ። 15. 👉በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉዱሩ ዞን አዴ ደንጎሩ ወረዳ ቱሉ ገና ወይም አንገርጉትን ላይ ጥር 11 /2012 ዓ'ም የጥምቀት በዓል ላይ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራ ለምን ይዛችሁ ወጥታችሁ ተብለው 30 የሚደርሱ የአማራ ብሄር ተወላጆች ታፍነው ተወስደው የት እንደደረሱ ሳይታወቅ መቅረቱን በአማራ ድምጽ ሲዘገብ ነበር። 16.👉በቀን 26/03/2015 ዓ.ም በሆሳዕና ከተማ ማንነታቸውን ባልተወቁ ሰዎች በግምት 9:00 ሰዓት አከባቢ 9 ተማሪ 1ዱ ከዋቸሞ አጠቃላይ 2ኛ ደረጀ ት/ቤት ስሆን ቀሪዎቹ ከWorld bright ትምህርት ቤት/ በመኪና አፍኖ ወደ ያልታወቀ ቦታ መወሰዳቸው ተገለፀ! 17.👉እሮብ ማታ እንጪኒ እና ዳንጎቴ መንገድ ሌሊት ላይ ከሰል ድንጋይ ጭነዉ ሲመጡ 8 ሹፌሮች መታገታቸው በሹፌሮች ድምጽ ተዘገበ። 18.👉 በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ከደብረሊባኖስ አከባቢ ወደ ያያ ጉሌሌ ለገበያ ሲጓዙ የነበሩ አንድ ተሽከርካሪ ሙሉ 50 ሰዎች ግድም የሚሆኑ ነጋዴዎች ሳዲኒ ብዮ ከሚባል የያያ ጉለሌ ወረዳ ታፍነው ተወሰዱ። ሕዝቡም ሰልፍ ወጥቶ ተቃወመ። 19.👉በምሥራቅ አርሲ ዞን በሮቤ ዲደዓ ወረዳ ጄና ገደምሳ ገበሬ ማኅበር ቀበሌ ውስ ጥ በልዩ ስሙ መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን አከባቢ ከቀኑ 11:00 ላይ በኦርቶዶክሳውያን ላይ የግድያና የእገታ ጥቃት ተፈጽሟል። በጥቃቱም አቶ ጣፋ በቀላ የሚባሉ ኦርቶዶክሳዊ ሲገደሉ፣ዲ/ን ገዛኸኝ ለማ ፣ከተማ ካሳ፣ጋሻሁንና ደሲ የተባሉት ደግሞ ታግተው መወሰዳቸውን የማሕበረ ቅዱሳን ሚዲያ ዘገበ። 20.👉 አምና በ2016 ዓመተ ምሕረት በአዲስ አበባ የሚሰሩና በኦሮሚያ የሚኖሩ የፐብሊክ ሰርቪስ ሰራተኞች በሰማያዊው የፐብሊክ ሰርቪስ ተጭነው ወደ ቤታቸው እየሄዱ ሳለ ታጣቂዎች ሹፌሩን ገድለው በውስጥ ያገኟቸውን አማርኛ ተናጋሪ ሲቪል ሰርቫንቶች አግተው ወሰዱ። ክፍል ሁለት ይቀጥላል። #ምንጭ እየጠቀሱ post ወይንም share ያድርጉት።

ሙሉ ቪዲዮው

አሰቃቂ የእገታ ታሪካቸውን የተናገሩበትን ቪዲዮ ያስጠፋው አረመኔው አገዛዝ ደብዛቸውን ሳያጠፋቸው በፊት እኅቶቻችንን ልንደርስላቸው ይገባል። እና ደግሞ ሙሉ ቪዲዮው ያላችሁ ብታጋሩን መልካም ነው።

የቄስ ሞገሴዎች ዝርዝር ➖➖➖➖ ❶ብርሐኑ ነጋ ❷ዳኛቸው አሰፋ ❸ዳንኤል ክብረት ❹ነቢዩ ባዬ ❺አለማሪያም ❻አበባው አያሌው ❼ግርማ ሰይፉ ❽ደበበ እሸቱ ➒ዮናስ ዘውዴ ❿ቀለጠ ሞላ እጩ ቄስ ሞገሴዎች ❶ጋሻው መርሻ ❷ጧሒር መሐመድ ጨምሩበት

በፋኖ የታወጀው ዘመቻ አንድነት የአፋሕድን የዲጂታል ሠራዊት ስለምን አበሳጬ? ከአገዛዙ ጋር የጀመራችሁት ድርድር ባላለቀበት ሁኔታ "መንግሥታችንና ሠራዊታችን ተጠቃብን" የሚል ለቅሶ ተገቢ ነው ወይ?

የጎጃም ግንባር የድል ዜና ደርሷል! "ዘመቻ አንድነት" በሚል በመላው አማራ እየተደረገ ባለው ጠላትን የመደምሰስ የጋራ ዘመቻ ዛሬ መጋቢት 10 ቀን 2017 ዓም በአማራ ፋኖ በጎጃም በሰባት ክፍለጦር በተደረገ ከባድ ማጥቃት በጠላት ላይ ከመቸውም ጊዜ በላይ ጠንካራ ሰዋዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ ማድረስ ተችሏል ። በዚህም :- 1/ 4 ብሬን ፣ 1 ስናይፐር 75, ክላሽንኮቭ ፣ 7,600 ጥይት ፣ 3 የመገናኛ ራዲዮ ተማርኳል። 2/ በአማራ ፋኖ በጎጃም በአጠቃላይ በ35 ግንባሮች አውደ ውጊያ የተደረገ ሲሆን ውጊያው አሁንም እንደቀጠ ለ ነው ። 3/ በደብረማርቆስ ፣ አዴት ፣ ጎንጅ ቆለላ ፣ ቢቸና ፣ ደብረወርቅ ፣ ሰዴ ፣ ድጎፅዮን ፣ ቁይ፣ የዕድ ውሐ ፣ አማኑኤል ፣ ደምበጫ ፣ መርጡ ለማርያም ፣ ረቡዕ ገበያ ከተሞች በመግባት የጠላት ሐይል ከባድ ኪሳራ አድርሰናል ። 4/ እስካሁን በአጠቃላይ ከ509 የጠላት ሐይል ሙት ሲሆን 287 ቁስለኛ በማድረግ ከባድ ኪሳራ አድርሰናል። ዘመቻ አንድነት ይቀጥላል!

ሰበር ዜና! ዘመቻ አንድነት በመላው አማራ ታወጀ የአማራ ሕዝብ የገጠመውን መንግሥት መር የዘር ጭፍጨፋ ለማስቆም የኅልውና ትግል ከጀመረ ሃያ ወራትን አስቆጥሯል። በእነዚህ ወራት በተበታተነ መልኩ ይሁን እንጅ በጠላት ላይ ቁሳዊ፣ ሰዋዊ፣ አዕምሯዊና መሰል ኪሳራዎችን ማድረስ ተችሏል። በስም መከላከያ የሚባለውን ወራሪ ሠራዊት በማፍረስ በኩልም አስደናቂ ተግባራት ተከናውነዋል። አማራውን በማጥፋት እብደት ውስጥ ቀጥተኛ ሱታፌ እያደረገ የሚገኘው የአብይ አሕመድ ደንገጡር የክልሉ ካድሬ መዋቅር ብትንትኑ ወጥቶ እንቅልፍ አልባ የዛፍ ላይ ሕይወትን በመግፋት ላይ ይገኛል፤ ጥቂት የማይባሉትም እጃቸውን ሰጥተዋል። "ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን" ነውና ከቀጠናዊ አደረጃጀቶች የተሻገረ ወጥ የሆነ አንድ ተቋም በመቋጨት ዋዜማ ላይ አንድ አማራዊ ተቋም መገንባት ያለውን ፋይዳ አመላካች ተግባርን ዛሬ መጋቢት 10/2017 ዓ.ም ላይ በመላው የአማራ ግዛቶች ጠላት በሚገኝባቸው ካምፖችና ምሽጎች ሁሉ ከሌሊቱ 10:00 ጀምሮ ማጥቃት ጀምረናል። ይህ በአንድነት እየተከናወነ የሚገኘው የማጥቃት ኦፕሬሽን በቀጣይ ገቢራዊ ለምናደርገው አንድ አማራዊ ተቋም እንደመስፈንጠሪያ ጉልበት ይሆነናል። የድላችን መቋጠሪያ፣ የኅልውናችን ማረጋገጫ መንገዱም ስልተ ጥበቡም አንድ ነው፤ እሱም አንድነት። መታገያ ጉዳያችን "ኅልውናችን" ዓለማና ግባችንም የታወቀ አንድ ጉዳይ እንደያዘ አካል አንድ አታጋይ ተቋምን ገቢራዊ ማድረግ ለነገ የማንለው ቁልፍ ጉዳይ እንደሆነ ብናምንም በትግል ሜዳችን የተሰገሰጉ ከኅልውና ትግላችን በተቃራኒ የቆሙ በታጋይነት ጭንብል የተጀቦኑ አስተሳሰቦች፣ ቡድኖችና አደረጃጀቶች ገቢራዊ ከምናደርገው አንድነታችን እንድንዘገይ አደረገን እንጅ አማራዊ አንድነቱን ገቢራዊ ከማድረግ አያስቆሙንም። በአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል የሚቆምሩትን፣ የሚቀልዱትን ግብራቸው፣ እኔነት አስተሳሰባቸው፣ ከፋፋይነታቸው፣ ግጭት ጠማቂነታቸው፣ ከሥርዓቱ ጋር ድብቅ ጋብቻቸው፣ የሥልጣንና የገንዘብ ፍትወታቸው ሕዝባችንም ታጋዩም በውል የተረዳበት ሰዓት ላይ እንገኛለን። እንደዚህ ያሉትን ጸረ አንድነት ኃይሎችን እያራገፍን የሕዝባችንን ኅልውና በአንድ ተቋምነት ማረጋገጥ ደግሞ በየቀጠናችን የተወሸቁ እንቅፋቶችን ተራምደን፣ ሳይረዱ በጠላት ጎራ የተሰለፉትን ጉዳዩንም መርምረው እንዲመለሱ ጥሪ እናቀርባለን። በአጠቃላይ ከዛሬ መጋቢት 10/2017 ዓ.ም ጀምሮ በጠላት ላይ ጥቃት የመሰንዘር ወታደራዊ ኦፕሬሽን በአራቱ ጠቅላይ ግዛቶች በሚገኙ ወታደራዊ አዛዦች ቅንጅት እየተከናወነ የሚገኝ አኩሪ ተግባር ነው። በዚህ ተናባቢና የአንድነት ዘመቻ የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አማራ)፣ የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር፣ የአማራ ፋኖ በሸዋ እና የአማራ ፋኖ በጎጃም ቀጥተኛ ተሳታፊዎች ናቸው። ዛሬ በወታደራዊ አዛዦች ፊታውራሪነት አፈሙዛችንን በአንድ እለት፣ በአንድ ሰዓት የማስተባበርና የማቀናጀት ተግባር ብርቱ ጉልበታችንን ከማሳዬት ባሻገር አንድ አስተሳሰብ ያለን መሆናችንን በገቢር ያሳየንበት የሠራዊታችንን እንዲሁም የሕዝባችንን ተስፋ ያለመለምንበት ድንቅ ሥራ መሆኑ ሥራችን ምስክር ነው። "ዘመቻ አንድነት" ዛሬን ጨምሮ ለሚቀጥሉት ተከታታይ ቀናት ተጠናክሮ የሚቀጥል ሆኖ አንድ አማራዊ ተቋም በመገንባትም የሕዝባችንን ኅልውና ያረጋግጣል። ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!! "ዘመቻ አንድነት" የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር የአማራ ፋኖ በሸዋ የአማራ ፋኖ በጎጃም የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አማራ)

ሀይ ወገኖች የብልጽግና የዲጂታል አርሚ በተደራጀ መልኩ በሚያደርገው ሪፖርት ሁለት ቪዲዮ ከማስወረድ ባለፈ ጠለስ ሚዲያን ለማዘጋት እየተንደፋደፈ ስለሆነ አዲስ የከፈትነውን ሁለተኛ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ታደርጉ ዘንድ እንጠይቃለን። https://youtube.com/@telesmedia2?si=Owd3fVUj-ck6zBs2