Assaye Derbie
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Assaye Derbie
تُعد قناة Assaye Derbie (@asayede) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 335 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 651 في فئة المدوّنات والمرتبة 2 347 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 335 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 26 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -104، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -8، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 35.99%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 12.61% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 158 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 808 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 30.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 27 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة المدوّنات.
14 335
المشتركون
-824 ساعات
-327 أيام
-10430 أيام
أرشيف المشاركات
14 335
የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የሮኬት ሳይንስ ማዕከል በአጼ ቴዎድሮስ ሥም የሰየመውን ሮኬት ስኬታማ በሆነ መልኩ ማስወንጨፉ ቢታወቅም... ጉዳዩን በንቃት ሲከታተሉ የከረሙ አንዳንድ አካላት በሮኬቱ ዙሪያ ሐሳባቸውን ከመግለጽ ተቆጥበዋል። 😆 👏👏
14 335
"በብሔር ማሰብ የለባችሁም" በማለት ብሔርተኛው መሪ የሠጡት ምክር በዋናነት የሚመለከተው የአማራ ተወላጅ የሆኑ የጦር መሪዎችን ሲሆን... የንግግሩ ፍሬ ሐሳብም "በአማራነት አታስቡ" እንደማለት ነው።
14 335
ከሰሞኑን በወለጋ አካባቢ በተካሄደ ኦነግ ሸኔን የማጥፋት ዘመቻ "መገደል የለብንም" በሚል አቋም እራሳቸውንና ቤተሰባቸውን ሲጠብቁ የነበሩ ጽንፈኛ አማራዎችን ትጥቅ የማስፈታት ሥራ ተከናውኗል።
14 335
ለፋኖዎች‼️
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
➔ፋኖን የመከፋፈልና የማጥፋት ዓላማ አንግበው የሚመጡ ሃይሎችን ለመከላከል ይረዳ ዘንድ ባግባቡ የማታውቋቸውን ወጣቶች አባሎቻችሁ አታድርጉ፤
➔ባንዳንድ ጉዳዮችና ችግሮች ዙሪያ ማብራሪያ ከሚሰጡ ቃለ አቀባዮች ውጭ በእናንተ ሥም ሚዲያ ላይ እየቀረበ ሕዝብንም ሆነ ፋኖን የማይጠቅም ንግግር የሚያደርግ አካል እንዲኖር አትፍቀዱ፤
➔በሳምንት ውስጥ የተወሰኑ ቀናትን በመምረጥ እያንዳንዱን የአማራ ወጣት የሚያሳትፍ የአካል ብቃት እና የፋኖነት የሥልጠና መርሐ ግብር አዘጋጁ፤
➔የትግል መርሓችሁ አንዱ ዞን ሲጠቃ ሌላ ዞን ላይ ተቀምጦ የወረራ ወረፋ መጠበቅ ሳይሆን ጥቃት በተከሰተበት ስፍራ ሁሉ ፈጥኖ መገኘት እንዲሆን በክልል ደረጃ የሚያስተሳስር አደረጃጀት መሥርቱ፤
➔በመሀከላችሁ ሽኩቻ እንዳይነግስ የእናንተ እውቅና በሌለው እክል እርዳታ የሚጠይቅ የፋኖ አባል እንዲኖር አትፍቀዱ፤
➔ከጥቃት የምትጠብቁት ወገን እንጂ ሥጋት የምትፈጥሩበት አካል አይኑር፥
➔እያንዳንዱ ተግባራችሁ ከካሜራ የራቀ ይሁን፤
➔በሰነድ የሚወጣውን የመንግሥት ዛቻ እና በፌስቡክ የሚሰራጨውን የሥም ማጥፋት ዘመቻ ስትመክቱ ሥልጠናው እንዳይረሳ... ብዛታችሁን ከሥማችሁ ጋር ለማመጣጠን ሞክሩ፤
14 335
ከሕዝብ ጉያ ሳታወጣ- ሰለባህን አትቅጣ‼️
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬
የትኛውም የብአዴን አመራር ከሥልጣን ሊነሳ የሚችለው አንድም የመንግሥትን አካሄድ ሲቃወም፣ አንድም የሕዝብን በደል ተጋርቶ ሲያልጎመጉም የተገኘ ቀን ነው፡፡ አለቀ፡፡
በተረፈ ለሥርዓቱ ታማኝ መሆኑን እስካረጋገጠና የሕዝብን ጉዳይ ‹‹ምን አገባኝ›› በሚል ስሜት ማለፍ እስከቻለ ድረስ በስነ ምግባር ጉድለትም ሆነ በኪራይ ሰብሳቢነት ጎዳና ውስጥ ተዘፍቆ ቢገኝ የሚያባርረው ቀርቶ የሚገመግመው አይኖርም፡፡ እንደውም የተሻለ ሥልጣን ሊሰጠው ይችላል፡፡
ከዚህ አንጻር ከዓመታት በፊት አቶ ዘርዓይ አሰገዶምን እና አባይ ወልዱን ተጋፍጠው የህውሓት ውድቀት ላይ ጉልህ ሚና የተጫወቱት አቶ ገዱና አቶ ንጉሡ ጥላሁን ዛሬ ከሥልጣን የተገፉት በሆነ መድረክ ላይ የሕዝብን ሕመም የሚጋራ ንግግር አድርገው ካልሆነ በቀር ‹‹የአማራን ሕዝብ ባግባቡ እያገለገላችሁ አይደለም›› ተብለው አይመስለኝም፡፡
ያመኑበትን እውነታ ያለምንም ማቅማማት በመናገር እና ኪራይ ሰብሳቢነትን በመታገል የሚታወቁት አቶ ጸጋ አራጌና አቶ ዮሐንስም ተመሳሳይ እጣ ያጋጠማቸው ‹‹ለዙፋኔ እስከታመኑ ድረስ ቢሞስኑ ምን አገባችሁ›› ተብለው ካልሆነ በቀር በሥልጣናቸው ሲባልጉ ተገኝተው አይመስለኝም፡፡
ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን… በብልሹ ሥርዓት ውስጥ የሹመት እድገት የሚያገኙ አመራሮች መባረር ቀርቶ መታሰር የሚገባቸው ሲሆኑ የሚባረሩት ደግሞ የተሻሉት መሆናቸው እርግጥ ነው፡፡ በዚህም መሠረት አቶ ዮሐንስ ቧያለውን፣ አቶ ጸጋ አራጌን እና አቶ ንጉሡን ከሥልጣናቸው ያነሳው አካል በቅርቡ ደግሞ ጠባቂዎቻቸውን ማንሳቱን እየሰማን ነው፡፡
ከሕዝብ የሚነጥል ጥፋት ቢያገኝባቸው ኖሮ ዶክመንታሪ ሠርቶ ከማሰራጨት ወደኋላ የማይለው መንግሥት የፈጸሙት ጥፋት ከሕዝብ የሚቀላቅል መስሎ ስለታየው ከወንበርም አልፎ ወደ መቃብር ሊያወርዳቸው ድምጹን አጥፍቶ እየተሳበ ነው፡፡
ሆኖም ግን የማካቬሌ አስተምህሮ ‹‹ከሕዝብ ጉያ ሳታወጣ- ተቀናቃኝህን አትቅጣ›› የሚል ምክር የሚሰጥ በመሆኑ… ይሄን ተልዕኮ የወሰዱ ተላላኪዎችም እኒህ አመራሮች ከመንግሥት ጥርስ ውስጥ ባስገባቸው ጥፋት ፈንታ በሥልጣን ዘመናቸው የፈጸሙትንና በሕዝብ የሚታወቀውን ስህተት መንቀስ ጀምረዋል፡፡
እኔ ግን እልኻለሁ…
እንዲህ ያለው መንቻካ ክስ በትናንት ጥፋት ተጸጽተው ወደ ትክክለኛ ጎዳና ለመግባት የሚያስቡ ባለሥልጣናትን የሚያከስም መሆኑን አውቀህ እኒህን አመራሮች ከሥልጣናቸው ባለፈ ጠባቂዎቻቸውን እስከማንሳት ያደረሰውን ምክንያት ወይም ጥፋት እስክታውቅ ድረስ ጠባቂያቸው ሁን፡፡
#Share
14 335
ክርስቲያን ታደለ
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬
➔የተባ አንደበትና ብሩህ ጭንቅላት የተሰጠው፤
➔በድምጹ ለመረጠው ሕዝብ ድምጽ በመሆን ላይ የሚገኝ፤
➔በአማራ ሕዝብ ላይ የተደቀነው የሕልውና አደጋ መነሻውም ሆነ ማርከሻው አራት ኪሎ ግቢ ውስጥ እንደሚገኝ ተረድቶ በገብስ ገብሱ ፈንታ ነጭ ነጩን ማመላከት የጀመረ...
➔ ኢትዮጵያንም ሆነ አማራን ለመታደግ ዓላማን አውቆ እና ዒላማን ጠብቆ ተራራውን በጽናት መጋፈጥ እንጂ የሤራ ሊቆችን በመለማመጥና በዙሪያቸው በመርመጥመጥ የጥፋት ድግሳቸውን ማስቀረት እንደማይቻል የተገነዘበ፤
➔"ሕዝባዊ ስጋትን በመጣል- ግላዊ ምቾትን ማስቀጠል" የሚለው የእራስ ወዳዶች ፍልስፍና የማይገዛው፤
➔"የኔ" የሚላቸው ሰዎች በጥቅም ተደልለው ሲኮሰምኑ በትችቱ ማረም፣ ሲጀግኑ ደግሞ በአድናቆቱ ማፈርጠም የሚሻ ብርቱ ወዳጅ ያለው 😆
14 335
ጃልመሮና ደብረ ጽዮን የደህንነት መሥሪያ ቤቱ ባለሥልጣን ሆነው ቢሾሙ አቶ ተመስገን ጥሩነህ ካዘጋጁት ሰነድ የላቀ የዘመቻ እቅድ ጽፈው ፋኖ ላይ ሊዘምቱ አይችሉም።
ለአንድ መሪ ያለውን ታማኝነት ለመግለጽ ወገንን ማጥቃት እጅግ ይቀፍፋል‼️
14 335
ለአማራ ክልል ባለሥልጣናት
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬
ባለፉት ሰላሳ ዓመታት ይቅርና ከጥቂት ወራት በፊት በአማራ ሕዝብ ላይ ያደረሳችሁትን ግፍ ለመጻፍ ሳስብ ዘልዛላ ታሪካችሁ እረዝሞ ከሊዮ ቶልስቶይ መጽሐፍ በላይ ግዙፍ ገጽ ያለው ይሆንብኛል፡፡ ታላቁን ሕዝብ እንዴት እንዳዋረዳችሁት ሳሰላስል ፋኖን ለመመታት ማሰባችሁ ቀርቶ አመራር ሆናችሁ መቀጠላችሁ ያስገርመኛል፡፡
ቆይ እኔ እምለው…
➔የአማራን ሕዝብ እንደ ሕዝብ የሚያወድም ወራሪ ጦር ሲመጣ ሕዝቡን በዞን ከፋፍላችሁ፣ የድርጅታችሁን ገንዘብ ተከፋፍላችሁ፣ ለቤተሰቦቻችሁ እና ለእራሳችሁ የአውሮፕላን ትኬት ገዝታችሁ… ማምለጫ ቀደዳ ስትፈልጉ የነበራችሁ ጉዶች ዛሬ ላይ ፋኖን ለማጥፋት የሚያስችል ሰነድና እቅድ ለማዘጋጀት የበቃችሁት የአማራን ሕዝብ ምን ያህል ብትንቁት ነው?
➔የአማራ ወጣት የትጥቅ ጥያቄ ሲያቀርብ እንቢ ብላችሁ መጋዘን ሙሉ ጦር-መሣሪያ ለወራሪው ሃይል ጥላችሁ እንዳልሸሻችሁ… በክትክታ ዱላ ማርኮ የታጠቀን ፋኖ ትጥቅ ለማስፈታት የደፈራችሁት ስንት ዳብል ውስኪ ብትጠጡ ነው?
➔መከላከያ ሠራዊት ላይ ጥቃት ፈጽመው ነፍሱን እና ትጥቁን የሚቀሙ፣ የዙፋን ጥያቄያቸውን ንጹሐን በመግደል የሚገልጹ እልፍ አእላፍ አማጺያን ባሉበት ሁኔታ... ከሠራዊቱ ጎን ቁሞ አብሮ ሲሞት የነበረውንና ወደፊትም አብሮ ለመሠዋት የተዘጋጀውን ፋኖ ከመከላከያ ጋር ማጋጠም የፈለጋችሁት የአማራን ሕዝብ ምን ያህል ብትጠሉት ነው?
➔በክልሉም ሆነ ከክልሉ ውጭ የሚኖረው አማራ በኦ-ያኔ እና በሸኔ ከበባ ውስጥ ወድቆ እየተሰቃዬ ባለበት ጊዜ… ሌሎች አካባቢዎች ላይ ወረራ በሚፈጽሙና ንጹሐንን በሚያወድሙ ኃይሎች ፈንታ ክልሉን የመከላከል ተግባር ይዞ የተደራጀውን ፋኖ ለማክሰም የሚያስችል ሰነድ ተቀብላችሁ ለማስፈጸም የበቃችሁ ከትሕ-ኦነጎች ምን ያህል ገንዘብ ብትቀበሉ ነው?
➔ይሄስ የጥፋት እቅድ በፋኖ ላይ የተዘጋጀው የትኛውን ክልል ወርሮ ነው? የትኛውን የመንግሥት ሠራዊት አጥቅቶ ነው? የስንት ባለሥልጣናትን ሕይወት ነጥቆ ነው? የትኛው የአማራ ሕዝብ ‹‹ፋኖ ስጋት ስለሆነብኝ አጥፉልኝ›› ብሏችሁ ነው?
እርግጥ በፋኖ ሥም የሚንቀሳቀሱ አንዳንድ አጭበርባሪዎች በገዛ ሕዝባቸው ላይ አንዳንድ ጥፋት ሊፈጽሙ ይችላሉ፡፡ ሆኖም ግን በውጫዊ ኃይሎች የትጥቅ ድጋፍ ኢትዮጵያን የማፍረስና መንግሥትን የመገርሰስ ዓላማ አንግበው በምድሩ ላይ ከተቀፈቀፉት አማጺያን ጋር ሲወዳደር የእነዚህ ኃይሎች ጥፋት መከላከያን ለማዝመት ቀርቶ የአገርም ሆነ የመንግሥት ስጋት ሊሆን አይችልም፡፡ እናንተ ግን በአማራዎች ወንበር ላይ የተቀመጣችሁ የትሕ-ኦነጎች አሽከር በመሆናችሁ የምስራቅ አማራን ፋኖን በመምታት ታማኝነታችሁን መግለጽ ፈለጋችሁ፡፡
አንድ ነገር ልንገራችሁ…?
በአማራ ሕዝብ ላይ እንደ ሠራችሁት ወንጀል ቢሆን ኖሮ ፋኖ ነበር ሰነድ አዘጋጅቶ ወደ እናንተ መምጣት ያለበት፡፡ መከላከያ ሠራዊቱም ቢሆን ትናንት አብሮት ሲሞት ከነበረው ፋኖ ላይ በመተኮስ ፈንታ ‹‹በጓዶቼ ሞት ላይ ተደራድራችሁብኛል›› ብሎ እናንተን ነበር መውቀስ የነበረበት፡፡
በተረፈ...
ፋኖ ላይ የጀመራችሁትን ዘመቻ ተግባራዊ ማድረግ የምትችሉት የአማራን ሕዝብ ከሕልውና ስጋት ነጻ ያደረጋችሁ ቀን ብቻ ነው፡፡ ወይም ደግሞ መላው አማራን ማጥፋት የቻላችሁ ቀን ብቻ ነው፡፡ ከዚህ ውጭ ግን የምትጀምሩት እንጂ የምትጨርሱት ዘመቻ አይኖራችሁም፡፡ እናም ፋኖን ለማጥፋት የነደፋችሁትን እቅድ መሰረዝ ካልቻላችሁ ገመድ ሆኖ የእናንተ አንገት እንደሚሸመቀቅ ጥርጥር የለውም፡፡
14 335
በብአዴን ፍቃድና እገዛ በፋኖ ላይ እየተወሰደ ያለው የጥፋት እርምጃ ባፋጣኝ ይቆም ዘንድ እጠይቃለሁ። "የአማራ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ የፖለቲካ ድርጅቶችም ተቃውሟቸውን መግለጽ አለባቸው" እላለሁ።
14 335
አገር ማፍረስ የሚሻ ኃይል ሥልጣን በያዘበት ዘመን አማራ ሆኖ እንደ መገኘት ሕመም ነው። ድካምም ጭምር...‼️
➔ሰኞ-ትሕነግ ይዘምትብኻል።
➔ማክሰኞ- ኦነግ ይጨፈጭፍኻል።
➔ሮብ- ኦህዴድ ይወነጅልኻል።
➔ሐሙስ- ብልጽግና ሤራ ይጠነስስብኻል።
➔አርብ- አማራን የሚወነጅል ሪፖርት አምነስቲ አውጥቶ ያስነብብኻል።
➔ቅዳሜ- ጦርነቱን ሲመራ የከረመው መንግሥት ሪፖርቱን መቀበሉንና እርምጃ ለመውሰድ መዘጋጀቱን ይነግርኻል።
➔እኁድ- አንዱ ቦታ ላይ ጥቃት ደግሰው ይጋብዙኻል።
ይህ ሁሉ ዘመቻ ታዲያ "የኢትዮጵያን ፍርሰት ለማቀላጠፍ ቀድሞ መመታት ያለበት ሃይል የቱ ነው?" ተብሎ ሲጠየቅ የአማራ ሕዝብ መልስ ሆኖ በመገኘቱ እንጂ የተለየ ኃጢያት ስላለበት አይደለም።
ምንም እንኳን የአማራ ሕዝብ ባሁኑ ሰዓት እራሱን እንጂ አገር መጠበቁን ያቆመ መሆኑን ያቆመ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያን ለማፍረስ የተስማሙ ውጫዊና ውስጣዊ ኃይሎች ግን "የሩዋንዳን እልቂት አማራ ላይ ሳንፈጽም አንገነጥልም" በሚል አቋም 24/7 ጥቃት መደገሳቸውን ቀጥለዋል።
ግን እያንዳንዱን ጥቃት ተቋቁመን እንደምናልፈው አልጠራጠርም‼️‼️
14 335
የሰሞኑን የአብን መግለጫ ማለፊያ ነው። ግን ከዚያ ባለፈ መልኩ ከመንግሥት ተነጥሎ መውጣትና ከፍተኛ ትግል ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።ነገ ከትሕነግ ጋር መሥራት ሲጀምር ከመገፍተር አሁኑኑ ፍቺ መፈጸም ይበጃል።
14 335
የእስክንድርን ቃለ-መጠይቅ በግርምት ውስጥ ሆኜ ተከታተልኩት።
ጋዜጠኛው በብዙ ነገሮች ነጥብ ሊያስጥለውና ከሕዝብ ጋር ሊያጣላው ሞክሮ ነበር።
እስኬው ግን የሚገርም ብቃቱን እና እውቀቱን ብቻ ሳይሆን የአስተሳሰብ ከፍታውን ማሳየት ቻለ።
እሳት ሆኖ ቃለ-መጠይቁን የጀመረው ጋዜጠኛም እንደ በረዶ ቀዝቅዞ ፕሮግራሙን አጠቃለለ።
እናም እልኻለሁ...
የእስክንድርን አስተሳሰብ ማወቅ የምትሻ ሁሉ ፍረጃውን ትተህ ይሄን ቃለመጠይቅ እንዲትመለከት ጋብዤኻለሁ።
14 335
በርካታ ንጹሐን በተጨፈጨፉበት እለት ጋዜጠኞችን እና ሚዲያዎችን ሰብስቦ ለማሳ ጉብኝት የሚወጣው "የኦሮሚያ ብልጽግና" ድምጽ አልባ ጭፍጨፋን በማመቻቸቱ ሊወገዝ ሲገባው አሚኮን ሲዘልፍ ማየት ያስገርማል።
ለማንኛውም ግን የአማራ ብልጽግና ድምጹን በማጥፋት ፈንታ ተገቢውን መልስ መስጠት ወይም ደግሞ የጌቶቹን መግለጫ Share በማድረግ ስምምነቱን መግለጽ ይጠበቅበታል።
14 335
የኦሮሚያ ብልጽግና መግለጫ‼️
አሳዬ ደርቤ
➔እጅግ አደገኛ በሆኑ ግጭት ቀስቃሽ ቃላቶች የታጨቀ፤
➔ጽንፈኝነትን በማውገዝ ጀምሮ- ጽንፍ በያዘ ዛቻ የተጠናቀቀ፤
➔በስሜትና በግንፍልተኝነት የተሞላና ከኃላፊነት መንፈስ ሙሉ በሙሉ የራቀ፤
➔በአማራ ክልል የምትገኘውን አውራ ጎዳና ቀበሌን ወደ ኦሮሚያ ክልል የወሰደ፤
➔ቁጣውን ለሕዝብ አከፋፍሎ ‹‹የአማራ ጽንፈኞች ከክልላችን ገብተው የፈጸሙት ጥቃት መላው ሕዝባችንን አስቆጥቷል›› በሚል ድምዳሜ የእርስ በእርስ እልቂት መለኮስን የወደደ፤
➔የአማራ ጽንፈኛ ከሚለው ሃይል በተጨማሪ በአማራ ብልጽግና እና በክልሉ ሚዲያዎች ላይ የቁጣ መዓት ያወረደ፤
➔የኢሰመጉ መግለጫን እና እውነትን በካዴ መልኩ ‹‹የአማራ ጽንፈኞች ከክልሌ ገብተው ጥቃት ፈጽመዋል›› በሚል ክስ ምንጃር ሸንኮራ ገብቶ የአማራ ገበሬዎችን ለመምታት ያቀደ…… እጅግ አደገኛ መግለጫ ነው፡፡
ከሁለት ወር በፊት ከ200 በላይ አማራዎች በወለጋ ሲገደሉ ቁጣውን ቀርቶ ኀዘኑን በወጉ መግለጽ የተሳነው አካል… ዛሬ ላይ ዛቻውን እና የጥፋት እቅዱን ይዞ እንዲመጣ ያስገደደው ምክንያትም… ሰለባ ይሆን ዘንድ የፈረደበት የአማራ ሕዝብ በአገር ሥም ለብልጽግና ወንበር በመታገልና በየስፍራው በመገደል ፈንታ እራሱን መከላከል መጀመሩ ነው፡፡
ስለሆነም የአማራ ጉዳይ የሚገደን ኃይሎች ሁሉ በተረኝነት እና በዘረኝነት መሃከል የሚወዛወዘው ይህ ሥርዓት በተግባሩም ሆነ በንግግሩ ውስጥ የሚያስተላልፋቸው መልዕክቶች ሁሉ የሮዋንዳን እልቂት የመድገም እቅድ መኖሩን የሚገልጹ ስለሆኑ... ሕዝባችን እንዲጠነቀቅ ከማድረግ ባለፈ እያንዳንዱን እንቅስቃሴያቸውን ለዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ማሳወቅ ግድ ይለናል፡፡
#Share
14 335
ስለ ብልጽግና ሳስብ:-
ከኢትዮጵያ አስከሬን ውስጥ የሆነች ሕጻን የማዋለድ እቅድ ይዞ በፕሮግራም የሚንቀሳቀስና.... ይሄንንም ሕልሙን ለመፈጸም የሚያስችል ምቹ ሁኔታ ፈጥሮ በጨረሰ ማግስት "ተገረሰሰ" በሚል ሥም ''ኦነግ ሸኔ' ሆኖ የሚከስም ይመስለኛል።
አብዛኞች እንደሚሉት "ልፍስፍስ መንግሥት" ሳይሆን አገር የማፍረስ ዓላማ ያለው "ጠንካራ ድርጅት" ሆኖ ይታየኛል፡፡
እናም ‹‹ይበቃኻል›› በሚል አቋም አገር ለማትረፍ የሚጥሩ ሃይሎችን እያከሰመ ‹‹ተዳክመኻል›› በሚሉት ነቃፊዎቹና ደጋፊዎቹ ላይ "ክክክክክክ" እያለ ሲስቅ ይሰማኛል። 😁
14 335
ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ የገባውን መከላከያ ሠራዊት አስወጥቶ የክልል ልዩ ሃይል ማከማቸት ያስፈለገበት ምክንያት ምን ይሆን? ብልጽግና ሆይ የደገስከው ፕሮጀክት ለማንም ስለማይበጅ ብትተወው ይሻላል!
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
