cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

የሻሸመኔ ደ/አርያም ቅ/አርሴማ እና ቅ/መርቆርዮስ ሰ/ት/ቤት

✟✟✟

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
1 490
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-107 أيام
-4430 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

🍁🍁የሲኦል እና የገሀነመ እሳት ልዩነት በአጭሩ 🍁🍁🍁ሲኦል ÷ የነፍስ ጊዜአዊ ማቆያ ነው ። የዓለም ፍፃሜ እስኪሆን ድረስ በምድር ላይ ከ ሕገ እግዚአብሔር ርቀው ፣ በሐጥያት እና በበደል ያሳለፉ ሰዎች ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ ስጋቸው ወደ መቃብር ነፍሳቸው በሲኦል ትቀመጣለች ፣ ትቀጣለች ። 🍁🍁🍁ገሀነመ_እሳት ደግሞ ÷ ከምፅአት( ከፍርድ ቀን) በኃላ በበደል ያሳለፈች ነፍስ እስከ በሌለው ፍርድ ለዘላለም የምትቀጣበት አስፈሪ ስፍራ ነው ። አሁን ሰው በሞተ ስጋ ሲለይ በሐጥያት አሳልፎ ከሆነ ነፍሱ እስከ እለተ ምፅአት ( የፍርድ ቀን) ድረስ እየተቀጣች የምትቀመጠው በሲኦል ነው ። ገሀነመ እሳት ፍርድ ቀን የሚመጣ ነው ። ከምፅአት ( ከፍርድ ቀን) በኃላ ግን የተበተነው ፣ የበሰበሰው ስጋ ተነስቶ ወንድ የ30 ሴት የ15 ዓመት ሆነው በሲኦል የነበረችው ነፍስ ከተነሳው ስጋ ጋር ተዋህዷ ነፍስም ስጋም አንድ ላይ በዘላለም ፍርድ በእሳት ቅጣት የሰው ልጅ ይኖራል ። ሁሉን ማስተካከል የሚቻለው በምድር እያለን በሞተ ስጋ ከዚህ ዓለም ሳንሔድ ብቻ እና ብቻ ነው ። የገሀነመ እሳት ሁኔታ ምን ይመስላል ÷ እሳቱ የማይጠፋ ፣ ትሉ የማያንቀላፋ በቁማችን የሚበላን ፣ ሰይጣን እና መልዕክተኞቹ የሚሰለጥኑብን ( የፈለጉትን የሚያደርጉብን) ......... ይሆናል ልዑል እግዚአብሔር ይህን ስፍራ እንዳናይ ይርዳን አሜን።
إظهار الكل...
👍 1
🍁🍁የሲኦል እና የገሀነመ እሳት ልዩነት በአጭሩ 🍁🍁🍁ሲኦል ÷ የነፍስ ጊዜአዊ ማቆያ ነው ። የዓለም ፍፃሜ እስኪሆን ድረስ በምድር ላይ ከ ሕገ እግዚአብሔር ርቀው ፣ በሐጥያት እና በበደል ያሳለፉ ሰዎች ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ ስጋቸው ወደ መቃብር ነፍሳቸው በሲኦል ትቀመጣለች ፣ ትቀጣለች ። 🍁🍁🍁ገሀነመ_እሳት ደግሞ ÷ ከምፅአት( ከፍርድ ቀን) በኃላ በበደል ያሳለፈች ነፍስ እስከ በሌለው ፍርድ ለዘላለም የምትቀጣበት አስፈሪ ስፍራ ነው ። አሁን ሰው በሞተ ስጋ ሲለይ በሐጥያት አሳልፎ ከሆነ ነፍሱ እስከ እለተ ምፅአት ( የፍርድ ቀን) ድረስ እየተቀጣች የምትቀመጠው በሲኦል ነው ። ገሀነመ እሳት ፍርድ ቀን የሚመጣ ነው ። ከምፅአት ( ከፍርድ ቀን) በኃላ ግን የተበተነው ፣ የበሰበሰው ስጋ ተነስቶ ወንድ የ30 ሴት የ15 ዓመት ሆነው በሲኦል የነበረችው ነፍስ ከተነሳው ስጋ ጋር ተዋህዷ ነፍስም ስጋም አንድ ላይ በዘላለም ፍርድ በእሳት ቅጣት የሰው ልጅ ይኖራል ። ሁሉን ማስተካከል የሚቻለው በምድር እያለን በሞተ ስጋ ከዚህ ዓለም ሳንሔድ ብቻ እና ብቻ ነው ። የገሀነመ እሳት ሁኔታ ምን ይመስላል ÷ እሳቱ የማይጠፋ ፣ ትሉ የማያንቀላፋ በቁማችን የሚበላን ፣ ሰይጣን እና መልዕክተኞቹ የሚሰለጥኑብን ( የፈለጉትን የሚያደርጉብን) ......... ይሆናል ልዑል እግዚአብሔር ይህን ስፍራ እንዳናይ ይርዳን አሜን።
إظهار الكل...
ቅኝት = ዋኔን
إظهار الكل...
👍 1
☝️☝️☝️☝️☝️ #አውደ_መጻሕፍት 👇👇👇👇👇
إظهار الكل...
🛑የሰላሳ አመታት /30/ የሰማዕትነት ጉዞ። ▪ለታሪክም አስቀምጡት። 🛑አንብቡት ይጠቅማችኋል በምን አይነት መከራዎች ውስጥ አልፈን እኛ እና ቤተክርስቲያን ለዛሬ እንደበቃን ትቃኙበታላችሁ።
إظهار الكل...
Repost from National Lottery et
✔️እንኳንንንን ደስስስስ አላችሁ👇👇👇 ብሄራዊ ሎተሪ ለባለ ዕድለኞች አስደሳች ዜና ይዞ መጥቷል የኢትዮጲያ ብሄራዊ ሎተሪ የማህበረሰቡን የቤት እጦት እና ፍላጎት በመገንዘብ ከEthio Telecom ጋር በመተባበር፣ #100_ሚሊዮን_ብር በመመደብ #ሚያዚያ 27/2016 በፋሲካ እለት የሚጠናቀቅ ልዪ የሆነ "ቤተሰባችንን ይቀላቀሉ " ፕሮግራም አዘጋጅቷል። የኢትዮ ቴሌኮምና ብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር በወሰነው መሰረት  ድርጅታችን በቴሌቪዢንና በሬድዮ ለማስታወቂያ ይመድበው የነበረውን በጣም ከፍተኛ ገንዘብ በመቀነስ የቴሌግራም ቻናል በመክፈት ራሱን እያስተዋወቀ ይገኛል!! ቴሌግራም ገፃችንን ብዙ ተከታይ እንዲያገኝ (ሼር) ላደረጉ ተከታዮቻችን 1ኛ እጣ ባለ 3 መኝታ ለ 25 ዕድለኞች 2ኛ እጣ ባለ 2 መኝታ ለ 25 ዕድለኞች 3ኛ እጣ ባለ 1 መኝታ ለ 50 ዕድለኞች እና ቀጥሎ ላሉ 200 እድለኞች የ1 አመት ያልተገደበ የኢንተርኔት አገልግሎት ሽልማት ይኖረዋል፡፡ አሁንስ ምን ይጠብቃሉ ሊንኩን ተጭነው ከገቡ በኃላ፣ ይህን ፅሁፍ ለ40 እና ከዛ በላይ ለሆኑ ወዳጅ ጓደኛችዎና ግሩፓች ላይ ሼር ፎርዋርድ ሲያደርጉ፣ የመሸለም እድሎ የሰፋ ነው። ይህን የማይገኝ አጋጣሚ በከንቱ እንዳያሳልፉ አሁኑኑ ሼር ፎርዋርድ ያድርጉ ፡፡ ከ40 በላይ ሼር ማረጋችሁ የመሸለም እድላችሁን ያሰፋዋል ልብ ይበሉ ❗️ ሼር አድርገው ሲጨርሱ ከታች ባለው ቦት ላይ 👇👇            @Abs_Ethiopiabot          @Abs_Ethiopiabot     Start በማለት የሽልማቱን ቀን ይጠባበቁ በኮምፒውተር እጣ አወጣጥ መሠረት #ሚያዝያ 27/2016 በትንሣኤው እለት ተሸላሚ ባለ ዕድለኛዎችን በ ቴሌግራም ቻናላችን የምንገልፅ ይሆናል መልካም እድል ከ ብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር @NATIONAL_LOTTERYET @NATIONAL_LOTTERYET ♻️ ሼር ሲያረጉ እኛ ደሞ እንሸልሞታለን!!
إظهار الكل...
👍 2
“ ኑሮ ከብዷት ነው ! ” ኑሮ ከብዷቸው ራሳቸውን ለማጥፋት ትልቁ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ታወር ጫፍ የወጡ አንዲት እናት በሕይወት ተረፉ። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ ጫው ካሬ ቀበሌ ወይሶ ሰፈር ጥር 21 ቀን 2016 ዓ/ም፣ ባለትዳርና የሁለት ልጆች እናት  ወ/ሮ ሂሩት በቀለ “ራሳቸውን ለማጥፋት” ረጅሙ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ታወር ጫፍ ላይ ወጥተው እንደነበር ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከወረዳው ባለስልጣን ማረጋገጥ ችሏል። ጉዳዩን በተመለከተ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ እንዲሰጡ የተጠየቁት በክልሉ ወላይታ ሶዶ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ የኮሚኒኬሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተመስገን አስራት ፣ “ ማክሰኞ ዕለት (ጥር 21 ቀን 2016 ዓ/ም) የመብራት ፖል ጫፍ ላይ ወጥታ፣ አውቶማቲክ ስለሆነ በራሱ ጊዜ ዘጋና ጠቆማ ሰጠን (ሰው ወደ ላይ እየወጣ እንደሆነ)፣ ከዚያ ከወረዳ ቲም ተዋቅሮ ፓሊስ፣ የወረዳው አመራርና የቀበሌ አመራር አንድ ላይ በመሆን ወደ ስፍራው ደርሰው ሴትዮዋ ጋ ሲደርሱ ጫፍ  ላይ ወጥታ ነበር ” ብለዋል። “ አንድ ላይ በመሆን እንድትወርድ ሰዎች ለምነው ነበረ፣ ‘አልወርድም’ ብላ በጣም አስቸግራ ነበር” ያሉት አቶ ተመስገን፣ “ሌሎቹ ሰዎች ተደብቀው ፓሊስ፣ የሴትዮዋ እናትና አባት አንድ ላይ ሆነው በመለመን ወረደች ” ሲሉ አስረድተዋል። ወ/ሮ ሂሩት እንዲህ ያደረጉት ለምን እንደሆነ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ አቶ ተመስገን፣ “ ኑሮ ከብዷት ነው። የሁለት ልጆች እናት ናት። ኑሮ ከብዷት ከባለቤቷ ሁሉ ተጣልታ ከቤተሰቦቿ ጋ ነች። እናትና አባቷ ጋ ሆና ነው ይሄ ክስተት የተፈጠረው ” ብለዋል። ሴትዮዋ ሕመምተኛ ስለሆኑ ከወረዱ በኋላም ሶዶ ኦተና ሆስፒታል ሕክምናቸውን እየተከታተሉ እንደሚገኙ ገልጸዋል። መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው ለጊዜው በወላይታ ሶዶ የሚገኘው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው። @tikvahethiopia
إظهار الكل...
ይድረስ እንደኔ ለተሸወዱ መፅሀፍ ቅዱስ የማያቃቸው እነሱ ግን በግድ አውቀዋለው የሚሉ ሴት ፓስተሪቶች ሴት ልጅ ባደባባይ ትሰብ ዘንድ መፅሀፍ ቅዱስ በፍፁም አይፈቅድም የሴት ፓስተርነት ይህ ፍፁም ኢ መፅሀፍ ቅዱሳዊ ነው ራሷን ሳትሸፍን እንደወንድ ሱሪ ታጥቀው ሲሰብኩ ሳይ እስቃለው ራስዋን ሳትሸፍን ሳትሸፍን ትንቢት የምትናገር ሴት ሁሉ ራሷን ታዋርዳለች !! እንደተላጨች ያህል ነውና 1ኛ ቆሮ 11_5 ይሄ ጥቅስ የሻራችሁት የብሉይ ጥቅስ አይደለም 🤭 ዳሩ ግን ማንንም ሊከራከር ቢፈቅድ እኛ እግዚአብሄር አብያተ ክርስትያናት እንዲ ያለ ልምድ የለም 1ኛ ቆሮ 11_16 ሴት እህቶቻይን የምትሰብኩት እንዲ ይላል ማቴዎስ 7:21-23 “በሰማይ ያለውን የአባቴን ፈቃድ ሳይፈጽም ‘ጌታ ሆይ፤ ጌታ ሆይ፤’ የሚለኝ ሁሉ ወደ መንግሥተ ሰማይ አይገባም። በዚያ ቀን ብዙዎች፣ ‘ጌታ ሆይ፤ ጌታ ሆይ፤ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን? በስምህ አጋንንት አላወጣንምን? በስምህስ ብዙ ታምራት አላደረግንምን?’ ይሉኛል። በዚያ ጊዜ፣ ‘ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንት ክፉዎች፤ ከእኔ ራቁ’ ብዬ በግልጽ እነግራቸዋለሁ።🤭ጉድ ፈላ እሺ የእግዚአብሄር ፍቃድ ምንድነው 👇👇 ሴት በነገር ሁሉ እየተገዛች በዝግታ ትማር ሴት ግን በዝግታ ትኑር እንጂ ልታስተምር ወይም በወንድ ላይ ልትሰለጥን አንፈቅድም 1ኛ ጢሞ 2_11_12 እና ምን እያልኩ ነው ሲስተር አንቺ አውቀዋለው ብለሽ የምትሰብኪው ኢየሱስ እሱ አያቅሽም ሼር እያደረጋችሁ አስመልጡ ምእመናን https://t.me/debre_aryam_kidest_arsema
إظهار الكل...
የሻሸመኔ ደ/አርያም ቅ/አርሴማ እና ቅ/መርቆርዮስ ሰ/ት/ቤት

✟✟✟

👍 2 2🥰 1👏 1
#ታቦት_በአዲስ_ኪዳን #ሼር_share ትምህርት ሃይማኖት (የሃይማኖት ትምህርት) በሁለት ይከፈላል፡፡ ይኸውም፦ 1ኛ፡- ዶግማ 2ኛ፡- ቀኖና በሚል ነው፡፡ ዶግማ፡- ቃሉ የግሪክ ሲሆን ፍችውም እምነት ማለት ነው፡፡ ቀኖና፡- ደግሞ ቃሉ የግሪክ ሲሆን ሥርዓት ማለት ነው፡፡ ከእነዚህ ከሁለቱ ዶግማ ወይም እምነት አይጨመርበትም፤ አይቀነስበትም፤ አይሻሻልም፤ ችግርና ፈተናም ቢመጣ እስከ ሞት ድረስ አጥብቀን የምንይዘው ነው፡፡ ለምሳሌ ያህል ይህን ዓለም ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ የፈጠረ፤ ቢመረምር እንጂ የማይመረመር ሁሉን ቻይ አምላክ፤ የሚሳነው ነገር የሌለ ፈጣሪ፤ የሰማይና የምድር ባለቤት የሠራዊት ጌታ ሕያው እግዚአብሔር ነው፡፡ እግዚአብሔር (ፈጣሪ) የአካል ሦስትነት አለው፡፡ በመለኮት፣ በመፍጠር፣ በሥልጣን፣ በአገዛዝ፣ በፈቃድ ግን አንድ ነው፡፡ በሦስትነቱ አብ፤ ወልድ፤ መንፈስ ቅዱስ ሲባል በአንድነቱ አንድ መለኮት አንድ እግዚአብሔር ይባላል፡፡ በአዳም ምክንያት ከመጣው የዘለዓለም ሞትና ከዲያብሎስ ባርነት ነጻ የወጣነው ከሦስቱ አካላት በአንደኛው አካል ማለትም በወልድ በኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ይህ ዶግማ ወይም እምነት ይባላል፡፡ ቀኖና ግን በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው ያደጉ ክርስቲያኖች የሚመሩበት ሥርዓት ስለሆነ፤ በሃይማኖት አባቶች ወይም በቅዱስ ሲኖዶስ አማካኝነት እንደጊዜው ሁኔታ የሚሻሻል በመሆኑ የሚጨመርበት፤ የሚቀነስለት ነው፡፡ ለምሳሌ ያህል እኛ ኦርቶዶክሳውያን የምንጠመቀው ሴት በሰማንያ ወንድ በአርባ ቀናችን ነው፡፡ የተወለዱ ሕጻናት ሴቷ ሰማንያ ወንዱም አርባ ቀን ሳይሞላቸው ቢታመሙና በሽታው አስጊ ከሆነ በ10፣ በ20፣ በ30…ቀናቸው መጠመቅ ይችላሉ ቀኖና ነውና፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን የቀዳስያን ብዛት መነሻው አምስት ነው፡፡ ምናልባት ከአምስቱ አንዱ፤ ሁለቱ፤ ሦስቱ ቢታጡና ሌላም ተፈልጎ እስከ መጨረሻ የማይገኝ ከሆነ ከአቅም በላይም የሆነ ችግር ከገጠመ ሁለቱ ወይም አንዱ ብቻ ቀድሰው ማቁረብ ይችላሉ፡፡ ቀኖና ነውና፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን ታቦት ሲከብር ቤተ ክርስቲያኑን የሚዞረው ሦስት ጊዜ ነው ችግር ካለ አንድ ጊዜ ብቻ ዑደት ተፈጽሞ ሊገባ ይችላል። ቀኖና ነውና፤ ስለቀኖና (ስለሥርዐት) ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክቱ እንዲህ ሲል ጽፏል። 1. ‹‹ነገር ግን ሁሉን በአግባብና በሥርዐት አድርጉ፡፡›› 1ኛ ቆሮ. 14፥40፡፡ 2. ‹‹ወንድሞች ሆይ በሠራንላቸው ሥርዐት ሳይሆን በተንኮል ከሚሄዱት ወንድሞች ሁሉ ትለዩ ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናዝዛችኋለን፡፡ እኛን ልትመስሉ እንደሚገባችሁ እኛም በእናንተ መካከል ያለ ሥራ እንዳልኖርን ራሳችሁ ታውቃላችሁ›› 2ኛተሰ. 3፥6-7›› ቀኖና (ሥርዐት) የሚወሰነው በሃይማኖት አባቶች እንደሆነና ወንጌልን የሚስተምር ሰው ለሚያስተምራቸው ክርስቲያኖች በሃይማኖት አባቶች የተወሰነ ቀኖና ማስተማርና መሰጠት እንዳለበት መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ሲል ያስረዳል፡፡ በየከተማውም ሲሄዱ፥ ሐዋርያትና ቀሳውስት በኢየሩሳሌም ያዘዙትን /የወሰኑትን/ ሥርዐት አስተማሯቸው፡፡ አብያተ ክርስቲያናትም በሃይማኖት ጸኑ ዕለት ዕለትም ቁጥራቸው ይበዛ ነበር፡፡›› ይላል የሐዋ. 16፥4-5፡፡ በዚህ የእግዚአብሔር ቃል መሠረት ቅዱስ ጳውሎስ ደርቤንና ልስጥራን በተባሉ ቦታዎች ለነበሩ ክርስቲያኖች ወንጌልን ከሰበከ በኋላ ሐዋርያት የወሰኑትን ቀኖና (ሥርዐት) እነደሰጣቸው እንረዳለን፡፡ ስለዚህ ቀኖና ወይም ሥርዐት ቤተክርስቲያንን ይጠቅማል እንጂ አይጎዳም፡፡ በመሆኑም ዶግማንና ቀኖናን ወይም እምነትንና ሥርዓትን ጎን ለጎን ይዞ መጓዝ ሐዋርያትን መከተል እንጂ ወደ ኋላ ተመልሶ አይሁድን መከተል አይደለም፡፡ እንግዲህ ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን የሚቃወሙ ሰዎች ሁሉ፤ የሚቃወሙት በቀኖና (በሥርዐት) የሚመሩትን ክርስቲያኖች ሳይሆን የእግዚአብሔር ቃል የሆነ መጽሐፍ ቅዱስን በመሆኑ እንዳይሳሳቱ አደራ እንላለን፡፡ አሁን እንግዲህ የዶግማንና የቀኖናን ልዩነት ከተረዳን በቀጥታ ወደ ታቦቱ ጥያቄ እንሄዳለን፡፡ ጥያቄ፡-1 ዛሬ በእኛ ቤተክርስቲያን ያለው ታቦት ነው? ወይስ ጽላት በታቦትና በጽላት መካከል ልዩነት አለና፡፡ መልስ፡- ታቦት የጽላት ማደሪያ ነው፡፡ ዘዳ 40፥20፡፡ ጽላት ደግሞ ቅዱስ ቃሉ የተጻፈበት ሰሌዳ ማለት ነው፡፡ ዘዳ 34፥27-28፡፡ ስለዚህ እነዚህ ሁለት ነገሮች ዛሬም በሐዲስ ኪዳን አሉ። ሆኖም ግን አሠራሩ ሙሉ በሙሉ በዘጸ 25፥10-18 ያለውን የሙሴን ሕግ የተከተለ አይደለም፡፡ ምክንያቱም፤ 1ኛ፡- ታቦት እንደሙሴ ሕግ የሚዘጋጀው ከግራር እንጨት ሆኖ ርዝመቱ ሁለት ክንድ ተኩል፤ ወርዱም አንድ ክንድ ተኩል ቁመቱም አንድ ተኩል ይሁን ይልና በውስጥና በውጭም በጥሩ ወርቅ ለብጠው፤ በዙሪያውም የወርቅ አክሊል አድርግለት ይላል፡፡ ደግሞም ታቦቱን የሚሸከሙት ከወርቅ በተሠሩ መሎጊያዎች አራት ሰዎች እንደሆኑ እንረዳለን፡፡ በአጠቃላይ የብሉይ ኪዳን የታቦት አሠራር እጅግ ከባድ በመሆኑ በሁሉም ዘንድ አይቻልም ነበር፡፡ ምናልባት አንዳንድ የቤተክርስቲያን ፍቅር የነበራቸው ነገሥታትና ዛሬም ፍቅረ ቤተክርስቲያን ያላቸው አንዳንድ ምዕመናን ይችሉት እንደሆነ ነው እንጂ፡፡ 2ኛ፡- ጽላት፤ ጽላትም እንደሙሴ ሕግ ከሆነ መዘጋጀትና መጠረብ ያለበት ከከበረ ድንጋይ ነው፡፡ በአንድ ታቦት ውስጥም መቀመጥ ያለባቸው ሁለት ጽላቶች ናቸው፡፡ ዘዳ 34፥1፡፡ በአጠቃላይ እንደ ብሉይ ኪዳኑ ሕግና ሥርዐት ከባድ ነው፡፡ የብሉይ ኪዳኑ ሥርዐትም ለሐዲስ ኪዳኑ ሥርዓት ጥላ ሆኖ አልፏል፡፡ 2ኛ ቆሮ 3፥7-11 ፤ ቆላ 2፥17፤ ዕብ 10፥1፡፡ እንግዲህ እዚህ ላይ የሐዲስ ኪዳኑ ታቦትና ጽላት የብሉይ ኪዳኑን የታቦት አሰራርና ሥርዐት ጠንቅቆና ተከትሎ የማይሄድ ከሆነ፤ ይህ የብሉይ ኪዳኑን የታቦትና የጽላት አቀራረጽ ሥርዐት ጠንቅቆ ያልሄደ የሐዲስ ኪዳን ታቦትና ጽላት ከየት መጣ የሚል ጥያቄም ሳይነሳ አይቀርም፡፡ አንባብያን ሆይ በቀጥታ ወደ ጥያቄው ከመግባታችን በፊት በዚህ ጽሑፍ ዶግማ ላይ ስለዶግማና ቀኖና ማብራሪያ የሰጠነው ይህን ለመሰለው ጥያቄ እንዲጠቅም ነው፡፡ አሁን ወደ ሐዲስ ኪዳን ታቦትና ጽላት ስንሄድ ቁም ነገሩ እንደሚከተለው ነው፡፡ የሐዲስ ኪዳን የታቦትና የጽላት አቀራረጽም ሆነ አጠቃቀሙ የተወሰነውና የሚወሰነው በቀኖና ነው፡፡ ቀኖና ደግሞ እንደ ሁኔታው የሚሻሻል ነው፡፡ ሲቻል ይጨመርበታል ሳይቻል ደግሞ ይቀነስለታል፡፡ እንግዲህ በቤተክርስቲያናችን ቀኖና ካበረከታቸው ነገሮች አንዱ የሐዲስ ኪዳን የታቦትና የጽላት አቀራረጽንና አጠቃቀምን ነው፡፡ ስለዚህ በሐዲስ ኪዳን ታቦትን ለመቅረጽ የግራር እንጨት ባይገኝ በዘፍ 1፥31 ላይ ‹‹ እግዚአብሔርም የፈጠረውን (ያደረገውን) ሁሉ እጅግ መልካም እንደሆነ አየ›› ስለሚልና እግዚአብሔር የፈጠረውን ስለማይንቅ ከግራር ሌላ ከማይነቅዝ እንጨት መቅረጽ እንችላለን፡፡ ቁመቱ ወርዱና ዙሪያውም እንደችሎታችን ይሆናል፡፡ በውስጥና በውጭ ስለሚሆነው የወርቅ ክብርም እንደችሎታችን ይወሰናል፡፡ ከሌለንም ወርቁ ይቀራል ቀኖና ነውና፡፡ ስለጽላቱም እንደዚሁ ነው ከቻልን ከከበረ ድንጋይ፣ ከዕብነ በረድ መቅረጽ እንችላለን፤ ካልቻልን ጽላቱን ከማይነቅዝ እንጨት መቅረጽ እንችላለን፡፡ በሌላ በኩልም ከቻልን እንደ ብሉይ ኪዳኑ በአንድ ታቦት ሁለት ጽላት ማስቀመጥ እንችላለን፤ ካልቻን በአንድ ታቦት አንድ ጽላት ብቻ ይሆናል፡፡ በተጨማሪም የጽላቱን ማስቀመጫ ታቦት ባይኖረን ጽላቱን ታቦት ብለን በመጥራት በጽላቱ ብቻ መጠቀም እችላለን ቀኖና ነውና፡፡
إظهار الكل...
👍 2
ይሁን ብለን ብንጠቀምበት ስህተቱ ምን ይሆን? ጥያቄ3፡- የሰሎሞን ቤተ መቅደስ እስኪሠራ ድረስ በእርግጥ ታቦቱ ከቦታ ወደ ቦታ ይዘዋወር ነበር፤ ቤተ መቅደሱ ተሠርቶ ታቦቱ ወደ ቤተ መቅደሱ ከገባ በኋላ ግን ካህናቱ ታቦቱን ተሸክመው ስለመውጣታቸው መጽሐፍ ቅዱስ አይናገርም፡፡ ታዲያ ዛሬ ክርስቶስ ደሙን ካፈሰሰ በኋላ፤ በብሉይም ሆነ በሐዲስ ኪዳን መመሪያ ሳይኖር፤ ከየት አምጥታችሁ ነው ታቦትን በየጊዜው በማውጣት የክርስቲያኖች ህሊና ሁሉ ወደተሰቀለው ክርስቶስ መሆኑ ቀርቶ ወደ ታቦቱ የሆነው? መልስ፡- በብሉይ ኪዳን እንኳን አይወጣም ነበር ማለት አንችልም ምክንያቱም በችግራቸው ጊዜ ለችግራቸው መፍትሔ ያገኙ ዘንድ ከነበረበት ከድንኳኑም ቢሆን ያወጡት ነበርና ለምሳሌ፦ 1. በሙሴ ምትክ የተመረጠ ኢያሱ ሕዝበ እስራኤልን እየመራ ወደ ምድረ ርስት ሲሄድ ድንገት የዮርዳኖስ ወንዝ ሞልቶ ባገኘው ጊዜ ወንዙን ከፍሎ አሕዛብን ለማሻገር ከእግዚአብሔር በተነገረው መሠረት ካህናቱ ታቦቱን ከነበረበት ቦታ ተሸክመው ወደ ወንዙ በመሄድ ታቦቱን የተሸከሙት ካህናት እግር ወንዙን ሲረግጥ ወንዙ ተከፍሎ ሕዝቡ ሁሉ በሰላም መሻገራቸውን እናገኛለን፡፡ ኢያሱ 3፥1-17፡፡ 2. እስራኤል ምድረ ርስት በደረሱ ጊዜ ምድረ ርስት (ኢያሪካ) በጠላት እጅ በጽኑዕ ግንብ ታጥራ አገኟት፡፡ በዚህም ጊዜ ይህን የጠላት የግንብ አጥር ለማፍረስና ርስታቸውን በእጃቸው ለማድረግ እግዚአብሔር የገለጠላቸው ጥበብ ካህናቱ ታቦቱን ተሸክመው ሕዝቡም እየተከተሉ ሰባት ጊዜ ግንቡን እንዲዞሩት ነው፡፡ የታዘዙትን አደረጉ ግንቡም ፈረሰላቸው፡፡ ኢያሱ 6፥1-17፡፡ 3. እስራኤል ጠላት በበረታባቸው ጊዜ ጠላትን ለማሸነፍ ካህናቱ ታቦቱን ተሸክመው ይወጡ ነበር፡፡ 1ሳሙ 5፥1-ፍ፡፡ ስለዚህ በብሉይ ኪዳን ካህናቱ ታቦቱን ከቦታ ወደ ቦታ ሲንቀሳቀሱ ካልሆነ በቀር ለሚፈልጉት ዓላማ ታቦቱን ካለት ቦታ ተሸክመው አያወጡትም ነበር ማለት አንችልም፡፡ ሰሎሞን ቤተ መቅደሱን ሠርቶ ካስገባው በኋላ ቢሆንም ካህናቱ ታቦቱን ተሸክመው እንዳያወጡ የሚል ሕግም የለም፡፡ እግዚአብሔር የሠራው ሥራ በብሉይ ኪዳን የተፈጸመው አገልግሎት ሁሉ ሙሉ በሙሉ በመጽሐፍ ቅዱስ አልተጻፈም፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስም ያልተጻፈ ብዙ ነገር እንዳለ እናምናለን ከዚህ በመነሳት ነው እኛ በሐዲስ ኪዳን ታቦትን ተሸክመን የምናወጣው፤ በብሉይ ኪዳን በእግዚአብሔር ቸርነት (ትእዛዝ) ካህናቱ ታቦታቱን ተሸክመው እንዲወጡ ተደርጎ ካህናቱም ታቦታቱን ተሸክመው በመውጣት በታቦቱ ያደረ ኃይለ እግዚአብሔር ለሕዝበ እስራኤል ያደረገው ድንቅ ሥራ ለማሰብና እግዚአብሔርን ለማመስገን ነው፡፡ዛሬም ለሥጋና ለደሙ የክብር ዙፋን የሆነውን ቅዱስ ስሙም የተጻፈበትን ቅዱስ ታቦት በምናወጣበት ጊዜ በደሙ የባረከን መድኅነ ዓለም ክርስቶስ አሁንም የሥጋውና የደሙ ዙፋን በሆነው በታቦቱ ረቂቅ ኃይሎች በማስተላለፍ በረከቱን ያበዛልናል ብለን በማመን ነው፡፡ የተሰቀለው አምላክ መክበሩና መንገሡ ቀርቶ በየጊዜው ታቦት ወጣ እየተባለ ታቦቱ ብቻ ነገሠ ከበረ ሕዝቡም ወደ አምልኮ ባዕድ ኮበለለ ስለሚለው ግን አንድ ሕዝብ የንጉሡን ዙፋን ሲያከብርና ሲፈራ ንጉሡን ማክበሩና መፍራቱ እንደሆነ መዘንጋት የለበትም፡፡ እኛ የምናምነው ቅዱስ ስሙ የተጻፈበትን የክርስቶስ ሥጋና ደም የክብር ዙፋን የሆነውን ታቦት ማክበራችን በኪሩቤል ዙፋን የሚቀመጥ መድኅነ ዓለም ክርስቶስን ማክበራችን መሆኑን ነው፡፡ በታቦቱ ፊት መስገዳችንም በታቦቱ ለተጻፈው ለቅዱስ ስሙ ነው፡፡ በታቦት ፊት ለእግዚአብሔር ስም ይሰግዱ የነበሩ ኢያሱና የእስራኤል ሽማግሌዎች በረከት አገኙበት እንጂ አልተጎዱበትምና ነው፡፡ ኢያ 7፥6፣ ዘዳ 33፥10፡፡ በሐዲስ ኪዳንም ‹‹ድል ለነሣው ስውር መናን እሰጠዋለሁ፤ የብርሃን መጽሐፍንም እሰጠዋለሁ፤ በዚያ መጽሐፍ ውስጥ ላይ ከተቀበለው በቀር ማንም የሚያውቀው የሌለ አዲስ ስም ተጽፎበታል›› ራእ 217፡፡ ለዚህ ስም ደግሞ ጉልበት ሁሉ መንበርከክ እንደሚገባ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፤ ‹‹ይህም በሰማይና በምድር በቀላያትና ከምድርም በታች ያለ ጉልበት ሁሉ ለኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይሰግድ ዘንድ ነው። አንደበትም ሁሉ ኢየሱስ ክርስቶስ በእግዚአብሔር አብ ክብር ጌታ እንደሆነ ያምን ዘንድ ነው›› ፊልጵ 2፥10-11፡፡ በዚህ መሠረት ቅዱስ ስሙ በተጻፈበት ከነጭ ድንጋይ (ከዕምነ በረድ፣ከእንጨት) በተሠራው በጽላቱ ፊት ለቅዱስ ስሙ መስገድ ታላቅ የመንፈስ ጥበብ እንጂ ሞኝነት አይደለም፡፡ ምናልባት ስለታቦት፣ ስለጽላት ባለማወቅ ባጠቃቀሙ በኩል የሚሳሳቱ አባቶችን፤ እናቶችን ወንድሞችንና እህቶችን በተገቢው መንገድ ማስተማር ተገቢ ነው፡፡ ከዚህ በላይ ስለ ታቦት ከቤተ መቅደስ መውጣትና አለመውጣት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ከመሆኑም በተጨማሪ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሆኑ መታወቅ አለበት፡፡ ብዙዎች በሐዲስ ኪዳን ታቦትን ለመቃወም በኤር 3፥16፡፡ የተጻፈውን ጠቅሰው “በዚያ ዘመን ፦የ እስራኤል ቅዱስ እግዚአብሔር የቃል ኪዳኑ ታቦት እነኋት እያሉም በአፋቸውም አይጠሯትም ከእንግዲህ ወዲህ አይሿትም።” ተብሏልና ታቦት አያስፈልግም በማለት ያስተምራሉ፡፡ እንደተባለው ታቦት ብሎ መጥራት ካላስፈለገ በኤርምያስ 31፥34፤ ደግሞ “እያንዳንዱ ሰው ባልንጀራውን፣ እያንዳንዱም ወንድሙን፦ እግዚአብሔርን ዕወቅ ብሎ አያስተምርም” ተብሎ ስለተጻፈ እንግዲህ ሰው ሁሉ በየዘመኑ እግዚአብሔርን እንዲያውቅ ማስተማር አያስፈልግም ማለት ነዋ! ደግሞም ጌታችን በማቴ 28፥19 “እንግዲህ ሂዱና በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው አሕዛብን ሁሉ አስተምሩ” ብሎ መናገሩ ስህተት መሆኑ ነዋ! በአጠቃላይ እንዲህ ነው ብሎ ከመናገር አስቀድሞ በመጽሐፍ የተጻፈው ነገር ለምንና እንዴት ባለ ሁኔታና ጊዜ መጻፉን ማጥናትና መልእክቱን (ምስጢሩን) መመርመር ይገባል እንላለን፡፡ በመጨረሻ ግን በኢትዮጵያ ኦርቶኮክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የማርያም፣ የቅዱሳን፣የሰማዕታት፣ የመላዕክት ወዘተ…. ታቦት እየተባለ የተሰየመበት ምክንያቱና የዚህ ስያሜ ከየት ነው የመጣው ምንድን ነው የሚሉ ጥያቄዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ እርግጥ ነው፡፡ እንዲህ ተብሎ መሠየሙ በትንቢተ ኢሳይያስ 56፥46 በተገለጸው መሠረት የእግዚአብሔርን ሰንበቱን ለሚጠብቁ ደስ የሚያሰኘውንም ለሚመርጡ ቃል ኪዳኑንም ለሚይዙ ጃንደረቦች (ስለእግዚአብሔር መንግሥት ራሳቸውን ጃንደረባ ያደረጉ ቅዱሳን) ማቴ 19፥12 በእግዚአብሔር ቤትና በቅጥሩ የዘለዓለም መታሰቢያ እንደሚደረግላቸው የተገለጠ በመሆኑ ይህን አብነት በማድረግ ጌታ ሥጋው፣ ደሙ የሚከብርበት ሆኖ ለቅዱሳኑም መታሰቢያ ለማድረግ ነው፡፡ /መዝ 111፥7/ እንዲሁም የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነውና ምሳ 10፥7፡፡ በዚህ ምክንያት እንጂ በታቦታቱ የሚከብረው መድኃኒተ ዓለም ክርስቶስ መሆኑ ግልጽ ሊሆን ያስፈልጋል፡፡ እግዚአብሔር አስተዋይ ልቡና ይስጠን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን። /ምንጭ፦ ሐመር መጽሔት ሚያዝያ 1985 ዓ.ም/
إظهار الكل...
👍 1