Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ
الذهاب إلى القناة على Telegram
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ
تُعد قناة Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ (@tadeletibebu) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 52 631 مشتركاً، محتلاً المرتبة في فئة اخرى والمرتبة 510 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 52 631 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 02 ديسمبر, 2024، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 0، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 0، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 0%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً N/A% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 0 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 0 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 0.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“ማንኛውንም ሀሳብና አስተያየት በዚህ ሊንክ መላክ ይችላሉ @Tadeletibebut”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 03 ديسمبر, 2024) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة اخرى.
52 631
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
52 631
የራማው ገብርኤል ..እንዴት ነው የሚያምረው ባካችሁ። ጎንደር ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን 💚💛❤️
የራማው ልዑል
የአራርባብ አለቃ
ብርሃናዊ መላዕክ
የብስራት ባለቤት
የጽናት ሰባኪ
የምዱባን እረዴት
የእሳት ንዳድን ገዢ
በኪሩቤልና ሱራፌል ላይ የተሾምክ
በእግዚአብሔር ፊት ለመቆም የተመረጥክ
ባለ ሙሉ ግርማ መላኩ ቅዱስ ገብርኤል ሆይ
እኛም ያንተን መምጣት እንሻለን🙏
📸 Fanos picture
52 631
ወዳጄ ይህ የምትመለከተው በዛሬው ቀን በሁመራ ከተማ
የተመረቀው #የተከዜ_የሰላም_ዘብ ነው። ክብርህንም፣ ማንነትህንም ለማስጠበቅ ከዚህ ውጪ ምርጫ የለም።
52 631
በቀደም ዮሐንስ ቧያለው በምክርቤት እንደተናገረው ነው። በህመም ምክንያት እንደ ፊታውራሪ ገበየሁ ተክሌ ዘንግ ይዞ ያዋጋው ብ/ጄ ተፈራ ማሞ ህክምና ተከልክሎ፤ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ሲኦል ቢሆን እንገባለን ያሉት እንደ ፃድቃን ገብረ ተንሳይ ያሉት ደግሞ ያለምንም ከልካይ ከመቀሌ አዲስአበባ፤ ከአዲስአበባ ኒዮርክ በነፃነት ይመላለሳሉ። ኢትዮጵያ እንዲህ ነች። 86 ንፁሐንን ላስጨፈጨፈው ጃዋር ፍትህ ሰጥታ፤ እስክንድር ነጋን የምታሳድድ ጉደኛ ሀገር ናት። አቦይ ስብሃት ነጋን በነጻ አሰናብታ ከ12 ሺህ በላይ የዐማራ ተወላጆችን በአዲስአበባ ጉርኖ አፍና የያዘች ሀገር ናት ኢትዮጵያ።
እነዚህ ልጆች ልዩ ኃይሉን በማሰልጠን፣ በማደራጀትና በማዋቀር የነበራቸው ሚና ቀላል አይደለም። ምንም እንኳን አፍርሰው ቢበትኑትም አቅማቸው እስከፈቀደው ድረስ የአማራ ልዩ ኃይልን ለማቋቋም ደክመዋል፤ አሰልጥነዋል።ነገርግን ለዋሉት ውለታ ሽልማት እንኳን ባይሰጣቸው ያለምንም ፍትሕ ከጥምቀት እስከ ክረምት አስሮ ማሰቃየት ምን ይበላል?
ፍርድቤት ለይስሙላ ይቀርባሉ፤ ፍርድ ቤቱ ቀጠሮ እየሰጠ ይመልሳቸዋል። አሁንም ይቀርባሉ፤ ፍርድ ቤት ረዥም ቀጠሮ ሰጥቶ ይመልሳቸዋል። እንዲህ እንዲህ እያሉ እስካሁን አሉ። ፍርድ ቤት ለቀጣይ ሐምሌ 25 ደግሞ ቀጥሯቸዋል። ምንም ፍትሕ የሚባል የሌለበት ሾላ በድፍን የሆነ ነገር ነው።
በአሁኑ ሰዓት በጎንደር አንገረብ ማረሚያ ቤት ታስረው የሚገኙት፦
-ዮሴፍ አስማረ (ጆሲ)
-ማርሸት ዳሰው
-ጋሸው መንበሩ እና
-አንድነት ደመቀ ናቸው። በተለይ በሰንበት ቀን እየሄዳችሁ ጠይቋቸው፤ አንዳንድ ነገር ብናግዛቸውም በረከቱ ለኛ ነው። የታመመና የታሰረ የጠየቀ እንዲል ቃሉ።
52 631
#ሼር_ፖስት! በትግራይ ጉዳይ በውስጤ የቀረችው የተስፋ ጭላንጭል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ነበረች። ዛሬ ግን ስኡል ሚካኤል የጠጣውን ውሐ እየጠጡ ያደጉ የእፍኝት ልጆች የነበረችን ተስፋ አጨልመውታል። በይፋ ዛሬ ኦሮቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከሁለት ከፍለናል ብለው በደስታ እየቦረቁ ናቸው።
በጣም ይገርማል ባንዳነትና ሀገር ማፍረስ በትግራይ ቁምጣ ልክ ተሰፍቶ የተሰጠ ነው የሚመስለው። ሚካኤል ስኡል የሚባል የትግራይ ገዥ ዐፄ ኢዮአስን በማነቅ እንዲሁም ዳግማዊ ዮሐንስን በመርዝ በመግደል የጎንደርን ሥርዓተ መንግሥት አፍርሶ ዐማራውን ዘመነ መሣፍንት (Era of the princes) ለሚባል ስቃይና የባርነት (misery and slavery) ውስጥ እንዲዘፈቅ ምክንያት ሆኖ ነበር። ሚካኤል ስኡል ያፈረሰውን ሥርዓተ መንግሥት ከ60 ዓመት በኋላ መልሶ ያስተካከለው ዐፄ ቴዎድሮስ ነው። ቴዎድሮስ ከ30 በላይ ጦርነት አድርጎ ወደ አንድ ያመጣውን አንድነት መልሶ እንደገና ያፈራሰው ደግሞ ሌላኛው የትግራይ ሰው ዐፄ ዮሐንስ አራተኛ ነው።
ሚካኤል ስኡል እና ዐፄ ዮሐንስ የሚያመስሳለቸው ብዙ ነገር አለ። ሚካኤል ስኡል በታሪካችን ለመጀመሪያ ጊዜ ንጉሥን ያህል ሥልጣን ያለውን ዐፄ ኢዮአስን በስቅላት ገድሎ ሀገሪቱ እንደ አቡጀዲ ለብዙ ነገሥታት እና መሳፍንት እንድትቆራረረስ አድርጓል። ቀጥሎ ዕድሜው 70 ዓመት የሆነውን ዳግማዊ ዮሐንስን በ1762 ዓ.ም. በመርዝ አስገድሎታል። ሌላኛው ዐፄ ዮሐንስ አራተኛ ወደሥልጣን የመጣው ደግሞ ዳግማዊ ተክለ ጊዮርጊስን ዓይናቸውን በጉጠት አውጥቶ በመግደል እና የእንግሊዝን ጦር እየመራ አምጥቶ ዐፄ ቴዎድሮስን በማስገደል ነው።
ዛሬ ላይ በሀገሪቱ የጎሳ አወቃቀርን በመዘርጋት ስሁት ትርክት ፈጥረው፣ ለዚህ ማስፈጸሚያ ፓኬጅ ቀርጸው ዐማራው ስነልቦናዊ፣ ሰብዓዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ሥነ ብዕላዊ ቀውስ እና የዘር ማጥፋት ወንጀል እንዲፈጸምበት ያመቻቹት ሚካኤል ስኡል እና ዐፄ ዮሐንስ የጠጡትን ውኃ እየጠጡ ያደጉት ሕወሓቶች ናቸው።
ታሪካቸው በሙሉ ሲጠና፤
-ሀገር ማፍረስ፣
-መሬት መቁረስ፣
-ባንዳነት
-ሌብነት
ውሸትና ቅጥፈት ብቻ ነው።
ሕወሓትን የመሠረቱት በአብዛኞቹ ከፋሽስቶች ጎን ተሰልፈው ኢትዮጵያን የወጉ የባንዳ የልጅ ልጆች ናቸው። ለምሳሌ፣
ሀ~ የሽሬው ደጃዝማች አርአያ ገብረ እግዚያብሔር የጥሊያን ዋነኛ ባንዳ ነበር፤ የሕወሓቱ ኃየሎም አርአያ ልጃቸው ነው።
ለ~የአድዋው ደጃዝማች አስረስ ተሰማ የጥሊያን ዋነኛ ባንዳ ነበር፤ የሕወሓት ፈላጭ ቆራጭ የነበረው መለስ ዜናዊ የልጅ ልጁ ነው።
ሐ~ የአድዋው ደጃዝማች ተክሉ መሸሻ የጥሊያኖች ታማኝ አሽከር ነበር፤ የሕወሓት አለቃ የሆነው ስብሃት ነጋ አጎቱ ነው።
መ~የአድዋው ደጃዝማች ገብረ እግዚያብሔር አብርሃ በኢትዮጵያ ታሪክ በባንዳነት ስማቸው ከተዘረዘሩት መካከል አንዱ ነው፣ የሕወሓቷ ተጋደልቲ ሞንጆሪኖ ፈትለ ወርቅ አባቷ ነው።
እነዚህ የባንዳ የልጅ ልጆች በ1968 ዓ.ም. ትግል የጀመሩት ፀረ-እግዚአብሔር፣ ፀረ-ኦርቶዶክስ፣ ፀረ-ጽዮን እና ፀረ-ዐማራ በማለት ነበር። በማርክሲስም ሌኒኒዝም አስተህምሮ ሰክረው አምላክን በማውገዝ ነበር ትግል የጀመሩት። ታላላቅ የግሑሳን ባሕታውያን መሸሸጊያ፣ ለስውራን ቅዱሳን መናኸርያ፣ በብዙ ሺሕ ለሚቆጠሩ መነኮሳት፣ መነኮሳይያት እና መናንያን መጠጊያ፣ ለምእመናኑንም መማፀኛ እና ተስፋ የሆነውን የዋልድባ ገዳም የዘረፉ ደፋር ሌቦች ናቸው። በ1983 ወደሥልጣን ሲመጡ 4ኛውን ፓትርያርክ ብፁእ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ እንዲሰደዱ ያደረጉ ናቸው። በ1986 ዓ.ም. ባላቸው የዜማ እውቀትና ስነ ምግባር በሊቃውንቱ የሚወደዱና መመኪያ የነበሩት ሊቁ መሪጌታ እንደሥራቸው አግማሴን አፍነው ወደ ትግራይ በመውሰድ ደብዛቸውን ያጠፉ ናቸው።
አሁን ደግሞ የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንድነት ሆኖ እንዳይቃወማቸው ልክ እንደ ናዚ ፓርቲ ኩላዊት የኾነችውን ቤተክርስቲያን በዘውግ በመከፋፈል የመጀመሪያዎች ሆነዋል። በጀርመን ናዚ ፓርቲ አይሁድን ለመጨፍጨፍ ሲያስብ በሃይማኖት አንድ የሆኑ የጀርመን ፕሮቴስታንቶችን በመለያየት ነበር። ከአይሁዳውያን ጋር አንድ የሚያደርጋቸውን ሰንሰለት በጣጥሰው የራሳቸውንም የጀርመን ፕሮቴስታንት ቤተ ክርሰቲያን ከአቋቋሙ በኋላ ነው 6 ሚሊዮን አይሁዳውያን የተጨፈጨፉት።
በተመሳሳይ በሩዋንዳ ከጭፍጨፋው በፊት "የሁቱ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን" እና "የቱትሲ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን" በማለት የየራሳቸውን ቤተክርስቲያን አቋቁመው ነበር። የሁቱ ምእመናን እና የቱትሲ ምእመናን ተቀላቅለው አንድ ቤተክርስቲያን ውስጥ አብረው በጸሎት እንዳይቆሙ፣ ቱትሲዎች ወደ ሁቱዎች ቤተክርስቲያን እንዳይገቡ፣ ሁቱዎችም ወደ ቱትሲዎች ቤተክርስቲያን እንዳይሔዱ ከአደረጉ በኋላ ነበር የዘር ማጥፋት ወንጀሉ የተፈጸመው።
በኢትዮጵያም አሁን እያየን ያለነው ይሄንኑ ነው። ድንበር የሌላትን ኩላዊቷን ቤተ ክርስቲያን ወደ ክፍልፋይ (Denominations) አውርዶ ለመበታተን ሕወሓት፣ የትግራይ ቄሶች ከኦሮሞ ኤሊቶች ጋር በመተባበር መንገዱን ጀምረውታል። የትግራይ እና የኦሮሞ ቤተክርስቲያን በማቋቋም ቤተክርስቲያኗን ከመበታተን ባሻገር ሀገሪቱን ወደለየለት የእርስበርስ እልቂት ለማስገባት ሩጫቸውን አፍጥነውታል።
52 631
እዛ ከተራራው የወገብ መሃል በደን ተከባ የምታዪት ቤተክርስቲያን #ሳይኮ_ኪዳነምህረት ትባላለች። በደቡብ ጎንደር ዞን እብናት ወረዳ ትገኛለች። የተተከለችው ከሸዋ ቡልጋ በመጡት አባ መቅደሰ ክርስቶስ በ1587 ዓ.ም ነው። ወደግራ በኩል ዝቅ ብሎ ደግሞ የቆሎ ተማሪዎች ትምህርት ቤት ይገኛል። እፁቡ ድንቅ ነው🙏
52 631
እናመሰግንሻለን ምሳወይ አባተ🙏 እንደ ምሳወይ ያሉ ጋራና ሸንተሩን እያቆራረጡ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ህዝባቸውን የሚያገለግሉ አሉ። ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ደግሞ ቢሮ ወንበር ውስጥ ተቀምጠው ህዝቡን የሚያማርሩ አሉ። መኪና የሚገባቸው እንደ ምሳወይ በእግር እየተጓዙ ህዝቡን ለሚያገለግሉ ሆኖ ሳለ፣ አንድ ሰዓት እንኳን ቢሮ ቁጭ ብለው በትክክል ህዝቡን ማስተናገድ የማይችሉ ደግሞ ዘመናዊ መኪና ይዘው በጎርፍ ውሐ ረጭተውን ያልፋሉ።
ምሳወይ በአማራ ክልል በሰቆጣ ከተማ ከ17 ዓመት በላይ የጤና ባለሙያ ሁና አገልግላለች። "Global Citizen" ስለ ምሳወይ አባተ "This Health Worker Walks 6 Hours to Vaccinate Children in Ethiopia" በሚል ይዞት በወጣው ዘገባ፣ ምሳወይ ለህፃናት ክትባት ለመሥጠት የሰቆጣን አቀበትና ቁልቁለት፣ ተራራና ሸንተረር በማቆራረጥ 6 ሰዓት በእግሯ ትጓዛለች። በሰቆጣ ዙሪያ ባሉ መንደሮች ለህፃናት ክትባት ትሰጣለች። ህዝቧን ስለቤተሰብ ምጣኔ፣ ስለእርግዝና እና ስለጡት ማጥባት እና ስለተመጣጠነ ምግብ ታስተምራለች።
ነገም በጥዋቱ ተነስታ የክትባቱን ሳጥን በትከሻዋ በማንገት የቆቦ ሰንሰለታማ ተራሮችን ትወጣለች፤ ትወርዳለች። ወደ ወገኖቿ ለመድረስ በጣም አስቸጋሪ የሆኑ መልክዓ ምድርን ታቆራርጣለች። ከስድስት ሰዓት በላይ ትጓዛለች....ይህ ለ17 ዓመት የኖረችበት ሕይወቷ ነው።
በተለይም በጦርነቱ ምክንያት በሰቆጣና አካባቢው ከሦስት ዓመት በላይ ክትባት ተቆርጦ በመቆየቱ ከአስፈላጊም በላይ ሆኗል። ምሳወይ ለግሎባል እንደተናገረችው ጤናማ የነበሩ ህፃናት በጦርነቱ ምክንያት ተጎሳቁለዋል። በክትባት እጥረት ታመዋል። ክብደታቸው ቀንሷል። "እናም ደሞዜ ትንሽ ቢሆንም የእነዚህን ህፃናት ህይወት ለመታደግ በመሆኑ በሥራዬ ደስተኛ ነኝ። የኔ ትልቁ ክፍያ የህፃናቶችን ሕይወት መታደግ ነው" ትላለች።
እንግዲህ ኢትዮጵያ እንደ ምሳወይ የሚያገለግሏት አሉ። እንደማትነጥፍ ላም እያለቧት የሚኖሩም አሉ። ሀቀኛ ነጋዴዎች አሉ፤ ፣ ከተመኑ በላይ አንድን ዕቃ አስወድደው የሚሸጡም አሉ። ንፁህ ወተት የሚሸጡ አሉ፤ በወተቱ ላይ ውሐ ጨምረው የሚሸጡ አሉ። በተመሳሳይ በቅቤ ላይ ለውዝ፣ በዱቄት ላይ ሳጋቶራ፣ በማር ላይ ስኳር ጨምረው የሚሸጡ ለማኅበረሰቡ ጤና የማይጨነቁ አሉ። ከታሪፉ በላይ የሚያስከፍሉ ሹፌሮች፣ ጉቦ ተቀብለው በንፁሃን ላይ የሚፈርዱ ዳኞች፣ ገንዘብ ተቀብለው በሀሰት የሚመሰክሩ፣ የሥራ ቅጥር ሲወጣ ገንዘብ ተቀብለው የሚቀጥሩ አሉ።
እንደ ምሳወይ በማለዳ ተነስተው ለሥራ የሚጓዙ አሉ፤
ዘግይተው ወይንም ሰዓቱ ሳይደርስ ቀድመው ከቢሮ የሚወጡ አሉ። እንደ ምሳወይ ደሞዝ በቅጡ ሳይከፋላቸው ባልተመቻቸ ሁኔታ ማኅበረሰባቸውን እንደ ሻማ እየቀለጡ የሚያገለግሉ አሉ፣ በጆርጅ አርዌል "የእንስሳት እርሻ" ውስጥ እንዳሉት ባህርያት በሥልጣናቸው ህዝብን ከማግለል ይልቅ የሚባልጉ፣ለራሳቸው ምቾት የሚጨነቁ አሉ።
እኛ ግን እንደ ምሳወይ እና እንደሷ ላሉ ብርቱ ሠራተኞች ክብረት ይስጥልን እንላለን🙏
52 631
የቅዱስ ሚካኤል አመታዊ ንግስ እና የፃዲቁ ንጉስ ቅዱስ ላሊበላ የእረፍት መታሰቢያ በዓል በደብረ ሮሃ ቅዱስ ላሊበላ በዚህ መልኩ ተከብሯል። እንኳን አደረሳችሁ🙏
📸Menilk Farahun
52 631
አያት፣ አባትና ልጅ። መሀከለኛ ባያብል ምትኩ ይባላሉ አያቴ ናቸው። በቀኝ በኩል አባቴ ቄስ ጥበቡ ባያብል ናቸው። በግራ እኔ። አባቴ የአያቴ የመጀመሪያ ልጅ ነው። እኔ ደግሞ የአባቴ የመጀመሪያ ልጅ ነኝ። ፎቶው የዛሬ ሳምንት በካሜራ ያስቀረሁት ነው። አያቴ ትንሽ አመመኝ ብለው ህክምና ላሳያቸው ሲሙጡ ያስቀረሁት ፎቶ። በነገራችን አያቴ 85 አመት ሆኗቸዋል። እግዚአብሔር ይመስገን ይህን ያህል ግዜ ሲኖሩ ለመጀመሪያ ግዜ አመመኝ ብለው ህክምና የታዩት አንድ ግዜ ብቻ ነው። በዚህ ምርመራም ሙሉ ጤነኛ ናቸው ተብለው ተመልሰዋል።
አያቴ እጅግ ሲበዛ ሰው ወዳድ፣ ሰው አክባሪና በሀገሩ የተከበሩ፣ የሚጣላ አስታራቂ ልጆቻቸው በሥርዓት ያሳደጉ አባት ናቸው። ሴቷ አያቴም በሙሉ ጤንነት በህይወት አሉ።
ለአባቶቻችን እድሜና ጤና ይስጥልን🙏
