cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

Orthodox Wallpaper ✝✝✝

የኦርቶዶክስ የሆነ ለስልኮ ፎቶ ከፈለጉ ይህንን ቻናል ይቀላቀሉ ይህንን ቻናል ለኦርቶዶክስ ቤተሰብ በመላክ ይተባበሩን@orthdoxswallper

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
2 938
المشتركون
+1524 ساعات
+857 أيام
+58730 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

Photo unavailableShow in Telegram
#የኔ_ትውልድ_ባለውለታውን_ያሳክማል! "ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ ታሟል" ብዙዎቻችንን ወደ መንፈሳዊ መንገድ የመራን፣ በሐጢአት የገገረውን ዓለት ልባችንን በመንፈሳዊ መዝሙሮቹ ያቀለጠልን፣ ልንጠፋ ጫፍ ስንደርስ በሚስረቀረቅ ድምፁ የመለሰን፣ በአገልግሎቱ አዋጅ ነጋሪ የሆነ፣ መዝሙሩ ወደ ጸሎት ያደገለት ታላቁ አባታችን ሊቀ መዘምራን ኪነ ጥበብ ወልደ ቂርቆስ ሕክምና ይፈልጋል። ጠንካራ ቤተ ክህነት ቢኖረን ኖሮ ይህ የቤተ ክርስቲያን ባለውለታ መታከሚያ ባላጣ ነበር። ዳሩ ግን...ሆድ ይፍጀው። እኛ የመዝሙራቱ ተጠቃሚዎች ግን ባለውለታችንን አንተውም። ዘማሪ ኪነጥበብ ወልደ ቂርቆስን ለማሳከም እንቅስቃሴ ተጀምሯል። በዚህ ገጽ ቢያንስ 100,000 ብር እንሰብስብ። በሌሎች ገጾችም ዘመቻው ጀምሯል።  ባለውለታችንን ለማሳከም ፈቃደኛ የሆናችሁ በውስጥ መስመር @Teyaka_Lemtykebot ብር ያስገባችሁበትን ስክሪን ሹት እንድትልኩልን በትሕትና እንጠይቃለን። እነሆ በረከት! መርዳት የማትችሉ በማጋራት ተባበሩ። CBE 1000481007287 KINETIBEB W/KIRKOS W/MESKEL CMC Michael Branch
إظهار الكل...
🙏 6👍 3
Photo unavailableShow in Telegram
+ #የመንፈስ ቅዱስ ሙሽራ + እንደጨረቃ የደመቀች እንደከዋክብት ያበራች ማለት ፀርይተ ህሊና ፀርይተ ነብስ ፀርይተ ስጋ የተሰጣት በውስጥ በአፋ በነብስ በስጋ በቅድስና የተሸለመች የመንፈስ ቅዱስ ሰርገኛ የመንፈስ ቅዱስ ሙሽራ እንጂ የስጋ ሙሽራ ያይደለች ላንገቷ ማርዳ ለልብሶቿ ሽቶ የማትሻ ለጆሮዎቻ የጎልማሶችን ቃል የማትፈልግ ከመላእክት ቃል የተነሳ የምትፅናና በአይኗ መነፅር ያላሻት በመንፈስ ቅዱስ የብርሃን መነፅር ሦላሴን እያየች ለምልማ ጠግባ በመቅደስ ያደገችና የህይወት ፍሬን ዘመን በተፈጸመ ጊዜ ለተራቡ ወፎች አፍርታልን የተገኘች ቤቴልሔማዊት የህይወት እንጀራ እና መሶባችን እውነተኛይቱ ምርኩዝ ቅድስት ድንግል ማርያም በእውነት እሷን ባሰቡ ጊዜ ነብያት ከምርኩዛቸው ከሞታቸው ይፅናኑ ነበር ። (ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ ስለእመቤታችን ካስተማሩት ) #ኦርቶዶክሳዊ #አእምሮ
إظهار الكل...
👍 2
إظهار الكل...
$PRETON DROP

Preton community: @preton Preton community: @preton_cis Chat: @chat_preton Cooperation: @eleidans

👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
አምላኬ ሆይ ብዙ ነገር ተመኘው እነዛን ብዙ ነገር ባንተ እጅ ናቸውና የሚጠቅሙኝን አሳካልኝ የማይሆኑኝን አርቅልኝ! Share
إظهار الكل...
👍 14 8💯 3
9👍 4
Photo unavailableShow in Telegram
“#ቅዱስ_ያዕቆብ ዘሥሩግ እንዲህ አለ:- #በቅድስና_ውበት ስለተሞላችው ንጽሕት ትሕት እናገር ዘንድ አንደበቴ ብቁ አይደለም፡፡ ... የተራ ቀለማት መዋሐድ ለማይመጥኗት ለዚህች እጅግ ክብርት እንዴት ያለ ሥዕልን ልሣል? ውበትዋ ከእኔ መጠበብ በላይ ነው ፤ አእምሮዬም እንዲሥላት አልፈቅድለትም፡፡ #የድንግል_ማርያምን ክብርዋን ከመግለጥ ፀሐይን ከነብርሃንዋና ከነሙቀትዋ መሣል ይቀልላል፡፡ ምናልባት የፀሐይ ጨረር በሥዕል ሊቀመጥ ይችል ይሆናል፡፡ ስለ እርስዋ የሚነገረውን ነገር ግን አሟልቶ ለመስበክ አይቻልም፡፡ እርስዋን ከነማን ጋር መመደብ ይቻላል? ከደናግል ጋር? ከቅዱሳን ጋር? ከንጹሐን ጋር? ካገቡ ሴቶች ጋር? ከእናቶች ጋር? ከአገልጋዮች ጋር? እነሆ የድንግልናን ማኅተም ከወተት ጋር የያዘ ሰውነትዋን እዩ! መውለድዋንም ከታተመ ማኅፀንዋ ጋር እዩ! ከደናግል መካከል ናት ስል ሕፃን ይዛ ስታጠባ አያታለሁ! ከዮሴፍ ጋር ትኖራለች ስል በጋብቻ ቃልኪዳን እንዳልታሠረች አያለሁ! #ስለ_እርስዋ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል ፤ የክብርዋ ከፍታ ግን ያስቸግረኛል፡፡ ከቶ ምን ባደርግ ይሻለኛል? ስለ እርስዋ ለመናገር ብቁ እንዳልሆንሁ በግልፅ እናገራለሁ፡፡ ከፍቅር የተነሣ ግን ተመልሼ መናገር ያምረኛል፡፡... ሱራፌል ከእሳቱ የሚሸሸጉለትን የእርሱን ከንፈሮች በቡሩካን ከነፈሮችዋ የሳመች እርስዋ የተባረከች ናት! ዓለማት ሕይወትን የጠጡበትን ምንጭ እርሱን ያጠባች እርስዋ የተባረከች ነች’ (የብርሃን እናት ገፅ 352)              #_ሰናይ__ቀን @Mezmure_tewahdo
إظهار الكل...
6👍 2
Repost from ገዳማውያን
አያት ደብረ በረከት ቅድስት ማርያም ህንጻ ቤተክርስቲያን ግንባታዋ ተጠናቆ ግንቦት 17 እና 18 2016 ብፁዓን ሊቀነጳጳሳት በተገኙበት በድምቀት ይመረቃል። ገበናዬ ማርያም❤
إظهار الكل...
👍 5 3
20🙏 7🥰 4🤗 3👍 2
10🙏 4👍 3
Photo unavailableShow in Telegram
📌 ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ እንዲህ አለ ✍️ "በምሰብክበት ጊዜ ስታጨበጭቡልኝ ሰው እንደመሆኔ በዚያ ቅጽበት ደስታና መደነቅ ይሰማኛል ወደ ቤቴ ሔጄ ያጨበጨቡልኝ ሰዎች ምንም ጥቅም እንዳላገኙ ሳስብ ግን ንግግሬ ሁሉ በከንቱ እንደቀረ ይሰማኛል፤ ስለዚህ ማጨብጨባችሁን የሚከለክልና ዝም ብላችሁ እንድትሰሙኝ ብቻ የሚያደርግ ሕግ ስለማስቀመጥ አስባለሁ" (On His Message 80) ✍️“ቤት ውስጥ የእንግዳ ማረፊያ ቤት ይኑርህ አልጋ አዘጋጅ ጠረጴዛና መቅረዝም ይኑረው ክርስቶስ ሊመጣና ሊያርፍበት የሚችልበት ክፍል አዘጋጅና "ይህ የክርስቶስ ክፍል ነው" በል ምድር ቤት ያለ ትንሽ ክፍልም ቢሆን እሱ አይንቀውም፤ ዕርቃኑን የሆነው እንግዳ የሚፈልገው መጠለያ ብቻ ነው"  (On Acts Homily 40.2) ✍️ “ለሞቱት ብቻ አናልቅስ፤ በቆሙት ብቻም አንደሰት ታዲያ ምን እናድርግ? ለኃጢአተኞች በሞቱ ጊዜ ብቻ ሳይሆን በቁማቸውም እናልቅስ፤ ስለ ጻድቃን ደግሞ በቁማቸው ብቻ ሳይሆን በሞቱም ጊዜ ደስ ይበለን ምክንያቱም ኃጢአተኞች ቆመውም ሞተዋል፤ ጻድቃን ግን ሞተውም ሕያዋን ናቸው" (On Phil. 3) ✍️ "ጴጥሮስ አለቀሰ ማልቀስ ብቻ ሳይሆን ምርር ብሎ አለቀሰ፤ ከዓይኑ በፈሰሰው ዕንባ ድጋሚ ተጠመቀ አምርሮ በማልቀሱም በዕንባው ኃጢአቱን አጠበ አንተም እንዲሁ አድርግ" (Paent 3.4) ✍️“ንብ ከሌሎች እንስሳት ሁሉ ትከበራለች፤ የምትከበረው ታታሪ ሠራተኛ በመሆንዋ ሳይሆን የምትሠራው ለሌሎች በመትረፉ ነው" 📌ምንጭ ✍️ ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ግንቦት 12 2014 ዓ.ም
إظهار الكل...
❤‍🔥 17👍 4 2