cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

FIDEL POST NEWS

Fast news about Ethiopia

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
14 472
المشتركون
+6724 ساعات
+3367 أيام
+2 00030 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

ፖሊስ 89 ተጠርጣዎችን በቁጥጥር ስር አውሎ በተለያዩ ጊዜ የተሰረቁ በርካታ የመኪና እቃዎችን ማስመለሱን አስታወቀ በልደታ ፤በአራዳና በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አዋሳኝ ወረዳዎች  የመኪና እቃ በሚሰርቁ ፣ ህጋዊ የንግድ ፈቃድን ሽፋን በማድረግ የተሰረቀውን የመኪና እቃ ከሌቦች በሚቀበሉ በአጠቃላይ ወንጀሉን ተደራጅተው ሲፈፅሙ በነበሩ  ህገወጦች ላይ  በተወሰደ  እርምጃ 89 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል በተደረገ ምርመራ በልዩ ልዩ ጊዜ የተሰረቁ ከ1ሺ በላይ የሚሆኑ  33 አይነት የተለያዩ የመኪና እቃዎችን አስመልሷል፡፡ ፖሊስ የመኪና እቃ ስርቆትን ለመከለከልና ህገወጦችን ህግ ፊት ለማቅረብ ልዩ ልዩ ማስረጃዎችን በማሰባሰብ በተቀናጀ ኦፕሬሽን በተለምዶ ሱማሌ ተራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ህግን መሰረት አድርጎ በወሰደው እርምጃ 528 ልዩ ልዩ ፍሬቻዎችን ፣ 187 ስፖኪዮችን ፣ 113 የመኪና መብራቶች ፣ 172 የዝናብ መጥረጊያ  በአጠቃላይ 33 ልዩ ልዩ  1ሺ 269 አይነት የመኪና እቃዎችን መያዙን አስታውቋል፡፡  የተሰረቁ የመኪና እቃዎችን የሚገዙ እና የሚያሻሽጡ 89 ግለሰቦችንም በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ መቀጠሉን ገልጿል፡፡  የተሰረቁ የመኪና እቃዎችን የሚገዙ ህገ-ወጦች ለወንጀሉ መስፋፋት ዋና መንስኤ በመሆናቸው ፖሊስ በእነሱ ላይ የሚያደርገውን ቁጥጥር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡ የተሰረቀባቸውን እቃ ከወንጀለኞች  የሚገዙ ግለሰቦችም በተዘዋዋሪ ለወንጀል ፈፃሚዎች ምቹን ሆኔታ እየፈጠሩ መሆኑን ተገንዝበው ከዚህ ድርጊታቸው ሊታቀቡ እንደሚገባ  አዲስ አበባ ፖሊስ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡ በተለያየ ጊዜ የመኪና እቃ የተሰረቀባቸው ግለሰቦች በልደታ ፣  በአራዳና በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያዎቸው በመቅረብ  ንብረታቸውን መምረጥ እንደሚችሉም ፖሊስ አስታውቋል፡፡
إظهار الكل...
😁 1
በካዛክስታን ሴት አስከሬን ሲደፍር የነበረ የሬሳ ክፍል ሰራተኛ ተያዘ ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር የዋለው ሰውዬው ስልክ ሲሸጥ የእሱ እንደሆነ ለማረጋገጥ በገዢ ሱቅ ውስጥ የተቀጠረው ሰራተኛ የስልኩን የፎቶ እና የማህደር ሲያይ ሻጩ በርካታ የሴት ሬሳን ሲደፍር የሚያሳይ ነገር በማየቱ ነው። በመጣበት የፓውንስሾፕ ሰራተኞች ነው። የስልኩን ባለቤትነት ለማረጋገጥ ጋለሪውን እንዲያሳይ ተጠይቋል። ሰራተኞው ወዲያውኑ ለፖሊስ አሳውቆ የሬሳ ክፍል ሰራተኛውን ለፖሊስ አስይዞታል። እስከ 3 አመት እስራት የገንዘብ ቅጣት ይጠብቀዋል ሲሉ ሰሞኑን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
إظهار الكل...
👍 3😱 2
በአዲስ አበባ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ መፀዳጃ  ቤት ውስጥ እርድ ሲከናወን ተገኘ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምግብ እና መድኃኒት ባለስልጣን በአስራ አምስት ቀናት ውስጥ ከወረዳ እስከ ማዕከል የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በማከናወን ከ805 በላይ የሚሆኑ ተቋማት ላይ የቁጥጥር ስር መስራቱን አስታውቋል።በዚህም ባለስልጣኑ ባከናወነው የቁጥጥር ስራ ለ251 ተቋማት የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ሲሰጥ ሶስት ድርጅቶችን ማሸጉን አስታውቋል። ከታሸጉት  ተቋማት ውስጥ አንዱ  በፆም ወቅት አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን ህግ እና ደንብ በማይፈቅድ መልኩ መፀዳጃ ቤት ውስጥ በግ እና ፍየል እርድ ሲያከናውን መያዙ ተገልፆል፡፡ በተጨማሪም የባለስልጣኑ የብቃት ማረጋገጫ ሳይኖራቸው ፅዳቱን ያልጠበቀ ዶሮዎች ለሱፐርማኬት ሲያከፋፍሉ የተገኙ የስጋ ማቀናባበሪያ እና ሱፐር ማርኬት መታሸጋቸው ተገልፆል፡፡ በፍተሻው የተገኙት ምርቶች በአጠቃላይ የተወገዱ ሲሆን በኮልፌ፣በለሚ ኩራ እና በአራዳ ክፍለ ከተሞች ናቸው፡፡ በቀጣይ ቀናቶች የበዓል ወቅት በመሆኑ  ህብረተሰቡ ህገ ወጥ እርድ የሚያከናውኑ ተቆማቶች በሚመለከትበት ጊዜ በነፃ የስልክ መስመር 8864 ላይ በመደወል ለባለስልጣኑ ማሳወቅ እንዳለበት የባለስልጣኑ የምግብና የጤና ነክ ተቋማት ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ እስጢፋኖስ ጌታቸው  ተናግረዋል።
إظهار الكل...
👍 5👎 1
ትላንት ማታ በአቃቂ የገበያ ማዕከል በደረሰው ድንገተኛ የእሳት አደጋ 16 ሱቆች ሙሉ በሙሉ ተቃጥለዋል። ሚያዚያ  24 ቀን2016   ዓ.ም ምሽት 3:10 ሰዓት ላይ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ  ወረዳ 03 አቃቂ የገበያ  መዕከል በተነሳ የእሳት አደጋ 16 ንግድ  ሱቆች  ሙሉ በሙሉና በከፊል ተቃጥለዋል። የእሳት አደጋዉን  ለመቆጣጠር አምስት የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪ ሁለት የዉሀ  ቦቴ  ከ44 የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ጋር የተሰማራ ሲሆን እሳቱ ወደገበያ ማዕከሉ ተስፋፍቶ በሰዉና በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ መቆጣጠር የተቻለ ሲሆን አደጋዉን ለመቆጣጠር ሁለት ሰዓት ፈጅቷአል። በአደጋ መቆጣጠሩ ሂደት የፌደራልና የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት ከፍተኛ ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን በሰው  ላይ የደረሰ ጉዳት  የለም ። አቃቂ የገበያ ማዕከል ትንሹ መርካቶ እየተባለ የሚጠራ የገበያ ማዕከል ሲሆን ገበያ ማዕከሉ በከተማ ደረጃ ለእሳት አደጋ ተጋላጭ ተብለዉ ከተለዩ አንዱ ሲሆን በገበያ ማዕከሉ በተደጋጋሚ የእሳት አደጋ እያጋጠመ በንብረት ላይ ጉዳት ሲደርስ ቆይቷል። ኮሚሽን መ/ቤቱ ገበያ ማዕከሉ ለአደጋ የተጋለጠባቸዉን ዝርዝር ጉዳዮችን የመፍትሄ ሀሳቦችን አካቶ ለገበያ ማዕከሉ ማህበራትና ለሚመለከታቸዉ አካላት ያቀረበ ቢሆንም የማስተካከያ ዕርምጃዎች አልተወሰዱም። በመሆኑም በቀጣይ መሰል አደጋዎች እንዳያጋጥሙ መፍትሄ እንዲሰጥ ኮሚሽኑ አሳስቧል።
إظهار الكل...
👏 1
⚡️በካንሰር የሚሰቃየው አንድ የላኦሺያ ስደተኛ በአሜሪካ 1.3 ቢሊዮን ዶላር ፓወር ቦል ሎተሪ አሸንፏል። ገንዘቡን ካንሰሩን ለሚያከመው ለአንድ ጥሩ ሐኪም እንደሚያውለው እና ቤተሰቡንም እንደሚረዳ ተናግሯል።
إظهار الكل...
👍 13🥰 3🙏 3👏 1
2
በቻይና አንድ የ86 ዓመት አዛውንት የ81 ዓመት አዛውንት የመጀመሪያ ፍቅራቸውን አገቡ ከ60 ዓመታት በፊት ፍቅረኛሞች ነበሩ ። በመጨረሻም የትዳር ጓደኞቻቸው ሲሞቱ ሰሞኑ መጋባታቸውን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
إظهار الكل...
🥰 8👍 2
ምጥ ይዟት ወደ ሆስፒታል እየሄዱ የነበሩ ሶስት የአንድ ቤተሰብ አባላት እና አንድ ጎረቤትን ጨምሮ የ4 ሰዎች ህይወት በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የትራፊክ አደጋ መከላከል መረጃና ስታቲክስ ክፍል ኃረፊ ኢንስፔክተር ታምራት ደሳለኝ እንደገለፁት በሀዲያ ዞን ሾኔ ከተማ አስተዳደር ማዞሪያ ቀበሌ ሌሊት 11 ሰዓት 40 ከወላይታ ሶዶ ወደ አዲስ አበባ ይጓዝ የነበረ ፒካፕ መኪና በተቃራኒ አቅጣጫ ከሚጓዝ ባለሶስት እግር ባጃጅ ጋር ተጋጭቶ በውስጡ የነበሩ 3 የአንድ ቤተሰብ አባላት እና አንድ ጎረቤት በድምሩ የ4 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተናግረዋል። በ2 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ነው። ከሟቾቹ መካከል ምጥ ይዟት ወደ ሆስፒታል እያመራች የነበረች እናት እንደምትገኝበት ነው ኢንስፔክተር ታምራት የገለጹት። የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ መሆኑንም ኢንፔክተር ታምራት ጠቁመዋል።
إظهار الكل...
😱 8👍 4🥱 1
ዛሬ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክሃይማኖት መሪነት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም የሕፅበተ እግር ስነ ሥርዓት ተከናወነ። በስነ ሥርዓቱ ላይ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ ቆሞሳት ፣ ካህናትና በርካታ ምዕመናን ተገኝተው እንደነበር ከቤተክርስቲያኗ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተገኘው መረጃ ያሳያል። Photo Credit - TMC
إظهار الكل...
👍 15 3🙏 3👎 1