Mega Projects Construction Office
الذهاب إلى القناة على Telegram
ይህ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትልልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ መረጃ እና መልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
إظهار المزيد2 079
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-17 أيام
+930 أيام
أرشيف المشاركات
+1
በአዲስ ፈጠራ የተገነቡና ህዝብን ማዕከል ያደረጉ ፕሮጀክቶች
****
አሳታፊና ሁሉን አቀፍ የልማት ፕሮጀክቶች ቀጣይነት እንዲኖራቸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በትኩረት ይሰራል ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባዋ በአራት ኪሎ ፕላዛ የተገነቡ 73 የገበያ ማዕከሎች፣ 100 መኪናዎች ማቆም የሚችል የመኪና ማቆሚያ እና የታክሲ ተርሚናል አስመርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
በአዲስ ፈጠራ የተገነቡና ህዝብን ማዕከል ያደረጉ ፕሮጀክቶች በመዲናዋ በፍጥነት እና በጥራት እየተከናወኑ መሆኑን የገለጹት ከንቲባ አዳነች፤ የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማስፋት እና አዲስ አበባን ተወዳዳሪ ለማድረግ በቀጣይ በርካታ ሥራዎች ይከናወናሉ ብለዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ ጃንጥራር አባይ፥ በከተማዋ የሚገነቡ ፕሮጀክቶች የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው ብለዋል።
በሚከናወኑ ፕሮጀክቶች ላይ ህብረተሰቡ ለሚያደርገው ተሳትፎም ምክትል ከንቲባው አመስግነዋል።
+9
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዛሬው ዕለት መርቀው አገልግሎት ያስጀመሯቸው በአራት ኪሎ ፕላዛዎች :4ኪሎ የገበያ ማእከል እና የመኪና ማቆምያ ፕሮጀክቶች- በምስል
+2
ሁሉም ኢትዮጵያዊ ነገ ሀምሌ 24 ለተመሳሳይ አለማ በነቂስ ወጥቶ አሻራውን ያኖራል!
በነገው ዕለት ከማለዳው አስራ ሁለት ሰዓት ጀምሮ በአንድ ጀንበር 700 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ሁሉም ኢትዮጵያዊ ከያለበት በነቂስ ወጥቶ አረንጏዴ አሻራውን ያኖራል::
“በመትከል ማንሰራራት” የሚለውን መሪ ቃል አንግበን ህፃን አዋቂ ሳንል ሁላችንም ኢትዮጵያውያን እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ ተባብረን አሻራችንን እናኑር፡፡
አዲስ አበባ ከተማችንም በነገው እለት የችግኝ ተከላ መረሃ ግብር ቅድመ ዝግጅት አጠናቃለች::
+9
ከሁሉም በላይ የረዳን ፈጣሪ የተመሰገን ይሁን !
በ2017 በጀት አመት በ5 .2 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ የገነባናቸዉን 150 የትምህርት ፕሮጀክቶች መርቀን ለአገልግልሎት ክፍት አድርገናል ።
ፕሮጀክቶቹ በጥራትና ደረጃቸዉን ጠብቀዉ የተሰሩ 14 አዳዲስ ትምህርትቤቶች ፤ በ64 ነባር ትምህርትቤቶች ላይ ማስፋፋያ የተገነቡ 1655 የመማሪያ ክፍሎች ፣ የአይሲቲ ክፍሎች፣ ቤተ ሙከራዎች፣ የመመገቢያ አዳራሾች፣ ቤተ መፅሀፍቶች ፣ የስፖርት ሜዳዎች ፣ ምድረጊቢዎችን ፅዱ ፣ ዉብ የማድረግ ፣የመጸዳጃ ቤቶች እና የውሃ አገልግሎት ጨምሮ ለአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች እና መምህራን ምቹ የማድረግ ስራዎችን ያካተተ ነዉ፡፡
ትውልድን ለማነጽ በተሰራው ስራ አብራችሁን የሰራችሁትን በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም እያመሰገንኩኝ እነዚህ ትምህርትቤቶች የእናንተ እና የልጆቻችሁ ሀብት በመሆናቸው እንድትንከባከቧቸው አደራ እላለሁ፡፡
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ተካሄደ
ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት የሰኞ ማለዳ ከስራ ሰዓት መግቢያ በፊት የሚያዘጋጀውን የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር አካሂዷል።
በተካሄደው መርሃ ግብር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት ከፍተኛ የቅየሳ ባለሙያ አቶ አደም ሁሴን በሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ላይ ‘የአለም አቀፍ የአሰሳ ሳተላይት ስርዓት” በሚል ርዕስ ከሳተላይት ጂኦስፓሻል ቴክኖሎጂ ጋር ተያያዥነት ያለው አጭር ሰነድ አቅርበው ተሞክሯቸውን አጋርተዋል፡፡
በ31ኛው ዙር የመማማርያ መድረክ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤቱ በየደረጃው ያሉ አመራሮች፣ የማኔጅመንት አባላት እና አጠቃላይ ሰራተኞች በመድረኩ ተገኝተው የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብሩ ተካፋይ ሆነዋል፡፡
የሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ተካሄደ
ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት የሰኞ ማለዳ ከስራ ሰዓት መግቢያ በፊት የሚያዘጋጀውን የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር አካሂዷል።
በተካሄደው መርሃ ግብር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት ከፍተኛ የቅየሳ ባለሙያ አቶ አደም ሁሴን በሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ላይ ‘የአለም አቀፍ የአሰሳ ሳተላይት ስርዓት” በሚል ርዕስ ከሳተላይት ጂኦስፓሻል ቴክኖሎጂ ጋር ተያያዥነት ያለው አጭር ሰነድ አቅርበው ተሞክሯቸውን አጋርተዋል፡፡
በ31ኛው ዙር የመማማርያ መድረክ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤቱ በየደረጃው ያሉ አመራሮች፣ የማኔጅመንት አባላት እና አጠቃላይ ሰራተኞች በመድረኩ ተገኝተው የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብሩ ተካፋይ ሆነዋል፡፡
+3
የረዳን ፈጣሪ ይመስገን !!
እንኳን ደስ አላችሁ!!
ዛሬ በመዲናችን 31.5 ኪ.ሜትር ርዝመት ያላቸዉ 13 የመንገድ ፕሮጀክቶችን እና 8 ድልድዮችን በአጠቃላይ 21 ፕሮጄክቶችን መርቀን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል፡፡
ከተማችንን ለማዘመን ከኮሪደር ልማት ስራዎቻችን ባሻገር የመንገድ መሰረተ ልማት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ልዩ ትኩረት ሰጥተን እየሰራን እንገኛለን፡፡
ዛሬ የተመረቁት እነዚህ የመንገድ መሰረተ ልማቶች ፦
ከአጉስታ- ወይራ መጋጠሚያ፣ቱሉዲምቱ ኮንዶሚኒያም መቃረቢያ፣
ከቃሊቲ ቀለበት መንገድ ዐደባባይ - በአቃቂ ድልድይ-ቱሉ ዲምቱ ዐደባባይ፣
ከቃሊቲ ቀለበት መንገድ አደባባይ ቡልቡላ-ቂሊንጦ 2ኛ ቀለበት መንገድ አደባባይ፣
የለቡ አደባባይ ማሻሻያ ፕሮጀክት፣
ከአፍሪካ ህንፃ- ጀሞ መስታዎት ፋብሪካ፣
ከቂርቆስ ማርገጃ - ቡልጋሪያ፣
ከቤላ -ፈረንሣይ ፓርክ - ፈረንሣይ አቦ ቤተክርስቲያን፣
ከናሰዉ ሪል ስቴት አርሴማ ቀለበት መንገድ እና ዮናስ ሆቴል ኬብሮን ፋርማሲ አስፋልት መንገዶች ናቸው፡፡
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቧቿን ይባርክ
+1
በመዲናዋ ተገንብተዉ የተጠናቀቁ ከ15,960 በላይ ፕሮጀክቶች ተመርቀዉ ከነገዉ እለት ጀምሮ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ እናትዓለም መለሰ ገለፁ፡፡
ከተማ አስተዳደሩ በ2017 በጀት ዓመት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው የጎላ ዘርፈ-ብዙ የልማት ስራዎችን በማቀድና ተግባራዊ በማድረግ ከ15 ,960 በላይ የተለያዩ ትልልቅ ፕሮጄክቶች ከነገ እሁድ ሰኔ 29/2017 ዓ.ም ጀምሮ ተመርቀዉ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ እናትዓለም መለሰ ተናግረዋል፡፡
ለአገልግሎት ክፍት ከሚሆኑት እና ከሚመረቁትፕሮጀክቶች መካከል የመንገድ፣ የውሃ፣ የቤቶች ልማት ፣ የመስሪያ ቦታዎች፣ የወጣቶች ስፖርት ማዘወተሪያ ሜዳዎች፣ በአረንጓረዴ ልማት የተሰሩ እና ሌሎች ለህብረተሰቡ ፋዳቸው ጉልህ የሆኑ ፕሮጀክቶችን ያካተቱ ናቸው ተብሏል፡፡
ፕሮጀክቶቹ በ91 ቢሊዮን ብር ወጪ በመንግስት እና በ4 ቢሊየን ብር ወጪ በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተገነቡ ሲሆን ፤ የተጠቀሰው በጀት ብቻ ሳይሆን ሌሎች በሂደት ላይ ያሉ ፕሮጀክቶችም በፈጣን ክትትል ሥራው ውስጥ እንዳሉ ወ/ሮ እናት ዓለም መለሰ በሰጡት ማብራሪያ ገልፀዋል፡፡
በተጨማሪም የከተማ አስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ አጠቃላይ ከተያዘለት በጀት ውስጥ 71 በመቶ የሚሆነዉን ለካፒታል ፕሮጀክት ግንባታ እና ለድህነት ቅነሳ ፕሮግራም እንዲውል በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን፣ ገልጸው፣ ለትራንስፖርት ለዳቦ ፍብሪካ ድጎማ፣ ለባሶች ግዥ፣ ለተማሪዎች ምገባ፣ ለጤና መድህን ፕሮግራሞች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝም የቢሮው ኃላፊ አስረድተዋል፡፡
+9
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ 4ኛ ዓመት 13ኛ መደበኛ ስብሰባዉን በአራት ወሳኝ ከተማ አቀፍ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አሳልፏል፡፡
በዚህም መሰረት ፤
1ኛ:- የከተማዋን ፈጣን ለዉጥ ታሳቢ በማድረግ፣ ወጪን ለመቀነስ ፣ አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል እና ወጤታማነትን ለማሳደግ እንዲረዳ ተጠንቶ የቀረበዉ የአስፈፃሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር የማሻሽያ አዋጅ ላይ ተወያይቶ ለምክር ቤት እንዲቀርብ ዉሳኔ አሳልፏል፡፡
በዚህም መሠረት
1..ቱሪዝም ዘርፍ ራሱን ችሎ በኮሚሽን እንዲቋቋም፤
2..የዲዛይን እና ግንባታ ሥራዎች ቢሮ እና የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ፅ/ቤት ጋር እንዲወUድ፤
3.. ማህበራዊ ትረስት ፈንድ ፅ/ቤት ከህብረተሰብ ተሳትፎ እና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ጋር እንዲወUድ
4..የከተማ ውበትና አረንጋዴ ልማት ቢሮ የህዝብ መፀዳጃ ቤቶችን የማልማት ተግባር ለውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን ማስተላለፍን ያከተተ ማሻሻያዎች ተደርገዉ ለምክቤት እንዲቀርብ ወስኖል።
2ኛ:-ለአስተዳደራዊ አመቺነት ፣ ለአገልግሎት ተደራሽነት እና ወጪን ለመቀነስ እንዲያግዝ በፕላን ልማት ቢሮ ተጠንቶ በቀረበዉ የሶስት የወረዳዎች አስተዳደር ወሰን ማሻሻል ጥናት ላይ ተወያይቶ አገልግሎት ተደራሽነትን እና ወደፊት በከተማዋ የሚመጣውን ልማት ታሳቢ ያደረገ በመሆኑ የቀረበውን ማሻሻያ ሀሳብ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል፡፡
3ኛ:-በጤና ቢሮ በኩል ተጠንቶ በቀረበዉ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባላት ክፍያ መጠን ላይ ተወያይቶ ዉሳኔ አሳልፏል፡፡
4ኛ. አገራዊ ፋይዳ ያላቸውን ፕሮጀክቶች ላይ የቀረበ የመሬት ልማት ጥያቄ ላይ በመወያየት አፅድቋል ።
የኮሪደር ልማትን በተመለከተ
የኮሪደር ልማቱ ከተሞቻችን አካበቢያችን ለረጅም ዓመታት የቆዩበትን ቆሻሻና አረንቋ በማስወገድና ደረጃውን የጠበቀ ጽዱ አካባቢን እየፈጠረ ነው። አዲስ አበባ ላይ የመጣው የኮሪደር ለውጥ በራስ የፋይናንስ አቅም፣ በራስ እውቀት እና በዚህ አስገራሚ ደረጃ መገንባቱ ብዙዎችን እያስደነቀ ነው። የነዋሪዎችን አኗኗር አሻሽሏል። የኮሪደር ልማቱ አዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን በሌሎችም አካበቢዎች ነው። ጎንደር፣ ጅማ፣ ባህርዳር፣ ቢሾፍቱና ሌሎችም ብዙ ከተሞች እየተዋቡ እየተቀየሩ ነው። ከተሞችን ጨምሮ በሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች እስከ ነሐሴ መጨረሻ ድረስ ከ20 ሺህ በላይ ፕሮጀክቶች ይመረቃሉ፤ መንገድ፣ ጤና ጣቢያ፣ ትምህርት ቤት እና ሌሎችም በርካታ መሰረተ ልማቶችን ያካተቱ ናቸው። ይህ ስንተባበር ከተማንም ሀገርን የመቀየር አቅም እንዳለንም ማሳያ ነው።
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
የኮሪደር ልማትን በተመለከተ
የኮሪደር ልማቱ ከተሞቻችን አካበቢያችን ለረጅም ዓመታት የቆዩበትን ቆሻሻና አረንቋ በማስወገድና ደረጃውን የጠበቀ ጽዱ አካባቢን እየፈጠረ ነው። አዲስ አበባ ላይ የመጣው የኮሪደር ለውጥ በራስ የፋይናንስ አቅም፣ በራስ እውቀት እና በዚህ አስገራሚ ደረጃ መገንባቱ ብዙዎችን እያስደነቀ ነው። የነዋሪዎችን አኗኗር አሻሽሏል። የኮሪደር ልማቱ አዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን በሌሎችም አካበቢዎች ነው። ጎንደር፣ ጅማ፣ ባህርዳር፣ ቢሾፍቱና ሌሎችም ብዙ ከተሞች እየተዋቡ እየተቀየሩ ነው። ከተሞችን ጨምሮ በሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች እስከ ነሐሴ መጨረሻ ድረስ ከ20 ሺህ በላይ ፕሮጀክቶች ይመረቃሉ፤ መንገድ፣ ጤና ጣቢያ፣ ትምህርት ቤት እና ሌሎችም በርካታ መሰረተ ልማቶችን ያካተቱ ናቸው። ይህ ስንተባበር ከተማንም ሀገርን የመቀየር አቅም እንዳለንም ማሳያ ነው።
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
ዘመናዊ የታክሲ ተርሚናሎች እና የመኪና ማቆሚያዎች ግንባታ ዘርፈ ብዙ አግልግሎት እንዲሰጡ ተደርገው እየታነፁ ነው። ሰኔ 26 ቀን 2017ዓ.ም አዲስ አበባ
+5
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የ90 ቀናት የንቅናቄ ስራዎች ያሉበትን ደረጃ በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎችን ሰጥተዋል።
ከንቲባዋ ከ15 ቀናት በፊት ከመላው አመራር ጋር በመወያየት ዝርዝር አቅጣጫ የተሰጠባቸው 18ቱም ከተማ አቀፍ የክረምት ንቅናቄ አጀንዳዎች ዙሪያ አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ለአብነትም በገበያ ማረጋጋት፣ ስራ ዕድል ፈጠራ፣ ከተማ ግብርናና ሌማት ትሩፋት፣ ገቢ አሰባሰብ፣ የክረምት በጎ ፍቃድ ስራዎች፣ የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር፣ የሁለተኛ ዙር ኮሪደር ልማት ቀሪ ስራዎችን ቆጥሮ ማጠናቀቅ እና ሌሎች ትላልቅ ፕሮጄክቶች አፈጻጸም ዙሪያ አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆናቸውን በተደረገው ግምገማ ተረጋግጧል።
በተለይም ደግሞ የህዝባችንን የኑሮ ጫናዎችን ለማቃለል በተሰራው የተቀናጀ ስራ የከተማችን የገበያ ማዕከላት፣ የእሁድ ገበያዎች፣ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ስራዎች፣ አምራች ኢንዱስትሪዎች እና መሰል ዘርፎች የምርት አቅርቦት ሰንሰለትን በማሳለጥ ከፍተኛ አበርክቶ እንዲኖራቸው መደረጉም ተገልጿል።
ቀሪ ስራዎችን በተሟላ መልኩ ለማሳካት በየደረጃው ያለው አመራር ለላቀ ውጤት በትብብር እንዲረባረብ አቅጣጫ ተሰጥቷል።
የሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ተካሄደ
ሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት የሰኞ ማለዳ ከስራ ሰዓት መግቢያ በፊት የሚያዘጋጀውን የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር አካሂዷል።
በተካሄደው መርሃ ግብር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት የግዥ ቡድን መሪ አቶ ሃብታሙ በዙ በሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ላይ “አይቤን ማን ወሰደው” በሚል ርዕስ ከለውጥ ጋር ተያይዞ በህይወታችን የሚያጋጥሙንን ማንኛዉንም የህይወት ውጣ ውረድ እንዴት ማለፍ እንዳለብን የሚያትት አጭር ሰነድ አቅርበው ተሞክሯቸውን አጋርተዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤቱ በየደረጃው ያሉ አመራሮች፣ የማኔጅመንት አባላት እና አጠቃላይ ሰራተኞች በመድረኩ ተገኝተው የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብሩ ተካፋይ ሆነዋል፡፡
