cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

𝐅𝐢𝐧𝐟𝐢𝐧𝐧𝐞𝐞 𝐏𝐫𝐞𝐬𝐬

إظهار المزيد
Advertising posts
8 015المشتركون
+1924 hour
+2477 يوم
+1 09630 يوم

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

አምና የኤርትራን የነጻነት ቀን በጭፈራ በአዲስ አበባ ያከበሩ ወደ 18 ሺ የሚጠጉትን ኤርትራዊያን የብልጽግና መንግስት አባሯል፡፡ ምን ለማለት ነው፤ ከሶስት ሳምንት ቦኋላ ዘንድሮ የሚከበረውን 33ተኛውን የኤርትራ የነጻነት ቀን፤ በአዲስ አበባ የሚያከብረው የለም ለማለት ነው፡፡ በነገራችን ላይ ኤርትራ የኢትዮጵያን ብዙ ነገር ወስዳ የተገነጠለች በመሆኑ፤ እራስ ወዳድ ሐገር ስለሆነች፤ በሰላም ተረጋግታ መኖር የማትችል ናት፡፡ ለማንኛውም ኢሳያስ አፈወርቂ ማህበራዊ እድገቱን፤ ኢኮኖሚውን እና ልማቱን ጥሩ ስለያዘ፤ እንዲቀጥል ይደገፋል፡፡ በርታ ኢሱ ጀግናው😎!
إظهار الكل...
ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጡሩነህ ትላንት በኮምቦልቻ እንዳለው፤ የትግራይ ህዝብ መከላከያ ሰራዊት [Tigray Defenece Force (TDF)] ትጥቅ ካልፈቱ እና ያቀረብንላቸውን አማራጮች የማይቀበሉ ከሆነ፤ በትግራይ ክልል ላይ ድጋሚ ህግ ለማስከበር እንገደዳለን በማለት የአለቃውን መልእክት አስተላልፏል፤ ባጭሩ ትግራይ ላይ ዳግም ወረራ እንፈጽማለን በማለት መግለጫ ሰቷል። አቶ ተመስገን ጡሩነህ የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት በነበረበት ወቅት፤ ትግራይ ላይ ከፌደራል መንግስት ጋር በጋራ በመሆን በዘመተበት ግዜ፤ ከታች እንደሚታየው ትግራይ በተወረረች በሶስተኛው ቀን የወታደር ልብስ በመልበስ እና ባርኔጣ በማድረግ፤ ጦርነቱን እየመራ በሚመስል መልኩ፤ በፌስቡክ ገጹ ላይ ሸረሪት ምናምን እያለ መግለጫ መስጠቱ ይታወቃል፤ ለማስታወስ የጻፈውን አንብቡት፡፡ ትግራይ ከአፍሪካ ቀዳሚ፤ ታሪካዊ እና የስልጣኔ መሰረት የሆነች ሐገር ናት፡፡ ከጥንት ከአክሱም ዘመነ መንግስት ጀምሮ ማንም ሳይደፍራት በነጻነት የኖረች ሀገር ናት፡፡ በቅርቡ እንኳን የነ አሉላን እና የነ ዮሐንስን ታሪክ ማንበብ በቂ ነው፡፡ ሐገሮች ባልተፈጠሩ ግዜ ትግራይ ለብዙ መቶ አመታት ሐገር ነበረች፡፡ ይህ ሐቅ ነው፡፡ ህግ ማስከበር በሚል ትግራይን መውረር ትላትም አልተቻለም፤ ዛሬም ነገም አይቻልም❗️ ለተጨማሪ መረጃዎች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ 📌 t.me/Fastsinfo99     🌴  🌴  🌴
إظهار الكل...
Repost from Gumaa Saaqqataa
ናሁሰናይ አንዳርጌ እና ሌሎች ስሞቹ🤔
إظهار الكل...
Repost from Gumaa Saaqqataa
"የከሸፈው ሴራ" ዶክመንተሪ ውስጥ አጅሬ እጇ ገብቶ ነው? (ፓስፖርቱ ማን ይላል?)
إظهار الكل...
👍 1
በኢምፓየረ ኢትዮጵያ እግር ኳስ ተዓምራቱ እንደቀጠለ ነው።😎 ባለፈው ስምንት፤ ጅማ አባ ጅፋር፣ እግር ኳስ ክለብን ፣ በድብቅ ለመሸጥ ሲወያ፣ በተቀረጹት ድምፅ ፣መገለጡ የታወሳል። ይሄ የዛሬ ክስተት ደሞ፤ ጎል አግብተው ደስታቸውን እየገለፁ እንደ ሚመሰለው ዳኛዉን ከበው እያናገሩት ነው። አንዱ ተጨዋች ለማናገር ሜዳው ሁላ አልበቃውም ተጨዋች ላይ ወጥቶ ነው የሚያናግረው።😎 ለተጨማሪ መረጃዎች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ💕 📌 t.me/Fastsinfo99       🥦    🥦    🥦
إظهار الكل...
በአዲስ አበባ በዛሬዉ እለት ባጋጠመ የጎርፍ አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት አልፏል። በዛሬው ዕለት ሚያዚያ 21 ቀን 2016 ዓ.ም ንጋት ላይ በቦሌ ክ/ከተማ በወረዳ 11 ወረገኑ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የጣለዉን ዝናብ ተከትሎ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉን የአዲስ አበባ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታዉቋል። የከተማ አስተዳደሩ ማስተር ፕላናቸዉን ያልተከተሉ የወንዝ ዳርቻ ግንባታዎች ህብረተሰቡን ለጎርፍ አደጋ እንደሚያጋልጡ በጥናት በመለየት ይህንን የአደጋ ስጋትና ተጋላጭነት በመሠረታዊነት የሚፈታ ፕላኑን የጠበቀ ዘላቂ የመፍትሄ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አስታዉቋል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ በደረሰው በዚህ ድንገተኛ አደጋ ምክንያት ህይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል::በመሆኑም ተመሳሳይ አደጋዎች እንዳያጋጥሙ ህብረተሰቡ ከከተማ አስተዳደሩና ከእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የሚተላለፉ የጥንቃቄ መልእክቶችን ተግባራዊ እንዲያደርግ አሳስቧል:: ለተጨማሪ መረጃዎች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ 📌 t.me/Fastsinfo99     🌴  🌴  🌴
إظهار الكل...
ግራኝ አህመድ ብርጌድ ተመሰረተ...⁉️ ሰው ላመነበት አላማ ስለሚከፍለው ዋጋ ሀሳብ መስጠት አልፈልግም። ምክንያቱም ያልገባኝ ነገር ስላለ አያገባኝም። እኔ ግን የሚገርመኝ አንድ ነገር አለ። ሰው አንድ አይነት ቋንቋ እያወራ ለአንድ አላማ እየታገለ ትልቅ ጠላት አለኝ ብሎ በርሃ ገብቶ እንዴት ትልቁ ጠላቱን እረስቶ እዛው እርስ በ እራሱ ይጋጫል? .* አሜሪካን ሀገር ቁጭ ብለው እኛ የዘመነ ካሴ ነን! እነ እከሌ የእስክንድር ነጋ ናቸው።የጎጃም ፋኖ ተጠሪነቱ ለእከሌ ነው። የምስራቅ ፋኖ መግለጫ እኛ አይመለከተንም። የጎንደር ወጣት በማንም አይመራም ። የሚንሊክ ብርጌድ ተጠሪነቱ በሟች አሳምነው ፅጌ ነው። የወሎ ፋኖ ማንም ተነስቶ አያዘውም። ግራኝ አህመድ ብርጌድ በወሎ እዝ ነው። .* ብቻ ምን አለፋችሁ የማይሰማ ጉድ የለም።ባለፈው ሶስት ሳምንት ናሁሰናይ ብርጊድ ተመሰረተ በአዲስ አበባ ፋኖ እንቅስቃሴ ተጀመረ ተብሎ ጠዋት ተመስርቶ በዛኑ ቀን ጠዋት ፈርሶ በዛኑ ቀን ጠዋት ጥይት ጠጥቶ ሞተ የሚል ዜና በተሰማ በዛው ጠዋት ደግሞ ሌላው የፋኖ ብርጌድ ይህ እኛን አይመለከትም ብሎ መግለጫ ያወጣ ነበር። .* ወንድሜ ሆይ በቁምህ እያለህ አሜሪካ ያለው ዲያስፖራ በስምህ ጎፈንድሚ ከፍቶ ይሰበስባል። ስትሞትም በመሞትህ ያዘነ መስሉ አሁንም ሞትህን ምክንያት አድርጎ ገፈንድሚ ይሰበስባል። በዚህ ብቻ የሚያበቃ እንዳይመስልህ በቤተሰብህ ስም እንደገና ብር ይሰበስባል። ተቸግረዋል ብሎ አደባባይ አውጥቶ መለመኛ ያድርጋቸዋል። ዲያስፖራው በዚህ መጠን ክፉ ነው ንቃ! .* ደግሜ ደጋግሜ አሁንም እኔ ግን እንዲህ እላለሁኝ። ወጣት ሆይ ውድ ነፍስህን በጎፈንድ ሚ እራሱን እና የቤተሰቡን ኑሮ ለሚለውጥ ብለህ አትሙት። አሜሪካ እና አውሮፓ ቁጭ ብሎ ገፋ በለው እያለህ ወደ ነበልባል እሳት የሚከትህን አትስማው። ተበድለናል ብለህ ካመንክ ቀድመህ ውስጥህን አጥራው። ገዳይህ አብሮ የቆመው መንድምህ ነው።😂😭 የተፃፈው በ #TST_APP ____ 📌 t.me/Knowledge055         🥦    🥦    🥦
إظهار الكل...
👍 5 1🤯 1
«ለኢትዮጵያ አየርመንገድ አመራሮች እንዲደርስ ሼር አድርጉልኝ» በ©ረከት አደራ! ለካ እንደዚም አለ ወገን ትላንትና ማታ ነው Apr 28 2024 በኢትዮጵያ ሰአት አቆጣጠር ከፍሽቱ 2:20  ቦሌ ኢንተርናሽናል ኤርፖርት የደረስኩት business class  ካውንተር ላይ አንድ ሴት እና አንድ ወንድ የአየር መንገዱ ሰራተኞች ነበሩ። በስተቀኝ ቼክኢን ሲያደርግ ለነበረ  ቀጭን  የቀይ ዳማ ወጣት የኢትዮጵያ ፓስፖርቴን ሰጠሁት የት ነው የምትሄጂው አለኝ ደብሊን አልኩት በየት በኩል አለኝ በአርላንዳ  ኤርፖርት በስቶኮም በኩል አልኩት ሲስተም ቼክ አላረገ ፓስፖርቴን አላየ መሄድ አትችይም  ትራንዚት አይፈቀድም አለኝ። ሁሌ የምመላለስበት መንገድ ነው እኮ ወንድሜ አውሮፖ ውስጥ ስፔሻል ቪዛ የሚያስፈልገው ለለንደን ብቻ ነው አልኩት  በቃ ዞር በይ ሌላ ከስተመር ላስተናግድበት አለኝ እኔስ አልኩት  የማውቀው ነገር የለም ሴኩሪቲ ከመጥራቴ በፊት  አትረብሺኝ ዞር በይልኝ አለኝ እሺ ጥራ በቃ  ዞር አልልም አልኩት። አንድ ኢሚግሬሽን የሚሰራ ወጣት በአጋጣሚ እያለፈ አይቶ እባክህን እየረበሸችኝ ነው ዞር አድርግልኝ አለው ወጣቱም  ምንም ሳይናገር ጥሎ ሄደ እኔም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቢሮ ሄጄ  ሱፐርቫይዘር ካለ አናግሩኝ ተቸግሬአለው አልኳቸው  አንድ የአየር መንገዱ ሰራተኛም ምን ልርዳዎት አረፍ ይበሉ አለኝ። የሆነውን ነገርኩት ነይ እንሂድ ብሎ ወደ ካውንተሩ ሄድን ምንድ ነው ይችላሉ እኮ መብረር ለምን አስቆምካቸው ብሎ ጠየቀው  እራሱ ሲስተሙ ውስጥ ገብቶ  ካየ በኃላ እንቢ ያለው ወጣት እንዲሰራ አዘዘው ወጣቱም ቼክኢን አደረገኝ  ቆም ብዬ ብዙ አሰብኩ  የኢትዮጵያ ፓስፖርት በመያዜ ብቻ ሲስተም ቼክ ሳያደርግ  አትበሪም በማለቱ መርህ አልባ  ድርጊት በመፈፀሙ በጣም አዝኛለው አፍሬአለም እኔ አንድ ቀንም ዜግነት ባለመለወጤ ፀፅቶኝ አያውቅም፣ ሀገሬን ወዳታለው  እንደዚ ያሉ ብራንዳችንን ክብራችንን መጠሪያችን የሆነውን  ብቸኛው አየር መንገዳችን  ስሙ እንዲጎድፍ ሰዎች እንዲማረሩበት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ የሚሰሩ ግለሰቦች መኖራቸውን አውቄአለው። እኔ በሌላ አየር መንገድ business class ከምጏዝ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎ  ቢሆን ብጏዝ እመርጣለው  ብዙ ጥሩ ሰዎች ያሉበት ቤት ነው ግን ጥቂቶቹ ስርአት አልበኞች  የአየር መንገዱን መልካም ስም እያስጎደፉ ስለሆነ እርምጃ ሊወሰድባቸው ይገባል  እላለው። ሼር አድርጉ ለሚመለከተው አካል ይድረስ ለተጨማሪ መረጃዎች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ 📌 t.me/Fastsinfo99     🌴  🌴  🌴
إظهار الكل...
👍 5