cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

የተጓዦች ስንቅ

ለማይቀረው ጉዞ እንዘጋጅ

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدلم يتم تحديد اللغةالفئة غير محددة
مشاركات الإعلانات
179
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

Photo unavailableShow in Telegram
ለ3 ዓመት ገደማ ሲሰጥ የነበረው የቁርዓን ተፍሲር በአላህ ፍቃድ ተጠናቋል ። የድምጽ ፋይሉን ለማገኘት👇🏼👇🏼👇🏼👇🏼👇🏼 https://t.me/tefsirsheikhali ሼር በማድርግ የኸይር ስራ ተካፋይ ይሁኑ سُبْحَانَكَ اللَّهُمَّ وَبِحَمْدِكَ ، أَشْهَدُ أَنْ لا إِلَهَ إِلا أَنْتَ ، أَسْتَغْفِرُكَ وَأَتُوبُ إِلَيْكَ
إظهار الكل...
Repost from ABX
የአፈንዲ ወግ አንዳንዱን ሰው በርበሬ መቀባት ነው! -- ገበሬው አህያውን እየነዳ ወደ ገበያ ሊሄድ ተነሳ፡፡ ትንሽ ጊዜ ካዘገመ በኋላ አህያው መንቀርፈፍ ጀመር፡፡ በዱላ እየደጋገመ ቢወግረው አህያው ፍጥነቱን አልጨምር አለ፡፡ በዚህ ሁኔታ እያለ አንድ መንገደኛ አጋጠመው፡፡ ይህም መንገደኛ እንዲህ የሚል ምክር ሰጠው፡፡ “አህያውን በዱላ እየደበደብክ ከምታሰቃየው ሌላ ዘዴ ብትጠቀም ይሻላል፤ ለምሳሌ በጀርባው ላይ በርበሬ ብትቀባው ሽልል ብሎ ይጓዛል” ገበሬው ከመንገደኛው ያገኘውን ምክር በመቀበል በርበሬ ገዝቶ በአህያው ጀርባ ላይ ቀባው፡፡ ከዚያ በኋላ አህያው ሊቆም ነው? ጅብ እንዳየ በግ “ብርርር” ብሎ ይጓዝ ጀመረ፡፡ ተራራውን ሽቅብ እየወጣ ቁልቁለቱን በከፍተኛ ፍጥነት አስነካው፡፡ ሰውየውም አህያውን ተከትሎት መሮጥ ጀመረ፡፡ ነገር ግን ሊደርስበት አልቻለም፡፡ ይብሱኑ ደካከመውና ከአንድ ዛፍ አጠገብ ቁጭ አለ፡፡ በዚህን ጊዜም ሌላ መንገደኛ ገጠመውና ለምን እንደተቀመጠ ጠየቀው፡፡ ገበሬውም “አህያዬ ሲደክምብኝ ጊዜ አንዱ ሰውዬ በጀርባው ላይ በርበሬ ቀባው አለኝ፤ በርበሬ ስቀባው ግን ልደርስበት አልቻልኩም” በማለት መለሰለት፡፡ መንገደኛውም “ይህማ ቀላል ነው፤ አንተም በጀርባህ ላይ በርበሬ ብትቀባ በቶሎ ትደርስበታለህ” የሚል ምክር ሰጠው፡፡ ----- ተረቱን ሳንሱር አድርገነው ነው እንጂ በርበሬው የተቀባው በጀርባው ላይ አይደለም፡፡ በጀርባ ላይ የተቀባ በርበሬ እንዴት ያቃጥላል? በርበሬው የተቀባው በእንትኑ ላይ ነው፡፡ (ቂቂቂቂቂቂቂቂ… ) ---- እውነቴን ነው። ከአንዳንድ ዓይነት ጎታታና ተቸካይ ሰው ጋር መጨራጨስ ግመል አይቶ ከማያውቅ የከተማ ሰው ጋር በሰሀራ በረሃ እንደ ማቋረጥ ነው። እናንተ የበረሃው ንዳድ አቃጥሎአችሁ ቶሎ ለመገላገል ትኳትናላችሁ። እርሱ ግን በመንገድ ላይ ባለሻኛውን ግመል ያይና "እንዴ! ቀጭኔው በጀርባው ላይ ተራራ አለበት እንዴ?" እያለ ለማዳነቅና ብዙ ጥያቄ ለመቅደድ ይቆማል። እሱንም በርበሬ ነው መቀባት አቦ!! ---- http://t.me/MuhammedSeidABX
إظهار الكل...
የ ጁምዓ ኹጥባ ፡ በ ዶ/ር ሸይኽ ሙሐመድ ሓሚዲን _________*****______ ያለንበትን አህዋል አስመልክተው የሰጡት ምክር እንደወረደ _________*****______ ጉዳዩ በተደጋጋሚ የተነሰ ቢሆንም ካለው ተጨባች ሁኔታ አኳያ አሁንም ደጋግመን እናነሳዋለን። ሙእሚኖች ወንዲማማቾች ናቸው፡ አንዲ ሰው ከ ሌላ ሰው የሚበልጥበት ምንም አይነት መስፈርት የለም በ ቀርዓን የተቀመጡት ሁለት ነገሮች በሰተቀር። አንደኝው ኢማን ነው ፡ ሌላኛው ደግሞ ኢልም (እውቀት ) ነው። እውቀት ያለው እውቀት ከ ሌለው ይበልጣል። ይህም ማዕረግ ነው። ቁራንም እውቅና የሰጠው ነው። አላህ በ ቁርዓኑ የሚያውቁና የማያውቁ እኩል አይደሉም ብሎናል። ከዚያ ቀጥሎ ያለው ደግሞ ኢማን ያለው ሰው ነው ። አላህ ያመኑና እውቀት የተሰጣቸውን በ ማዕረግ ከፍ ያደርጋቸዋልና። ከዚህ ዉጭ ሁሉም ሰው እኩል ነው። ማንም ሰው ደግሞ አላህ ዘንድ ዋስትና ያለው ፡ የ አላህ ወዳጅ እና ባለሟል ስለመሆኑ ዋስትና የተሰጠው የለም። አንድ ሰው በ ግሉም እኔ የ አላህ ወዳጅ ነኝ ብሎ ጀዝም ሊያደርግ አይችልም፡ ሌላም ሰው እገሌ የ አላህ ሰው ነው ብሎ ቁርጥ አቋም መውሰድ አይችልም። ይህ ገይብ ነውና። ምናልባት ከምናያቸው መልካም ነገሮች ተነስተን ጥሩ ግምት ( ሚነ ሷሊሂን ሊሆን ይችላል ) ማለት እንችል ይሆናል እንጅ ከዛ የዘለለ ማለት አይቻልም። ቡድንም ይሁን ግለሰብም ይሁን ማንነቱን የሚያውቀው የውመል ቂያም ቀን አላህ ዘንድ አርድ ሲደረግ ብቻ ነው። አለዚያ ግን ኡመቱ አንድ ኡመት ነው ። ላ ኢላሃ ኢላ አላህ የሚለው ገመድ አስተሳስሮታል። አላህም ያዘዘን በዚሁ በ አላህ የ እምነት ገመድ ተሳሰሩ ነውና። አንዲ ወንዲሜ ጋር በ ሃሳብ ወይም ሌላ ዱንያዊ ነገር ግጭት ቢኖረኝ እንኳ እሱም ሙዕሚን እኔም ሙዕሚን እስከሆን ድረስ ምንም እንኳ ጠቡ ቢኖር የ ሙዕሚንነት ወንዲማማቺነቷ አትቀርም። ይሄን አላህ ነው ያለው " ሁለት የ ሙዕሚን ቡዲኖች ቢጣሉ ወይም ቢወጋጉ አስታርቁ " ብሎ። ህለቱንም ሙዕሚን ብሎ ነው የጠራቸው እና ««... አንደኛዋ በ ሌላኛው ላይ ዲንበር ካለፈች ግን ድነበር ያለፈችዉን ተባብራችሁ ያዟት »» ብሏል። ይሄም ወደ አላህ ፈቃድ እስከምተመለስ ድረስ ነው። ሃቂቃው ይሄ ሆኖ ሳለ ዛሬ ዛሬ እኔ ነኝ ትክክሉ ፡ ሌላኛው የተበላሸ ነው ማለት መጥቷል። ሃሳቦችን ከ ማስረጃ አንፃር ማረም እና መሞገት እውቀት ላለው ሰው አግባብ ነው። ነገር ግን እራስን ቅዱስ ሌላውን እርኩስ አድርጎ መግለጽ ከ ትቢትና ከ ኩራት የ ዘለለ አይደለም። ምኑ ታውቆ ነው እንዲህ ? ገና እኮ የ ዉመል ቂያማ ስራህ በ ቀኝህ ከተሰጠህ ብቻ ነው የ አላህ ወዳጀነትህ የሚታወቅልህ ። ዛሬ ዱንያ ላይ የ ዝግጂት ነው፡ የ ጥረት ነው ፡ ለመቃረብ በተቻለ መጠን መልፋት ነው ያለብን። ስለዚህ ባልሆኑ አስተሳሰቦች፡ ሰው ሰራሽ በሆኑ አመለካከቶች ፡ ከዚያም አልፎ ጠለቅ ብለን ካየናቸው የሙስሊሙ ሳይሆኑ የ ሌላ የሆኑ አመለካከቶች ፡ ኡመተል ኢስላምን መበታተን፡ ማለያየት ከዚያም አልፎ እስከ ማደባደብ ድረስ መሄድ ይቅር የማይባል በደል ነው ። ይህን ዙልም ማንኛውም ሙስሊም ይቁም ብሎ ድምጹን ክፍ ማረግ የሚኖርበት ጉዳይ ነው። የ አኪራ ጉዳይ ከሆነ እዛው እኬራ ነው የሚለይለት ። የ ዱንያ ጉዳይ ከሆነ ምንም ሌላ መስፈር የለንም « ላ ኢላሃ ኢላ አላህ » ካለ ሙስሊም ነው ። ወደ ቂብላ ዙሮ ዉዱዕ አድርጎ ከሰገደ እኛ ሙዕሚን ነው ነው የምንለው በሚታየን። አንዳንድ ግድፈቶች ካሉት ከ ኢልም አንጻር ማስተማር እና መምከር ነው። እንጂ ከዚያ ዉጭ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል አይነት ጉዞ በ ፍጹም ተቀባይነት የለውም። በተልይ በዚህ ዘመን የ ዲነል ኢስላም ጠላቶች በበዙበት እና ፊትና በ ተንሰራፋበት ሁኔታ ላይ ፡ በመቶዎች ሙስሊሞች ተገደሉ እያልን እያለቀስን ባለበት ሰዓት ላይ እንደገና እርስ በርሳችን ከ አቅል ውጭ ነው። ለመሆኑ ድነል እስላም ይሄን ያንተ ቤት ነውና እገሌ ይገባል እገሌ አይገባም ብለህ ልታባርርበት ነው ? የ አላህ ዲን አይደል እንደ ? ዲነል ኢስላም እኮ በ ቁርዓን በ ሱና ዉስጥ ነው የተቀመጠው ፡ ተመንጥሮ ወለል ብሎ ቁጭ ብሏል መከተል ለፈለገ ሰው ፡ ዘር አይቆጥር ፡ አካባቢ አይመለከት ፡ ይህ ነው የ አላህ ዲን እኮ። ስለዚህ በኛ መካከል ልዩነትን ለማስፋት መጣር ፡ ወይም ለማስፋት የሚጥሩ አካላትን ማበረታታት እስልምናን መበደል መሆኑን እንወቀው። ይህንንም በደል በጋራ ልንከላከለው ይገባል። ልጆቻቸው ወይም ቤተሰቦቻቸው በተሳሳተ መንገድ ላይ ካሉም መምከር ፡ መገሰጽ አለባቸው። ኡለማዎቻችንም ለ ሃቅ መቆም ነው እንጂ ለ ቡድን ወይም ለሆነ አስተሳሰብ ወግኖ ሃቅን መጨፍለቅ ለ አኪራም አያዋጣም ፡ በ ዱንያም ለ ስኬት አያበቃም። ከ ልዩነት ፡ ከ ጭቅጭቅና ንትርክ የሚገኘው መልፈስፈስ ፡ መድከምና መውደቅ ነው። አቅም ከተፈለገ በ አንዲነት ፡ በመዋደድ ፡ በወንዲማማቺነት እና በመደጋገፍ ዉስት ነው ያለው። ...እስኪ ከ ነፍስያችን ፡ ከ ዝንባሊያችን ገለል እንበልና ለ አላህ እንቁም። አላህ ««« ... እኔ የምገስጻችሁና የምመክራችሁ በ አንዲት ነገር ነው ፡ በተናጠልም ሆነ በ ቡዲን ስትሆኑ ለ አላህ እንዲትቆሙ ነው ። »»» ይላል። ለ አላህ ስትሰሩ መገምገም ይመጣል። ማሰብ ይመጣል ። አቅልም ይመለሳል። ለ አዱንያ ወይም አኬራህ የሚጠቅም ላይ እንጂ አትገኚም። አላህ ይወፍቀን። @daewa_tv
إظهار الكل...
አራተኛው፡- ፨ ከዒባዳዎች ሁሉ በላጩ በሁሉም ጊዜ ዉስጥ አላህ ዘንድ ለመወደድ መሥራት ነው። ጊዜ፣ ሁኔታና አንፃርን እያዩ፡፡ ለምሳሌ ጂሃድ በሚያስፈልግበት ጊዜ ምርጡ ሥራ ጂሃድ ነው። እንግዳ ቢመጣ በላጩ ሥራ የሚወደዱ ዚክሮችን ጭምር በመተው ሐቁን ለመወጣት ደፋ ቀና ማለት ነው፡፡  ከፈጅር በፊት ባለው የመጨረሻ ሌሊት ጊዜ፤ (ሱሑር) ላይ ትልቁና በላጩ ሥራ ሶላት፣ ቁርአን፣ ዱዓ፣ ዚክር እና ኢስቲግፋር ናቸው።      ተማሪን በሚመክሩበትና በሚያስተምሩ ጊዜ በላጩ ነገር - ሙሉ በሙሉ ከልብ ሆኖ ማስተማር ነው፡፡  በአዛን ጊዜ በላጩ ሥራ፡- ሙአዚኑን በመከታተል የሚለውን ማለት በዚህ ጊዜ ላይ የሚደረጉ ዚክሮችን ማድረግ ነው። በአምስቱ ሶላቶች ወቅት በላጩ ነገር፡- ሶላቶችን ባማረና በተገቢው መልኩ ለመፈፀም የቻሉትን ያህል መጣርና መበርታት፣ ጊዜያቸው እንደገባ ወዲያዉኑ መስገድ፣ ወደ መስጂድም ሄዶ መስገድ ነው፡፡ መስጂዱ ቢርቅም የሚሻለዉና የሚመረጠው ይህ ነው።   የተቸገረን ሰው በሚረዱበት ጊዜ በላጩ ነገር፡- ሌላውን በማስተባበርም ሆነ በራስ አቅም መርዳት፣ በገንዘብ ማገዝ፣ በዚሁ በማገዙ ሥራ ራስን መወጠር፣ ከችግር እስኪወጣ ድረስ የራስ ሥራዎችና በፊት የለመዱትን የዚክርና የኸልዋ ተግባራት ጭምር በመተው ለሱ መቆም ነው።   በቁርአን ቂርአት ጊዜ በላጩ፡- ቀልብን  በሙሉ አሰባስቦ ትኩረትን በመጨመር ማስተንተን፣ ለመገንዘብ መጣጣር፣ አላህ ልክ እንደሚያናግር ሆኖ በትኩረት መገኘት፣ ትዕዛዙና ምልከታዉን ለመተግበር መቁረጥ ናቸው።   ዐረፋ ላይ በሚቆሙበት ጊዜ በላጩ ነገር፡- በመተናነስ፣ በዱዓና በዚክር መበርታት፣ የሚያዳክም ፆም አለመፆም ናቸው። በዐሽር አልአዋኺር ረመዷን ጊዜ በላጩ፡- መስጂድ ዉስጥ መቆየት፣ በዒባዳ መገለል፣ ከሰዎች ወሬዎች መራቅ፣ ዕውቀትና ቁርአን ከማስተማርም በበለጠ በመስጂድ ዉስጥ በዒባዳ መቆየቱና መገለሉ ነው የሚመረጠው ብለዋል በርካታ ዑለሞች ።  ወንድም ሲታመም ወይም ሲሞት በላጩ ነገር፡- እሱን መዘየርና ማጽናናት፣ ሲሞት ጀናዛው ሽኝት ላይ መገኘትና መሸኘት ነው፡፡ መከራ ሲወርድ እና ሰዎች ችግር በደረሰባቸው ጊዜ በላጩ ነገር - ችግር ደረሰባቸው ብሎ አለመሸሽና ከነርሱ ጋር ታግሶ አብሮ መኖር ነው፡፡  በላጩ ሙስሊም ማስቸገራቸዉን የሚሸሸው ሳይሆን በማስቸገራቸው ላይ  የሚታገሰው ከነርሱ ጋር ተቀላቅሎ አብሮ የሚኖር ነው፡፡   በኸይር ነገር ከሙስሊሞች ጋር ተቀላቅሎ መኖር ከመገለል ይመረጣል፣ መጥፎ የሚሠሩ ከሆነ ግን ከነርሱ ጋር ከመኖር መገለሉ ይመርጣል። እነርሱን መቀላቀሉ መጥፎነታቸው የሚቀንስ ከሆነ ከነርሱ ጋ ተቀላቅሎ መኖሩ ይመረጣል። በሁሉም ነገሮች ውስጥ በላጩ፡- የአላህን ውዴታ መምረጥና ማስበለጥ ነው፤ በዚያ ጊዜ ግዴታ የሆነዉን ነገር መወጣት፣   የሁለገብ ዒባዳ ባለቤት ውስን የሆነ ዒባዳ ይዞና መርጦ አይንቀሳቀስም፡፡ በርካታ የአምልኮ ተግባራት ውስጥ ይገላበጣል። አንድ ወደ አላህ የሚያደርሱና ከፍ የሚያደርገው የዒባዳ መንገድ ያስተዋለ እንደሆነ ወደዚያው በመግባት ይሄድበታል፣ በዚያው ወደ ሌላ ደረጃ ከፍ ይላል። ጉዞ እስኪያልቅ ድረስም ይህ መስመሩ ነው። ከዑለሞች ጋር ይታያል። መልካም መፅዋቾች ካየም ከነርሱ መካከል አይጠፋም። ቅድሚያ ለኢማን መጽሐፍ http://t.me/MuhammedSeidABX
إظهار الكل...
ከተረሱ ሱንናዎች - የሌሊት ሶላት የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ.) እንዲህ ብለዋል -        ከግዴታ ሶላት ቀጥሎ በላጩ ሶላት የሌሊት ሶላት ነው፡፡ -        ሰዎች ሆይ ምግብ መግቡ፣ ዝምድናን ቀጥሉ፣ ሰዎች ተኝተው ባሉበት በሌሊት ሰዓታት ስገዱ፡፡ ጀነትን በሰላም ትገቡ ዘንድ፡፡ -        የሙእሚን ክብሩ ለሌሊት ሶላት መቆሙ ነው፡፡ -        የሌሊት ሶላትን አደራ፤ የደጋጎች ፈለግ ነዉና፣ ወደ አላህም ያቃርባል፣ ከወንጀል ይከለክላል፣ ኃጢኣትን ያረግፋል፣ በሽታን ከሰዉነት ያስወግዳል፡፡ ከደጋግ የአላህ ባሮች እንዲህ ያሉ አሉ፡፡ -        ከዒባዳዎች ሁሉ በዉድቅት ሌሊት መስገድን የሚያህል አላየሁም፡፡ (ሐሰን አል-በስሪ) -        ለመቃብር ጨለማ ይጠቅማችሁ ዘንድ በሌሊት ጨለማዎች ተነስታችሁ ስገዱ፡፡ (አቡ ደርዳእ) -        ከዱንያ ጥፍጥናዎች የቀሩት ሦስት ነገሮች ብቻ ናቸው - የሌሊት ሶላት፣ ከወንድሞች ጋር መገናኘት፣ የጀማዓ ሶላት፡፡ (ኢብኑል ሙንከዲር) -        አንድ ሰው በሌሊት ይሰግዳል፤ ሰዎችም ፊቱን አይተው ብቻ ይወዱታል፡፡ (ሰዒድ ኢብኑል ሙሰየብ) -        በሌሊት የአላህን ምህረት ከመለመን በላይ አንድን የአላህ ባርያ መቃብሩ ዉስጥ የሚጠቅመው ነገር የለም፡፡ (አቡል ሚንሃል) -            ለሌሊት ሶላት ለመነሳት ከሚያግዙ ነገሮች -        ወንጀልን መተው፣ -        ብዙ አለማምሸት፣ -        ጠግቦ አለመብላት፣ -        ዱዓ ማድረግ፣ -        ሐላል መመገብ፣ -        ቀን ላይ ጥቂት መተኛት፣ -        አላህን ማውሳት ማብዛት፣ https://t.me/NejashiPP https://bit.ly/3r4948i
إظهار الكل...
💎💎ሁሉንም ጥያቄዎቼን ቁርዐን ሲመልስልኝ… #እኔ ``ዛሬ ሙስሊም መሆን እንደ ወንጀል ተቆጥሮ ጥቃት ይፈፀምባቸዋል። ብዙዎቹ አካላቸውን አጥተዋል መቁሰልም አጋጥሟቸዋል ለምን?`` ስለው… 📓ቁርዐን << ቁስል ቢያገኛችሁ ሰዎችንም መሰሉ ቁስል አግንቷቸዋል። ይኽችንም ቀናት በሰዎች መካከል እናዘዋውራታለን>> (3:140) አላህ ያለውን አትርሳ እንጂ አለኝ። #እኔ ``በሙስሊሙ አለም መከራ በዛ ሙስሊም እህት እና ወንድሞቼ እንደ ቅጠል ረገፉ። ለምን እዲህ ይሆናል?`` ስለው… 📓ቁርዐን (እንድትገሰፁና) አላህም እነዚያን ያመኑትን እንዲያውቅ (እንዲለይ) ከናንተም ሰማዕታትን እንዲይዝ ነዉ። አላህም በዳዮችን አይወድም>>። (3:140) ተብሎ የለ አለኝ። #እኔ ``በጣም ታምሚያለሁ `` ስለዉ… 📓ቁርዐን <<በታመምኩም ጊዜ እሱ ያሽረኛል።>> (26:80) በል አለኝ። #እኔ ``ልቤ ውስጥ ጭንቀት አለ `` አልኩት… 📓ቁርዐን ንቁ! አላህን በማውሳት ልቦች ይረካሉ። (13:28) ተብሏል አለኝ። #እኔ ``ሰዎች ያሰቃዩኛል አልኩትና…`` 📓ቁርዐን ጌታህም ከሚሰሩት ሁሉ ዘንጊ አይደለም። (6:132) ብሏል አለኝ። #እኔ ``ብቸኝነት ይሰማኛል ስለው…`` 📓ቁርዐን እኔ ቅርብ ነኝ። የለማኝን ፀሎት በለመነኝ ጊዜ እቀበለዋለሁ። (2:186) ብሏል አለኝ። #እኔ ``ወንጀለኛ ነኝ ባልኩት ጊዜም…`` 📓ቁርዐን በላቸዉ <<እናንተ በነፍሶቻችሁ ድንበር ያለፋችሁ ባሮቼ ሆይ! በአላህ እዝነት ተስፋ አትቁረጡ። አላህ ኃጢአቶችን በመላ ይምራልና። እንሆ እሱ መሀሪው አዛኙ ነውና። (39:53) አለኝ። #እኔ ``አላህ እንዳይረሳኝ ምን ላድርግ ስለው… 📓ቁርዐን አስታውሱኝም አስታውሳችኋለሁና ለኔም አመስግኑ አትካዱኝም። (2:152) አለኝ። #እኔ ``ህይወቴን ጭንቀት ሞልቶታል ስለው…`` 📓ቁርዐን አላህንም የሚፈራ ሰዉ ለርሱ መውጫ ያደርግለታል። (65:2) አለኝ። #እኔ ``ብዙ ነገር እፈልጋለሁ ስለዉ…`` 📓ቁርዐን ጌታችሁም አለ <<ለምኑኝ እቀበላችኋለሁና። (40:60) አለኝ። 🤍 ምስጋና ለአላህ ይገባው ለህይወት ዘመን ሁሉ ጥያቄዎች መልሱን በቁርዐን ለሰጠ። ሙስሊም ስላደረገንም እጅግ ላቅ ያለ ምስጋና ይገባው። 4 any comment @anbabiyanbot #Share @Anbabiwoch
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
Member add eyadregachu
إظهار الكل...
ዐሊ ጠንጣዊ (አላህ ይዘንላቸውና)እነዲህ ይላሉ "ከ1335 — 1405 ዓሂ በየሊለቱ ለብዙ ሰአታት አንነባለሁ። በአንድ ሌሊት 100 ገፅ ብንገምት ( ምንም እንኳ ከዛ በላይ ባነብም)እስከ አሁን 2·5 ሚሊዮን ገፅ አንብቤያለሁ ማለት ነወ።" እኛስ?
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
#همم ‏يقول علي الطّنطاوي رحمه الله: ”بدأتُ أقرأ سنة ١٣٣٥ ونحن اليوم في سنة ١٤٠٥ وأنا أقرأ أكثر ساعات ليلي، فلو قدّرت لكل يوم مئة صفحة، وأنا في الحقيقة أقرأ أضعافها، لكان مجموع ما قرأت مليونين ونصفًا من الصفحات!“ [الذكريات | ٢١١/٣].
إظهار الكل...
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.