ዲያቆን ወልደ ሰንበት መጣጥፎች ፣ ትምህርቶች
ይህ መንፈሳዊ ቻናል ትምህርቶች ፣መጣጥፎችን ፣ወጎች የሚተላለፉበት ነው። እንዲሁም የበአላት ወረቦች ፣ምስባክ ያገኙበታል ይህ ቻናል በባለቤቱ የተከፈተ ቻናል ነው
إظهار المزيد1 119
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-17 أيام
-1130 أيام
- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
معدل نمو المشترك
جاري تحميل البيانات...
🕊
[ † እንኳን ለእናታችን ቅድስት ሰሎሜ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል እና ለበዓለ ቅዱስ ሜሮን በሰላም አደረሳችሁ † ]
† 🕊 ቅድስት ሰሎሜ 🕊 †
የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ስብከቱ ከመረጣቸው ፴፮ [36] ቱ ቅዱሳት አንስት የቅድስት ሰሎሜን ያሕል ያገለገለ: ክብርም የተቀበለ የለም:: ከእመቤታችን ቀጥሎ ከጽንሰቱ እስከ ዕርገቱ ያልተለየች ብቸኛዋ ሰው ናትና::
ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ:- ቅድስት ሰሎሜ ከነገደ አሮን በሚመዘዝ የዘር ሐረግ እናቷ ማርያም ትባል ነበር:: አባቷ ደግሞ ክቡር አረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍ ነው:: ቅድስት ሰሎሜና እመቤታችን የእህትማማች ልጆች ናቸው::
ቅድስት ኤልሳቤጥም ዝምድናዋ ተመሳሳይ ነው:: የ ፫ [3] ቱ እናቶች [ሐና: ማርያምና ሶፍያ] የማጣትና የሔርሜላ ልጆች በመሆናቸው እህታማቾች ናቸው::
"ጥቂት ነገሮች ስለ እናታችን ቅድስት ሰሎሜ "
፩. የአረጋዊ ዮሴፍ ልጆችን [ወንድሞቿን] እንደሚገባ አሳድጋለች::
፪. ጌታችን በተወለደ ጊዜ በቤተ ልሔም ነበረች:: የእመቤታችን መውለድ እንደ ሌሎች ሴቶች መስሏት ድንግልን ስለ ነካች እጆቿ ተቃጥለዋል:: ምሕረት ጠይቃ ጌታን ስትዳስሰው ግን ተፈወሰች::
፫. እመ ብርሃን ስደት ስትወጣ ቅድስት ሰሎሜ "ባንቺ የደረሰ በኔም ይድረስ" ብላት አብራ ተሰዳለች:: ረሐቧን ተርባለች:: ጥሟን ተጠምታለች:: በሐዘኗ አዝናለች:: አብራት አልቅሳለች:: ለ፫ [3] ዓመታት ከ፮ [6] ወራት ያን ሁሉ ጭንቅ አብራ ተካፍላለች::
ድንግል እመቤታችን እሾህ ሲወጋት ታወጣላት: እንቅፋት ሲመታት ደሟን ትጠርግላት ነበር:: ባለቤቱ አድሏታልና ጌታችንን አንዴ በጎኗ ታቅፈው: አንዴም በጀርባዋ ታዝለው: አንዳንዴም ትስመው ነበር::
"መለኮትን ማቀፍ: ማዘልና መሳም ምን ይደንቅ! ለቅድስት እናታችን አንክሮና ምስጋና በጸጋ ይገባል!"
ከስደት ከተመለሱ በሁዋላም ለ፳፭ [25] ዓመታት ከጌታና ከድንግል ማርያም ጋር ኑራለች: አገልግላቸዋለችም:: ጌታችን ተጠምቆ ማስተማር ሲጀምርም ተከተለችው:: እርሱም ከ፴፮ [36] ቱ ቅዱሳት አንስት ደምሯታል:: ለ፫ [3] ዓመታት ከ፮ [6] ወራት ከዋለበት ውላ: ካደረበት አድራ ተምራለች:: እንደሚገባም አገልግላለች::
አምላክ ሲሰቃይ ከጐኑ: ሲሰቀልም ከእግረ መስቀሉ ነበረች:: ብርሃነ ትንሳኤውም ከተገለጠላቸው ቅዱሳት አንስት አንዷ ናት:: ከመድኃኔ ዓለም ዕርገት በሁዋላ መንፈስ ቅዱስን ተቀብላ በሐዋርያት ዘመን የነበረችውን ቤተ ክርስቲያን አገልግላለች::
እድሜዋ ምን ቢገፋ ለወንጌልና ለማዕድ ተግባር ተግታለች:: ወገኖቿ አይሁድ ብዙ አሰቃይተዋት በዚህች ዕለት በመልካም ዕረፍት ወደ ፈጣሪዋ ሔዳለች::
† 🕊 ቅብዐ ሜሮን 🕊 †
ዳግመኛ በዚሕ ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛ የምንከብርበትን ቅብዐ ሜሮን አፍልቆልናል::
በስደቱ ጊዜ ጌታችን በምድረ ግብፅ ደክሟቸው ካረፉበት ቦታ ላይ የዮሴፍ በትርን ቆራርጦ: በኪነ ጥበቡ ውሃ አፍልቆ: አጠጥቶ: ትልልቅ ዛፎች አደረጋቸው:: እዛውም ላይ ቅብዐ ሜሮንን አፈለቀ:: ቅብዐ በለሶንም ይሏቸዋል::
በሁዋላም የጌታችን ወዙ በታጠበ ጊዜ ተቀላቅሎበታል:: ዛሬ እኛም: ንዋየ ቅድሳትም የምንከብረው በዚሁ ቅዱስ ቅብዐት ነው::
አምላካችን እግዚአብሔር በቅድስት ሰሎሜ ላይ ያሳደረውን ጸጋ በእኛም ላይ ያሳድርልን::
🕊
[ † ግንቦት ፳፭ [ 25 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. እናታችን ቅድስት ሰሎሜ [ከ ፵፮ [36] ቱ ቅዱሳት አንስት]
፪. ታላቁ አባ ሔሮዳ ሰማዕት
፫. ፴ ሺህ "30,000" ሰማዕታት [የአባ ሔሮዳ ማሕበር]
፬. ቅዱስ አብቁልታ ሰማዕት
፭. ቅዱስ ቅብዐ ሜሮን
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማዕት
፪. ቅድስት ቴክላ ሐዋርያዊት
፫. ቅዱስ አበከረዙን ሰማዕት
፬. ቅዱስ ዱማድዮስ ሶርያዊ
፭. አቡነ አቢብ [አባ ቡላ]
፮. ቅዱስ አባ አቡፋና ጻድቅ
" ሰንበትም ካለፈ በሁዋላ መግደላዊት ማርያም: የያዕቆብም እናት ማርያም: ሰሎሜም መጥተው ሊቀቡት ሽቱ ገዙ:: ከሳምንቱም በፊተኛው ቀን እጅግ በማለዳ ፀሐይ ከወጣ በሁዋላ ወደ መቃብር መጡ . . . ወደ መቃብርም ገብተው ነጭ ልብስ የተጐናጸፈ ጐልማሳ በቀኝ በኩል አዩና ደነገጡ:: እርሱ ግን አትደንግጡ የተሰቀለውን የናዝሬቱን ኢየሱስን ትፈልጋላችሁ:: ተነስቷል: በዚህ የለም . . . አላቸው:: " [ማር.፲፮፥፩-፰] (16:1-8)
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
🕊
[ † እንኩዋን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የስደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ † ]
የአርያም ንግሥት: የፍጥረታት ሁሉ እመቤት ድንግል ማርያም የባሕርይ አምላክ ልጇን አዝላ በዚህች ቀን ወደ ምድረ ግብፅ ወርዳለች::
በወንጌል ላይ [ማቴ.፪፥፩-፲፰] (2:1-18) እንደተጻፈው ጌታችን በተወለደ በ፪ [2] ዓመቱ የጥበብ ሰዎች [ሰብአ ሰገል] ወደ ቤተ ልሔም መጥተው ሰግደውለት: ወርቅ እጣን ከርቤውን ገበሩ: አገቡለት::
ንጉሥ ተወልዷል መባሉን የሰማ ሔሮድስ መቶ አርባ አራት ሺህ 144,000 ሕጻናትን ሲፈጅ በቅዱስ ገብርኤል ትዕዛዝ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፩ [1] አምላክ ልጇን አዝላ: በአንዲት አህያ ጥቂት ስንቅ ቁዋጥራ: ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ስደት ወጣች::
ከገሊላ ተነስታ በጭንቅ በመከራ: በረሃብና በጥም: በሐዘንና በድካም: በላበትና በእንባ ተጉዛ በዚሕች ቀን ምድረ ግብፅ ገብታለች::
- የአምላክ እናቱ
- እሳትን አዝላ በብርድ ተንገላታለች::
- ለእኛ የሕይወት እንጀራን ተሸክማ እርሷ ተራበች::
- የሕይወትን ውሃ ተሸክማ ተጠማች::
- የሕይወት ልብስን ተሸክማ ተራቆተች::
- የሕይወት ፍስሐን ተሸክማ አዘነች::
- እመ አምላክ ተራበች: ተጠማች: ታረዘች: ደከመች: አዘነች: አለቀሰች: እግሯ ደማ: ተንገላታች::
ለሚገባው ይሕ ሁሉ የተደረገው ለእኛ ድኅነት ነው:: በእውነት ይህንን እያወቀ ለድንግል ማርያም ክብር የማይሰጥ ሰይጣን ብቻ ነው:: አራዊት: ዕፀዋትና ድንጋዮች እንኩዋ ለአመላክ እናት ክብር ይሰጣሉ::
አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍና ቅዱስ ሰሎሜ ደግሞ የክብር ክብር ይገባቸዋል:: ከአምላክ እናት ከድንግል ማርያምና ከቸር ልጇ ጋር መከራ መቀበልን መርጠዋልና::
መድኃኔ ዓለም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለምን ተሰደደ? ለምንስ ስደቱን ወደ ግብፅና ኢትዮዽያ አደረገ?
፩. ትንቢቱን ይፈጽም ዘንድ:: በፈጣን ደመና ወደ ግብፅ እንደሚወርድ ተነግሯልና [ኢሳ.፲፱፥፩ 19:1, ዕን.፫፥፯ 3:7]
፪. ምሳሌውን ለመፈጸም:: የሥጋ አባቶቹ እነ አብርሃም: ያዕቆብ [እሥራኤል]: ኤርምያስ ወደዚያው ተሰደዋልና::
፫. ከግብፅ ጣዖት አምልኮን ያጠፋ ዘንድ:: [ኢሳ.፲፱፥፩] (19:1)
፬. የግብፅና የኢትዮዽያ ገዳማትን ይቀድስ ዘንድ::
፭. ሰው መሆኑ በአማን እንጂ ምትሐት እንዳልሆነ ለማጠየቅ:: ሰው ባይሆን ኑሮ አይሰደድም ነበርና:: ሔሮድስ ቢያገኘው ደግሞ ሊገድለው አይችልም:: ያለ ፈቃዱና ያለ ዕለተ ዐርብ ደሙ አይፈስምና::
፮. ስደትን ለሰማዕታት ባርኮ ለመስጠት:: እና
፯. የአዳምን ስደት በስደቱ ለመካስ ነው::
ቸሩ መድኃኔ ዓለም የድንግል እናቱን ስደት አስቦ ከመንግስተ ሰማያት ስደት ይሠውረን:: ከስደቱ በረከትም ያድለን::
🕊
[ † ግንቦት ፳፬ [ 24 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዕንባቆም ነቢይ
፪. ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊና ቅድስት ሰሎሜ
፫. ቅዱስ አብቁልታ ሰማዕት
፬. ቅዱስ አልዓዛር ካህን [የአሮን ልጅ]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት
፪. ቅዱስ አጋቢጦስ [ጻድቅ ኤዺስቆዾስ]
፫. ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
፬. ቅዱስ ሙሴ ፀሊም
፭. ቅዱስ ቶማስ ዘመርዐስ
፮. ቅዱስ አብላርዮስ ታላቁ
፯. "፳፬ 24ቱ" ካኅናተ ሰማይ [ሱራፌል]
፰. አቡነ ዘዮሐንስ ጻድቅ [ኢትዮዽያዊ]
" ዘንዶውም ሴቲቱ በወለደች ጊዜ ሕጻኑዋን እንዲበላ ልትወልድ ባላት ሴት ፊት ቆመ:: አሕዛብንም ሁሉ በብረት ዘንግ ይገዛቸው ዘንድ ያለውን ልጅ: ወንድ ልጅ ወለደች:: ልጇም ወደ እግዚአብሔርና ወደ ዙፋኑ ተነጠቀ:: ሴቲቱም ሺህ ከሁለት መቶ ስድሳ ቀን በዚያ እንዲመግቧት በእግዚአብሔር ተዘጋጅቶላት ወደ ነበረው ሥፍራ ወደ በረሃ ሸሸች:: " [ራዕይ.፲፪፥፬-፯] (12:4-7)
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
اختر خطة مختلفة
تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.