cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

Motivational speech and Bussiness Advertising!!!!

Promoting organization product, promoting brands, selling products to the customers. And give motivational speachs for the companies and learning about creating different job opportunities which is competitive to the market. Call me: 0943886916or @Akillaa

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدلم يتم تحديد اللغةالفئة غير محددة
مشاركات الإعلانات
172
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

إظهار الكل...
Wina beauty💋💄

Manicure 💅 Pedicure Makeup 💄 Eyelash Address:- 22 Contact us via @Winna 0905698978

إظهار الكل...
Wina beauty💋💄

Manicure 💅 Pedicure Makeup 💄 Eyelash Address:- 22 Contact us via @Winna 0905698978

የሠው ልጅ የሚኖረው የአስተሳሰቡን ያህል ነው።: አንድ ብርጭቆ ውሃ ይዘሃል እንበል ውሃውን ለአንድ ደቂቃ ይዘሀው ብትቆም ችግር የለውም ። ለአንድ ሰዓት ይዘሀው ብትቆም ክንድህን ሊያምህ ይችላል እሱም ችግር የለውም ችለህ ለአንድ ቀን ይዘሀው ብትቆም ግን ክንድህ ዝሎ ፓራላይዝድ ልትሆን ትችላለህ አስታወስክ እስካሁን የውሃውም ሆነ የብርጭቆው መጠን አልጨመረም ያው መጀመሪያ ዘና ብለህ የያዝከው ነው ። አንድ ተመሳሳይ መጠን ያለውን እቃ ብዙ ጊዜ ስትይዘው የአንተ ጉልበት ሲዝል ድካም ሲወርህ በተለይ በአእምሮህ መዛል ምክንያት የብርጭቆው ክብደት ይጨምርብሃል በእውነቱ ግን የውሃም የብርጭቆውም ክብደት ያው ነው ። በህይወት ውስጥ የሚያጋጥም ሃሳብና ጭንቀት ልክ እንደ ውሃው ነው ለችግርህ አንተ ስትጨነቅ ስታስብ ብዙ ጊዜ ስታብሰለስለው የችግር መጠን አይቀንስም የአንተ ችግር የመቋቋም አቅም ግን እየመነመነ ይመጣል ። የችግርህ ክብደት በተሸከምከው ጊዜ ልክ ይወሰናል ችግርህን ምንያህል ነው ? ከማለት ችግርህ ለአንተ ችግር ከሆነ ስንት ቀን ሆነው ብሎ መጠየቅ ጥሩ መልስ ያስገኛል ። ችግር አደንዝዞ ፓራላይርዝድ አድርጎ ሳይጥልህ ጥለሀው ወደፊት ተጓዝ ካልሆነ ወድቀህ አትነሳም ። 🌷🌷ሰናይ እለት🌷🌷 Join: @akituaaaa
إظهار الكل...
*✍️ሀሳብ ሁሉ ነገርህ ነው። ሀሳብ ሲስተካከል ስሜትና እምነትህ በብርሀን ፍጥነት ይስተካከላን፣ስሜትና እምነት ሲስተካከል ተግባራችን ፣ድርጊታችን ይቀየራን ፣ይስተካከላን።ተግባራችን ሲስተካከለ ውጤታችን ይስተካከላን።* *✍️እችላለሁ ብለህ ካሰብክ አወ ትችል አለህ።አልችልም ብለህ ካሰብክ አወ አትችልም። ይልሀን ሔነሪ ፎርድ* ✍️ስለዚህ በሀሳብ የከሰረ ንግድ በተግባር አያተርፍም። ✍️በሀሳብ የፈረሰ ትዳር፣በተግባር አይፀናም። ✍️ስለዚህ ሀሳብ :-ሀይል ነው :-ሀሳብ ዘር ነው :-ሀሳብ ማግኔት ነው *✍️ከበጎች ጋ ያደገው አንበሳ ታሪክ እኛላይ መደገም የለበትም።* *✍️ሰው የዘራውን ያጭዳን፣መልካም ተመኝ መልካም እንድታገኝ፣ይባል የለ ሀሳባችን ላይ እንስራ።
إظهار الكل...
አትፍራ! ተራመድ! “ጀግንነት ማለት የፍርሃት አለመኖር ማለት ሳይሆን ፍርሃትን አጥብቆ በመቋቋም የመቆጣጠርና ወደፊት የመራመድ ብቃት ማለት ነው” - Mark Twain ሳይወድቁ እንዴት መራመድን መልመድ ይቻላል? ሳይኮላተፉስ እንዴት መናገር ይለመዳል? የብዙ ሰዎች አጥር የተገነባው ፍርሃት በሚባል ወጥመድ ነው፡፡ ብዙ ሰዎች እንቅፋት እንደሌለ እርግጠኛ ካልሆኑ በስተቀር አይራመዱም፡፡ መክሰር የሚባለው “አስፈሪ” ነገር አለመኖሩን እርግጠኛ ካልሆኑ በስተቀር ንግድን አይጀምሩም፡፡ መገፋት የሚባለው ነገር እንደማይመጣ ማረጋገጫ ካልተሰጣቸው በስተቀር ለፍቅር ልባቸውን አይሰጡም፡፡ እነዚህ አሉታዊ ሁኔታዎች ግን ማንነታችንን ለስኬት የሚያዘጋጁ የተፈጥሮ መሳሪያዎች ናቸው፡፡ ከተጋፈጥካቸው ያሳድጉሃል፤ ከፈራሃቸው ግን ተራ ሆነህ እንድትቀር ያደርጉሃል፡፡ አንዳንድ ሰዎች ሌላው የማያደርገውንና ድፍረት የሚጠይቅን ነገር ማድረግ ብዙም አይከብዳቸውም፡፡ ከፍታው አስፈሪ ከሆነ ተራራ ላይ በጀርባቸው ባዘሉት ፓራሹት ተማምኖ መዝለል፣ በሞተር ባይስክል እየበረሩ መገለባበጥ፣ … ድፍረቱና ድርጊቱ ብዙ ነው፡፡ ከእነዚህ የድፍረት ድርጊቶች መካከል በሁለት እጅግ ከፍ ባሉ ህንጻዎች መካከል በተወጠረ ቀጭን ገመድ ላይ ካለምንም ድጋፍ ተራምዶ ማለፍ አንዱ ነው፡፡ በአለም ከታወቀው የቀጭን ገመድ ተራማጅ (Funambulist) አንዱ ካርል ዋሊዳ (Karl Wallenda) ነው፡፡ ካርል ብዙ ድፍረት የሚጠይቁ ነገሮች በማድረግ የታወቀ ሰው ነው - የፍርሃት ቃል አውጥቶ አያውቅም፡፡ በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ1978 ዓ.ም በሳንዋን፣ ፖርቶሪኮ ውስጥ በሚገኙ ሁለት የባለ አስር ፎቅ ህንጻዎች ላይ በተወጠረ ገመድ ላይ ለመራመድ ሙከራ አደረገ፡፡ ያቺ ሙከራ የዚህ ሰው የሕይወት መጨረሻው ነበረች - ተከስክሶ የሞተበት ቀን፡፡ ከሞተ በኋላ ሚስቱ ስትናገር እንዲህ አለች፣ “ይህንን ከመሞቱ በፊት ያደረገውን የመጨረሻ የገመድ ላይ ርምጃ ከማድረጉ በፊት ለሶስት ወራት ሙሉ አለወትሮው ወሬው ሁሉ የመውደቅ ፍርሃት ነበር፡፡ የፍርሃትን ሃሳብ ሲያስብ የመጀመሪያው ጊዜ ነው፡፡ እንደ እኔ አመለካከት ሃሳቡን ሁሉ የጣለው በገመዱ ላይ በመራመድ ላይ ሳይሆን ባለመውደቅ ላይ ነበር፡፡” የምትፈራው ጤና ቢስ ነገር ተስፋ ከምታደርገው መልም ነገር ይልቅ ፈጥኖ የመምጣት ባህሪይ እንዳለው አስተውለህ ታውቃለህ? ይህ የሚሆነው እድልህ እንደዚያ ስለሆነ አይደለም፤ በዙሪያህ ያለው ነገር መልካሙን ህልምህን ሳይሆን ፍርሃትህን የሚመግቡ መረጃዎችን የማቅረብ ዝንባሌ ስላለው ነው፡፡ ፍርሃትህን መጋቢው ብዙ ነው፡፡ የፈሪውና “የአጉል ጠንቃቃው” ወሬ፣ የሶሻል ሚዲው ወሬ፣ የዜና አገልግሎት የዝገባ ትኩረት … የፍርሃት ምግቡ ብዙ ነው፡፡ ማንኛውም አዲስ እርምጃ ፍርሃትና ማስከተሉ አይቀርም፡፡ ሆኖም ትኩረታችን ፍርሃቱ ላይ ከሆነ ወይ ሳንራመድ እዚያው እንቀራለን፣ ወይ እየፈራን ተራምደን እንወድቃለን፡፡ ፍርሃት እንዲህ ይልሃል … - አትመልከት - አንድ ነገር እንዳታይ! - አታድምጥ - አንድን ነገር እንዳትሰማ! - አታስብ - አንድ ድምዳሜ ላይ እንዳትደረስ! - አትወስን - ስህተት እንዳትሰራ! - አትራመድ - እንዳትወድቅ! - አትኑር - እንዳትሞት! - አትማር - ፈተና እንዳትወድቅ! - አትውደድ - እንዳትጎዳ! በሕይወትህ ልታነግስ የምትችለው ስሜት አንዱን ብቻ ነው - የፍርሃትን ወይም የመኖር ድፍረትን፡፡ አንዱ እንዲነግስ ስትፈቅድለት ለሌላኛው የባርነት ትእዛዝን እያስተላለፍክ ነው፡፡ ፍርሃት ሲነግስ የመኖር ጣእም ይጠፋል፡፡ ስለዚህ አትፍራ! ተራመድ! ውጣና ሞክር!!! 🌷❤🌷 ሰናይ እለት 🌷❤🌷 @akituaaaa
إظهار الكل...
ትህትና የመልካም ህይወት መሰረት ናት፡፡ሰዎችን ዝቅ ብሎ ማገልገል ወደ ከፍታ የምታወጣ መሰላል ናት፡፡ለራሳችሁም ሆነ ለሌሎች ትሁት ሁኑ፡፡ስትኖሩ መረን አትልቀቁ፡፡ህይወታችሁ በስነ ምግባር እና በበጎነት የታጠረ ይሁን፡፡ንግግራችሁ ለጆሮ ይጣፍጥ፡፡ሀሳባችሁ የሞተን መንፈስ ያንቃ፡፡ስራችሁን ምንጊዜም በታማኝነት ፈጽሙ፡፡ከምትሰሩት ስራ በስተጀርባ ተንኮል አይኑር፡፡ለሰዎችም ሆነ ለፍጥረት ሁሉ መልካም ሁኑ፡፡"ሞኝ!" ብትባሉም ደግነታችሁን አታቁሙ፡፡ዝቅ ብሎ ማገልገል ሞኝነት መስሎ ከተሰማችሁ ክርስቶስን አስቡት፡፡እሱ አምላክ ሲሆን ዝቅ ብሎ የተማሪዎችን እግር አጥቧል፡፡ "ከእናንተ መካከል ታላቅ ለመሆን የሚፈልግ ቢኖር ታናሹን ዝቅ ብሎ ያገልገል፡፡" ሲልም ተናግሯል፡፡ አለም ከምንጊዜውም በላይ የእኛን ዝቅ ብሎ ማገልገል የምትፈልግበት ሰዓት አሁን ነው፡፡ ኢትዮጵያም የእኛን ደግነት፣ ትህትና፣ አገልግሎት እና መስጠት የምተናፍቅበት ሰዓት አሁን ነው፡፡ ሰው በጠፋበት ሰዓት ፍጹም መልካም ሰው በመሆን ሰዎችን እናድን፡፡የበጎነት ብርሃናችን በአለም ያብራ፡፡የመልካምነታችን ፀሐይ በአገራችን ይፈንጥቅ፡፡በቀን ቢያንስ ለአንድ ጊዜ መልካም ነገር ማድረግን እንማር፡፡ዛሬ ይህንን ፖስት ሼር ማድረግ ሰዎችን ከማነቃቃት እንጀምር፡፡ 🌷❤️🌷 ሰናይ እለት🌷❤️🌷 @akituaaaa
إظهار الكل...
"ትልቅ ሕልም፣ የትም ተውሎ፣ እግር ባደረሰው ደርሶ፣ የባከነ አዕምሮ አልጋ ላይ ሲተኛ የሚታይ የማይጨበጥ የድርጊቶች ጋጋታ፣ አልያም ራስህን አልጋ ውስጥ የምታገኝበት የሌሊት ድራማ አይደለም። ትልቅ ሕልም፣ አዲስ ዓመት ሲገባ “አደርገዋለሁ” ተብሎ የሚፎከርለት፣ በማግስቱ ደግሞ የሚጠፋ ደራሽ ውሃም አይደለም። ብዙ ሰዎች አዲስ ዓመት ሲገባ፣ በዓል ሲመጣ ወይም አንድ ስልጠና ሲወስዱ ወኔያቸውን ያጠረቃቅሙና ትልቅ “ግብ” ወይም “ሕልም” ያስቀምጣሉ። ከዚያም ከጥቂት ቀናት በኋላ፣ ሕልማቸውን ረስተው፣ የተለመደ “ተራ” ሕይወታቸውን በድጋሚ እንደ በፊቱ መኖር ይቀጥላሉ። እንደዚህ ዐይነት ሕልም፣ በምንም አጋጣሚ፣ በማንም ሰው ሕይወት ላይ ትልቅ ለውጥ አያመጣም" 🌷❤🌷 ሰናይ እለት🌷❤️🌷 @akituaaaa
إظهار الكل...
እርስ በርሱ የሚጓተት ሕብረተሰብ “የአንድን ሰው እውነተኛ መለኪያው ማየት ከፈለክ የሚበልጡትን ሰዎች ሳይሆን አቻዎቹንና እንዲሁም የበታቾቹን ሰዎች በምን መልክ እንደሚቀርብ (እንደሚያስተናግድ) ተመልከት” - J. K. Rowling ቶም ራዝ (Tom Rath) እና ዶናልድ ኦ. ክሊፍተን (Donald O. Clifton) “ሃው ፉል ኢዝ ዩር በከት” (How Full Is Your Bucket?) በተሰኘው በጋራ በጻፉት መጽሐፋቸው ውስጥ በርካታ አስገራሚና አስተማሪ ታሪኮችን አስፍረዋል፡፡ ከእነዚህ ተቃሚ ታሪኮች መካከል የኮሪያንና የአሜሪካንን ጦርነት አስመልክቶ ለምሳሌነት የተጠቀሙበት ታሪክ ይገኝበታል፡፡ በኮሪያና በአሜሪካ መካከል የነበረው ጦርነት ከተጠናቀቀ በኋላ ዊልያም ሜጀር ኢ. ሜየር (Major William E. Mayer) የተሰኙ የአእምሮ ሃኪም (Psychiatrist) አንድ ሺህ በሚሆኑ በሰሜን ኮሪያ እስር ቤት በነበሩ አሜሪካዊ የጦር ምርኮኞች ላይ አንድን ጥናት አካሄዱ፡፡ ሃኪሙ በተለይም ለማወቅ የፈለጉት ኮሪያኖች በምርኮኞቻቸው በአሜሪካኖች ላይ በውጤታማነት የተጠቀሙበትን ስነ-ልቦናዊ የጦርነት ስልት ለማወቅ ነበር (How Full is Your Bucket, 2005, P. 7-9)፡፡ የአሜሪካ የጦር ምርኮኞች ታስረው የነበሩት የጦር ካምፕ እስር ቤት የአኗኗር ደረጃ ያን ያህል መጥፎ እንዳልነበረ ይታወቃል፡፡ ምርኮኞቹ በቂ ውኃና ምግብ፣ እንዲሁም መሰረታዊ ነገሮች ይሰጣቸው ነበር፡፡ ለምንም አይነት ግርፊያም ሆነ አካላዊ ስቃይ አልተዳረጉም ነበር፡፡ እንደውም በታሪክ ውስጥ እስካሁን ከሚታወቁት የጦር ምርኮ እስር ቤቶች እንደዚያን ጊዜው ያለ እስረኞቹ ምንም አካላዊ ስቃይ ያልደረሰባቸው እስር ቤት አይገኝም ይባላል፡፡ አንድ አንገብጋቢ ጥያቄ ግን የሰውን ሁሉ አእምሮ ወጥሮ ይዞት ነበር፡፡ ለምን ቁጥራቸው እጅግ ብዙ የሆኑ የአሜሪካ የጦር ምርኮኞች ካለምክንያት ሞቱ? እስር ቤቱ ምንም አይነት አደገኛ አጥር አልነበረውም፣ በወታደሮችም አልተከበበም ነበር፤ ሆኖም አንድም አሜሪካዊ እስረኛ የማምለጥ ሙከራ እንኳ አድርጎ አያውቅም፡፡ ነገር ግን እነዚህ ተማራኪ ወታደሮች ካለማቋረጥ የአለቃዎቻቸውን ትእዛዝ ይጥሱ ነበር፡፡ እርስ በርሳቸውም ከመጠን በላይ ይጣሉ ነበር፡፡ አንዳንዴ እንደውም ከራሳቸው ወገን ይልቅ ከማረኳቸው ከኮሪያ ወታደሮች ጋር የጠበቀ ወዳጅነትን በመመስረት እርስ በርሳቸው ይበዳደሉ ነበር፡፡ የሞቱት ሞተው የተረፉት ሰዎች ጃፓን የሚገኘው የቀይ መስቀል ጣቢያ ሲረከባቸውና ቤተሰቦቻቸው ጋር ስልክ እንዲደውሉ እድሉ ሲሰጣቸው አንዳቸውም እንኳ ስልክን የመደወል ፍላጎት አልነበራቸውም፡፡ ምንም እንኳን በነበሩበት እስር ቤት ምንም አይነት የከፋ አካላዊ ስቃይ ባይደርስባቸው፣ 38 በመቶው እስረኛ እንዲሁ ካለምንም አካላዊ ምክንያት እንደሞተ ይነገራል፡፡ ምክንያቱ ሲመረመር ኮሪያኖቹ የተጠቀሙበትን የመጨረሻና የከፋ የጦር ስልትና መሳሪያ ደረሱበት፡፡ ይህ የመጨረሻ የጦር ስልትና መሳሪያ “አንዱ ከሌላው ጋር ከነበረው የእርስ በርስ ትስስርና ግንኘኙነት የተነሳ ሊያገኝ የሚችለውን የስሜት ድጋፍ መንፈግ” ነበር፡፡ ይህንን ለማድረግ የተጠቀሙባቸው ስልቶች አራት ናቸው፡፡ አንዱ በሌላው ላይ መረጃን የማቀበል ስልት አንድ የአሜሪካ ምርኮኛ የፈጸመውን ጥፋት የራሱ አገር ሰው ለኮሪያኖቹ ሲያሳብቅበት፣ ለአሳባቂው ምርኮኛ እንደ ሲጃራና የመሳሰሉትን ነገሮች በመስጠት ኮሪያኖቹ ያበረታቱት ነበር፡፡ አሳባቂውም ለምን ይህንን የሰው ነገር አሳበክ ተብሎ አይጠየቅም፣ የተሳበቀበትም አሜሪካዊ ለምን ይህንን አደረክ ተብሎ አይቀጣም፡፡ ኮሪያኖቹ ይህንን ያደረጉበት ምክንያት ምርኮኞቹ እርስ በርሳቸው አንዲናናቁ፣ እንዲባሉና ወዳጅነታቸው እንዲበላሽ ለማድረግ ነው፡፡ ራስን የመውቀስ ስልት ይህንን ስልት ለመጠቀም ኮሪያኖቹ ከአስር እስከ አስራ ሁለት የሚሆኑ ምርኮኞችን በአንድ ላይ በማድረግ እያንዳንዱ ምርኮኛ በሌሎቹ የራሱ ሃገሩ ሰው ፊት እየቆመ፣ ከዚህ በፊት ስላደረጋቸው ክፉ ነገሮች፣ እንዲሁም ከዚህ በፊት ማድረግ ሲገባው ስላላደረጋቸው መልካም ስራዎች እንዲናገር ያደርጉት ነበር፡፡ የዚህ ስልት ዋነኛ አላማ ምርኮኞቹ ለኮሪያኖቹ እንዲናገሩ ሳይሆን የራሳቸው ሃገር ሰዎች ክፉ ክፉውን ብቻ እንዲሰሙባቸውና እርስ በርስ እንዲናናቁ፣ ግንኙነታቸው እንዲበላሽና አንዱ በሌላው ላይ ያለው ግምት እንዲወርድ ማድረግ ነው፡፡ ለመሪዎቻቸውና ለሃገራቸው ያላቸውን ታማኝነት የማፍረስ ስልት ይህንን ስልት ተግባራዊ ለማድረግ ኮሪያዎቹ ካለማቋረጥ አንድ የአሜሪካ ምርኮኛ ወታደር አብሮት ለተማረከው አዛዡ ያለውን መታዘዝና አክብሮት የመሸርሸር ዘይቤ ተጠቅመዋል፡፡ ይህ ስልት ስኬታማ እንደነበር የሚያሳዩ በርካታ ሁኔታዎች ተከስተዋል፡፡ ለምሳሌ፣ አንድ ጊዜ አንድ ኮሎኔል ለወታደሮቹ ሩዝ በሚያድግበት ረግረግ መሬት ላይ ያለው ውኃ አደገኛ ባክቴሪያ እንዳለው በመጥቀስ ከዚያ እንዳይጠጡ አዘዛቸው፡፡ አንዱ ወታደር እንዲህ ሲል መለሰለት፣ “ወዳጄ ሆይ፣ አንተ እኮ አሁን ኮሎኔል አይደለህም፣ እንደ እኔው ተራ እስረኛ ነህ፡፡ አንተ ለራስህ ተጠንቀቅ እኔ ደግሞ ለራሴ አውቅበታለሁ”፡፡ ይህንን ብሎ ውኃውን በጠጣ በጥቂት ቀናት ውስጥ በተባለው ባክቴሪያ ተመርዞ ሞተ፡፡ አንድ ጊዜ ደግሞ 40 የሚሆኑ ምርኮኞች በራሳቸው ጓዶች ከጎጇቸው ተገፍተው ውጪ እንዲሞቱ ሲጣሉ ማንም ምርኮኛ ምንም ነገር ለማድረግ አልሞከረም፣ ምክንያቱም የእርስ በርስ ግንኙነት ተበላሽቶ መናናቅ ስለነገሰ፣ “እኔን አያገባኝም” በሚል ስሜት ተይዘው ስለነበር ነው፡፡ አዎንታዊ ስሜትን የሚሰጥን ማንኛውንም ነገር መከልከል ይህንን ስልት ለመጠቀም ኮሪያዎቹ ያደረጉት ከምርኮኞቹ ምንም አይነት አዎንታዊ ዜናን በመንፈግና አሉታዊውን ብቻ እየመረጡ በማሰማት ነው፡፡ ጥሩ ዜና የያዘ ደብዳቤ ከአገራቸው ሲላክላቸው በፍጹም አይሰጧቸውም ነበር፡፡ የሞተን ዘመድ፣ እሱን ከመጠበቅ ተስፋ ቆርጣ የተወችው የፍቅረኛ ደብዳቤ፣ ያልተከፈለ እዳን አስመልክቶ የሕግ ጥያቄና የመሳሰሉት ተስፋ አስቆራጭ መልእክቶች ግን በፍጥነት እንዲደርሳቸው ይደረግ ነበር፡፡ ምርኮኞቹ ምንም አይነት ተስፋ እስኪያጡ ከመድረሳቸው የተነሳ አንዳንዶቹ ብርድ ልብሳቸውን ተከናንበውና አቀርቅረው በመቀመጥ በዚያው ይሞቱ እንደነበር ይነገራል፡፡ እነዚህ የአሜሪካ ምርኮኞች ያለቀላቸው እርስ በርሳቸው የተናናቁ ጊዜ ነው፡፡ ምንም እንኳ የነበሩበት ሁኔታ ተስፋ አስቆራጭ ቢሆንም፣ እርስ በርስ ከመናናቅና ከመጨካከን አንድነታቸውን፣ መከባበራቸውንና መደጋገፋቸውን የበለጠ ሊያጠናክሩ የሚገባቸው ሁኔታ ውስጥ ነበር ያሉት፡፡ በማንኛው ጊዜ፣ ከመለያየት አብሮ መሆን፣ ከመናናቅ መከባበር፣ ከመጨካከን ደግሞ መደጋገፍ ይመረጣልና፡፡ ሆኖም፣ እርስ በርሳቸው ከመናናቃቸው በፊት ሁሉም በመጀመሪያ ራሳቸውን መናቃቸው ግልጽ የሆነ ጉዳይ ነው፡፡ በራሴ ላይ ያለኝ አመለካከት ሲወድቅ በሃገሬ ሰው ላይ ያለኝ አመለካከትም አብሮ ይወርዳል፡፡ ራሴን ያየሁበት እይታዬ ወገኔን በዚያው መልክ እንዳይ የማስገደድ ባህሪይ አለው፡፡ “የማንነትህ መለኪያ” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ መጽሐፍ የተወሰደ። 🌷❤️🌷 ሰናይ እለት🌷❤🌷 @akituaaaa
إظهار الكل...
የቁጣ ስሜት!!! ከቁጣ ጋር የተያያዘ ችግር የነበረበት ጓደኛ ነበረኝ። አንድ ቀን፦የቁጣ ስሜት ከቁጥጥሬ ውጪ ሆኖ እየረበሸኝ ነው። ምንም ነገር ሳላደርግ ልቆጣጠረው የሚያስችለኝ መንገድ አሳየኝ። ከአቅሜ በላይ ስለሆነ የሆነ ነገር ማድረግ እችላለሁ ብየ አላስብም። በራሴ ጥረት ከዚህ ችግር እላቀቃለሁ ብየ አላስብም።" በማለት ችግሩን ነገረኝ። "አሁን እየተቆጣሁ ነው።የሚል ፅሁፍ የሰፈረበት ወረቀት ሰጠሁትና "ይህን ወረቀት ኪስህ ውስጥ ያዘውና ቁጣ በተሰማህ ቁጥር አውጥተህ በማንበብ መልሰህ ወደ ኪስህ ክተተው። ቢያንስ ይሄን ማድረግ ትችላለህ።" አልኩት። እሱም እንደሚሞክር ነግሮኝ ተለያየን። ከሁለት ወይም ሶስት ወራት በኋላ ተገናኘንና፦ "ምን ተከሰተ?" ብዬ ጠየኩት። እሱም እንዲህ አለኝ "በጣም ተገርሜያለሁ። ይህ ወረቀት ልክ እንደ ማንትራ ነው የሰራው። ቁጣ በተሰማኝ ቁጥር ከኪሴ አወጣዋለሁ ያኔ እግርና እጄ ሀይል ያጣሉ። ልክ እጄን ወደ ኪሴ ስከት የቁጣ ስሜት እየተሰማኝ መሆኑን እገነዘብና መለስ እላለሁ፣ ተቆጣጥሮኝ የነበረው ቁጣም ይጠፋል። እጄ ወደ ኪሴ ሲሄድ ዘና እላለሁ እናም ወረቀቱን ማንበብ ሁላ አያስፈልገኝም።" አለኝ ከዛም "ይህ ወረቀት የዚህ አይነት ውጤት እንዴት ሊኖረው ቻለ? ምክንያቱ ምንድን ነው?" ሲል ጠየቀኝ። እኔም "ምንም ሚስጥር የለውም በጣም ቀላል ነው። ንቁ ባልሆንክበት ጊዜያቶች ሁሉ የአይምሮ ሁከቶች ይቆጣጠሩሀል። ንቁ በሆንክ ቅፅበት ግን ሁሉም ነገር ይጠፋል።" አልኩት። እናም ወዳጄ ስሜትህ ላይ ንገስበት እንጂ ስሜትህ አንተ ላይ አይንገስብህ!!!! እምነት ይገላል እምነት ያድናል። አንተ የምትሻውን ፈጣሪህ እንደሚያደርግልህ እመን። "ሰው የስራውን ሳይሆን የሚያገኘው የእምነቱን ነውና።" እምነት ዘርን ትመስላለች ፣ራሷን ታበቅላለችና። መልካም ዘርን (ሐሳብን) በአእምሮህ ውስጥ ዘርተህ በቅን ሐሳብ እየተንከባከብካት ጠብቃት። 🌷❤️🌷ሰናይ እለት🌷❤️🌷 @akituaaaa
إظهار الكل...
ሰላም ጤና ይስጥልን የዚህ ቻናል ተከታታዮች ዛሬ ስለ ስህተት ጥቂት እናወራለን። 🍃🍃የሰው ልጅ በተፈጥሮ ስጋዊና ደማዊ ፍጥረት ነው ይህም ማለት የተለያዩ ስህተቶችን ይሰራል ማለት ነው።ችግሩ ግን እሱ ላይ አይደለም ብልህ ሰው ነገሮችን በማመዛዘን ከሰው ስህተት ተምሮ መጪውን ያስተካክላል፥ ሞኝ ከሆንክ ደሞ ከራስህ ስህተት ትማራለህ። ዋናው ነገር መማር አለመማሩ ላይ እንጂ ሁለቱም ለሕይወት በጣም ቁልፍ ነገሮች ናቸው ተምሮ ላስተካከለው ብቻ።መሳሳትን አትፍራ ስለሞከርክ ነው የተሳሳትከውና ቁጭ ብሎ ምንም ሳይሰሩ ከመሞት እየሞከሩና እየተሳሳቱ መሞት በምን ጣዕሙ ዛሬ ከባድ ነው ነገም ከባድ ነው ከነገ ወዲያ ግን የተሻለና የሚያምር ቀን ይሆናል ስለዚህ እጅ አትስጡ መሳሳትንም አትፍሩት ፍራቻቹን ማን እንደሆናቹ አሳዩትና እሱ ራሱ እናንተን ይፍራቹ። 🌷❤️🌷 ሰናይ ዕለት 🌷❤️🌷 @akituaaaa
إظهار الكل...