Pope Shenouda channel አቡነ ሽኖዳ በ ኤላብ
الذهاب إلى القناة على Telegram
380
المشتركون
+324 ساعات
+97 أيام
+2230 أيام
أرشيف المشاركات
"The prospect of major surgery for a patient may be more spiritually beneficial to him than a hundred sermons"
+ Pope Shenouda +
"ለታካሚ ሰው ከባድ የቀዶ ጥገና እድል ከብዙ መቶ ስብከቶች የበለጠ ለመንፈሳዊነት ይጠቅመዋል"
+ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሺኖዳ +
ስንቶቻችን ነን የሚወደን እግዚአብሔርን አንሰማህም ስንለው በህመም በተለያዩ ተግሳጾች ወደ እቅፉ የመለሰን ?
ተመስገን አባቴ ፍቅርህን አብዛልን በወደድከውም ጥራን ከቤትህ አታውጣን አሜን ❤❤❤
"As much as you are able to, share in the sufferings of others, and help lift them up off of them, and be a Cyrenian, carrying the cross of others"
+ Pope Shenouda +
"በተቻላችሁ መጠን የሌሎችን መከራ ተካፈሉ፥ ከእነርሱም ላይ አንሥታችሁ እርዷቸው ልክ የሌላውን መስቀል እንደተሸከመው የቀሬና ሰው ሁን"
+ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሺኖዳ +
የቀሬናው ሰው ስምኦን የጌታን መስቀል ተሸክሞ እንደተጓዘ ያግዘው ዘንድ 😥😥😥
"This is the big difference between love and lust: love always wants to give, and lust always wants to take"
+ Pope Shenouda +
"በፍቅር እና በምኞት መካከል ያለው ትልቅ ልዩነት ይህ ነው: ፍቅር ሁል ጊዜ መስጠት ይፈልጋል, እና ምኞት ግን ሁል ጊዜ መውሰድን ይፈልጋል."
+ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሺኖዳ +
22ቱ አሌፋት፡
በመዝሙር 118 ላይ የምናገኛቸዉ ቃላቶች የልዑል እግዚአብሄር ህቡህ ስሞች ናቸዉ። ትርጓሜያቸዉም
1-አሌፍ
👉አለምን ከነጓዟ ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ የፈጠረ እግዚአብሄር ነዉ ማለት ነዉ።
2-ቤት
👉እግዚአብሄር ሁሉን መስጠት የሚችል ቸር ለጋስ ባለፀጋ ማለት ነዉ።
3- ጋሜል
👉እግዚአብሄር ሊመረመር የማይቻል ግሩም ድንቅ ማለት ነዉ።
4-ዳሌጥ
👉እግዚአብሄር በጌትነቱ ዙፋን ለዘለአለም ይኖራል ማለት ነዉ።
5-ሄ
👉እግዚአብሄር በአንድነቱ በሦስትነቱ ጸንቶ ለዘላለም ይኖራል ማለት ነዉ።
6- ዋዉ
👉እግዚአብሄር በመንግሥት በሥልጣን በአገዛዝ በባህርይ አንድ አምላክ የሆነ ማለት ነዉ።
7- ዛይ
👉እግዚአብሄር በሥራዉ ሁሉ እየታሰበ ሲመሰገን የሚኖር ፈጣሪ ማለት ነዉ።
8- ሔት
👉እግዚአብሄር በመንግስቱ ሽረት በባሕርዩ ኀልፈት የሌለበት ለዘላለም ሕያዉ የሆነ ማለት ነዉ።
9-ጤት
👉እግዚአብሄር ጥበብን የሚገልጽ ከጥበበኞች ይልቅ ጥበበኛ የሆነ አምላክ ማለት ነዉ።
10-ዩድ
👉በእግዚአብሄር ቀኝ ያለ እሱ ኃያልና ጽኑ የሆነ ማለት ነዉ።
11-ካፍ
👉ለእግዚአብሄር የሚሳነዉ ነገር የሌለ ሁሉን ማድረግ የሚቻለዉ አምላክ ማለት ነዉ።
12-ላሜድ
👉እግዚአብሄር ልዑለ ባሕርይ የሆነ ማለት ነዉ።
13-ሜም
👉እግዚአብሄር ንጹሐ ባሕርይ የሆነ አምላክ ማለት ነዉ።
14-ኖን
👉እግዚአብሄር የነገሥታት ንጉሥ የገዥዋች ገዥ የሆነ አምላክ ማለት ነዉ።
15-ሳምኬት
👉እግዚአብሄር ሁሉን የሚገዛ አምላክ ማለት ነዉ።
16-ዔ
👉እግዚአብሄር ታላቅና ገናና የሆነ አምላክ ማለት ነዉ።
17-ፌ
👉እግዚአብሄር ተወዳጅ የሆነ አምላክ ማለት ነዉ።
18- ጻዴ
👉እግዚአብሄር ሐሰት የሌለበት ዕዉነተኛ አምላክ ማለት ነዉ።
19-ቆፍ
👉እግዚአብሄር ለልበ ቅኖችና ለየዋሃኖች ቅሩብ የሆነ አምላክ ማለት ነዉ።
20-ሬስ
👉እግዚአብሄር ክብሩ ከርሱ ለርሱ የተገኘ የሁሉ ጌታ ማለት ነዉ።
21-ሳን
👉እግዚአብሄር በሥራዉ ሁሉ የተመሰገነ ማለት ነዉ።
22-ታዉ
👉እግዚአብሄር ዕንቅልፍ የሌለበት ትጉህ ድካም የማይሰማዉ ጽኑ የሆነ ፈጣሪ ማለት ነዉ።
አሜን!
ምንጭ፡- https://www.ethiopianorthodox.org/amharic/yeqolotbet/lessons/psalm.pdf
መልካም ሳምንት🥰
"It is astonishing that God wants us but we do not want Him; astonishing that we are distracted from the sincerest Beloved who talks to us but we do not respond, who calls us to Him but we do not answer"
+ Pope Shenouda +
"እግዚአብሔር የሚፈልገን እኛ ግን የማንፈልገው መሆኑ የሚያስደንቅ ነው፤ እርሱ የሚያናግረን እኛ ምላሽ የማንሰጠው፣ ወደ እርሱ በፍቅር የሚጠራን እኛ ግን የማንመልስለት ከልብ ወዳጃችን (ፍቅረኛችን) ጋር መለያየታችን የሚያስደንቅ ነው።"
+ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሺኖዳ +
"Who is this devil that is attacking you? He cannot bear a psalm from you, and he cannot bear one of your prayers... and more than this, he is unable to bear your humility"
+ Pope Shenouda +
" የሚያጠቃችሁ ሰይጣን ማን ነው? የእናንተ መዝሙር (ምስጋና ) ሊቋቋም አይችልም ከጸሎታችሁም አንዲቷን መቋቋም አይችልም... ከዚህ የበለጠ ደግሞ ትሕትናችሁን ሊቋቋም (ሊሸከም) አይችልም።"
+ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሺኖዳ +
"If there is no church in your house, then at least is there found for the Lord even a simple corner in it, and an oil lamp and a place for prayer... is your house a holy house, in which the Lord has a portion?"
+ Pope Shenouda +
"በቤታችሁ ውስጥ ቤተ ክርስቲያን ከሌለ፥ እና ቢያንስ ለእግዚአብሔር አንድ ጥግ (ማዕዘን) ፥ ዘይት ÷ መብራት፥ የጸሎት ስፍራም ካልሰጣችሁ ... ቤታችሁ እግዚአብሔር ያደረበት የተቀደሰ ቤት ነውን ?
+ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሺኖዳ +
Repost from ሔዋናዊት ጉዞ
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼ወትባርክ አክሊለ ዓመትከ ወይፀግቡ ጠላተ ገዳም ወይረውዩ አድባረ በድው። "
እንኳን ለአዲሱ አመት አደረሳችሁ
አዲሱ አመት የደስታ፣የፍቅር፣የሰላም፣የአሰባችሁትን የሚሳካበት አመት እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞታችን ነው።
መልካም በዓል መልካም አዲስ አመት!!
+++++++#እንኳን_ደስ_አላችሁ#+++++++
#ትምህርተ_ጽድቅ_ክልስ_ዕትም_በቅርቡ_ይጠብቁ!!!
#የመጽሐፉ መጠን በ "መድሎተ ጽድቅ" መጠን ነው።
#የውስጡ ፎንት መጠን 10 ነው።
#የመጽሐፉ የገጽ ብዛት 452 ነው።
"ትምህርተ ጽድቅ" የተሰኘው በተአምረ ማርያምና በነገረ ክርስቶስ ዙሪያ ላይ የሚነሡ ዋና ዋና የሚባሉ ጥያቄዎችን መልስ የያዘው መጽሐፌ፥ በብዙ ማብራሪያዎች ዳብሮና ሌሎች ተጨማሪ የተአምረ ማርያምና የነገረ ክርስቶስ ጥያቄ መልሶች ተካተውበት ክልስ ዕትም ሊወጣ ጥቂት ቀናት ቀሩት።
መጽሐፉን ብዙዎቻችሁ በተደጋጋሚ ብትጠይቁኝም፡ በዋጋው ውድነት ምክንያት ሳላሳትመው ብዙ ጊዜ ቆይቻለሁኝ። ሲቀንስ ይታተማል ብዬ የነበርኹ ቢኾንም በተቃራኒው እጅግ በጣም ሲወደድ ታተመ። የኅትመት ዋጋ ምን ያህል አስቸጋሪ እንደ ኾነ መጽሐፍ ጽፎ ከሚያሳትም በቀር የሚረዳው ብዙም ያለ አይመስለኝም። አሳታሚው መጽሐፍ ከመጻፍ ባልተናነሰ ለማሳተም የሚደክመውን ድካም እግዚአብሔር ይይለት ከማለት በቀር ምን ማለት እችላለሁኝ🤔 ይህን የምለውም ማለት ስላለብኝ ብቻ ነው። ምንም እንኳን ርእሰ ጉዳዩ በእንደ እኔ ዓይነት ያልተማረ ማይም ሊጻፍ ባይገባውም፡ እንደው ትንሽም ብትኾን ከረዳ በሚል ያዘጋጀኹት መጽሐፍ ነው። ብዙ ደክሜበታለሁኝ፣ እጅግ በጣም ብዙ ብርም ወጥቶበታል። ለኔም ለናንተም ይጠቅመናል ብዬም ተስፋ አደርጋለሁኝና እባክዎን ገዝተው ያንብቡት ይወያዩበት። ለወዳጅዎት ለጓደኛዎትም ያስነብቡ፤ መጽሐፉንም ያስተዋውቁት ዘንድ በትሕትና እጠይቃለሁኝ🙏
Psalms 39/40 አማ - መዝሙር
17: እኔ ችግረኛና ምስኪን ነኝ፥ጌታ ግን ያስብልኛል፤ አንተ ረዳቴና መድኃኒቴ ነህ፤
አምላኬ ሆይ፥ አትዘግይ።
"The person who is poor in spirit is a person who is contrite before himself from within, and contrite before God, and contrite before people, and even before Satan also you see him likewise contrite"
+ Pope Shenouda +
"በመንፈስ ድሀ የሆነ ሰው ከውስጥ ለራሱ የተዋረደ በእግዚአብሔርም ፊት የተሰበረ በሰውም ፊት የተጸጸተ ሰው ነው በሰይጣንም ፊት ደግሞ እንዲሁ ሲሰቃይ ታዩታላችሁ"
+ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሺኖዳ +
