cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ጅማ/ዩ/ ዋና ግቢ - ግቢ ጉባኤ

"ይህ ቻናል የጅ/ዩ/ዋ/ግ/ግ/ጉ ሲሆን በጅማ ዋና ግቢ ለሚማሩ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ተማሪዎች በግ/ጉ ሚትላለፉትን መልዕክት፣ት/ቶች፣ስነ ጽሁፎች እና ሌሎችም ለማድረስ የተከፈተ ቻናል ነው።" ለማንኛውም አስተያየት 👉 @natidula 👉 @MeronW_BAHIRAN 👉 @Mek_J 👉 @AsegidT

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
1 940
المشتركون
+224 ساعات
+127 أيام
+5130 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

የ 2016 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች መጽሄት.pdf8.09 MB
👍 1
🎇✨✨ንኳን ደስ አላችሁ!!! ✨✨🎇 ተመራቂ ወንድም እህቶች እንኳን ለዚህች ቀን አበቃችሁ!  💐 " ስለማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን።" (2 ቆሮ 9: 15) 🎆✞🎆 የተመራቂዎች ሽኝት🎆✞🎆 💐እንደ ስሟ ሐመረ ኖህ (የኖህ መርከብ)😊 በመሆን ከሚያሰጥመው:-  የወቅቱ ፈተና ጠብቃ፤ ዘወትር ሳትሰለች ቃለ እግዚአብሔርን መግባ አደራዋን ተወጥታ ለዚህ ታበቃለች። በእውነት ቅድስቷን ኪዳነ ምህረትን የሰጠን አምላክ ይመስገን። 👉 ነገ ሰኔ 25🎇 በምርቃታችሁ ዕለት የግቢው የምርቃት ፕሮግራም እንዳበቃ፤ ከግቢ በር ጀምሮ በአንድነት በዝማሬ እግዚአብሔር እያመሰገንን  ሐመረ ኖህ ደርሰን ያ መጠጊያ የሆነን ደጇን እንሳለማለን። 🌹 💐 ሰኔ 25 (ማግሰኞ) 🌷የት?  መሐል በር እንሰብሰብ 👉 ረቡዕ (ሰኔ 26) 🎆 ከሰዓት በኋላ በጅማ ማዕከል ማህበረ ቅዱሳን ደማቅ የሽኝት እንዲሁም የአደራ መርሐ ግብር ስለሚኖር ተመራቂዎች ሁላችሁም የምረቃ ጋዎናችሁን እንደለበሳችሁ በሐ/ኖ/ቅ/ ኪዳነ ምህረት እንድትገኙ። አስመራቂዎችም የምንወዳቸውን እህት ወንድሞች በታላቅ ክብር እንድንሸኝ ግቢ ጉባኤ ጥሪዋ ነው።🌹 💐 ሰኔ 26 (ረቡዕ) ⏰ ከሰዓት 9:30 ጀምሮ 🌷የት? ሐ/ኖ ቅድስት ኪዳነ ምህረት "ከእግዚአብሔር-ቤት-መረቅናችሁ" መዝ 117:26🥰 መርሃግቦራቱ በሦስቱ ግቢ ጉባኤያት በአንድነት የሚከናወኑ ይሆናል (ዋና ግቢ፣ ቤኮ እና ማታ ግቢ ጉባኤ)። 💐🌹✨ጅ/ዩ/ዋ/ግ/ግ ጉባኤ✨💐🌹
إظهار الكل...
👍 5
📣ሰንበትን በቅዳሴ!🥰 (ከጰራቅሊጦስ የመጀመሪያው ሰንበት) ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ወረደ መንፈስ ቅዱስ ላዕለ ሐዋርያት ከመ ዘእሳት ወተናገሩ በነገረ ኵሉ በሐውርት። ትርጕም፦ መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት ላይ እንደ እሳት ሆኖ ወረደ በሀገሩ ሁሉ ቋንቋ ተናገሩ። የቅዳሴ ምንባባት፦ ኤፌ ፬፥፩ - ፲፯፤ ፩ዮሐ ፪፥፩ - ፲፰፤ ግብ ፪፥፩ - ፲፬፤ የዕለቱ ወንጌል፦ ዮሐ ፲፬፥፳፪ - ፍ የዕለቱ ምስባክ፦ መዝ ፷፯፥፲፰-፲፱ ዐረገ ውስተ ዓርያም ፄዊወከ ፄዋ፤ ወወሀብከ ጸጋከ ለእጓለ እመሕያው፤ እስመ ይክህዱ ከመ ይኅድሩ። ትርጕም፦ ወደላይ ዐረግኽ፤ምርኮን ማረክኽ፤ ስጦታንም ለሰዎች ሰጠኽ፤ ደግሞም ለዓመፀኞች በዚያ ያድሩ ዘንድ። 👉 ሰንበትን በታላቁ ድግስ ቅዳሴ ተጠራርተን በጋራ እናስቀድስ። @JuWanaGibiGG @JuWanaGibiGG @JuWanaGibiGG ጀማሪ ስትሆን ሰይጣን “አትችልም” ብሎ ተስፋ በማስቆረጥ ሊጥልህ ይሞክራል። ያም ባይሆንለት “ደርሰሃል” እያለ ያለ ልክ በማመስገን በትዕቢት ወጥመዱ ውስጥ ሊጥልህ ይሞክራል። “በሰይጣን እንዳንታለል፤ የእርሱን አሳብ አንስተውምና”  2ኛ ቆሮ 2:11 #ጅ/ዩ/ዋ/ግ/ግቢ ጉባኤ
إظهار الكل...
👍 1
በጣም የሚያስጨንቃችሁ፣ ዕረፍት የሚነሳችሁ፣ ሁሌ የምታለቅሱበት ችግር እና ጭንቀት ካለባችሁ ስለእርሱ እግዚአብሔርን አመስግኑ። እግዚአብሔር በደስታችን ጊዜ እንደማንፈልገው በሚገባ ያውቃል። እርሱ ትዝ የሚለን ሲከፋንና ሲቸግረን እንደሆነ በሚገባ ይረዳል። ስለዚህ ከፍቅሩ የተነሳ ጥለነው እንዳንሄድ፣ እንዳንክደው፣ እንዳንሸሸው ወደ ራሱ የሚያቀርብ ችግር ይሰጠናል። ጌታ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 21 ላይ ከትንሣኤው በኋላ ለሶስተኛ ጊዜ ሊነጋጋ ሲል ለሐዋርያቱ ተገልጦላቸው ነበር። ቅዱስ ጴጥሮስን ሶስት ጊዜ ትወደኛለህን ብሎ ከመጠየቁ በፊት ሌሊቱን ሙሉ ዓሣ ሲያጠምዱ አድረው አንዲት አሣ እንኳን ያልያዙትን ደቀ መዛሙርት "ልጆቼ ሆይ አንዳች የሚበላ አላችሁን?" ብሎ ጠየቃቸው። ምንም ዓሣ እንዳልያዙ እያወቀ ለምን ጠየቃቸው ቢሉ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ሲል ይመልሳል...   "የልጆቹ ሥጋዊ ፍላጎት እንደሚያሳስበውና የርኅራሄ አባት እንደመሆኑ የሐዋርያትን ሥጋዊም መንፈሳዊም ፍላጎታቸውን አሟልቶላቸዋል። ከሞት የተነሳው ክርስቶስ አሁንም በእያንዳንዱ ክርስቲያን ቤት ማለፉን ይቀጥላል፤ በተለይ የተቸገሩትንና የሚረዳቸው ያጡትን ቀርቦ 'ልጆቼ ሆይ አንዳች የሚበላ አላችሁን' ብሎ ይጠይቃቸዋል። ምንም የሚበላ እንደሌላቸው ቢያውቅም በእምነት የሚያስፈልጋቸውን ሁሉ ይሰጣቸው ዘንድ ወደ እርሱ እንዲጸልዩ ያነሳሳቸዋል። እርሱም በፍቅሩ ምንጮች ምግባቸውን ሰጥቶ ያጠግባቸዋል። የልባቸውን ዓይን ከፍቶ እርሱን እንዲያዩትና ረቂቅ አሠራሩን እንዲያውቁ ያደርጋቸዋል።" ወደ እርሱ መጸለይን፣ በእርሱ መመካትን ሊያስተምራቸው ለሐዋርያቱ ጉድለታቸውን፣ ችግራቸውን አስታወሳቸው። እውነት እንነጋገርና፣ ጸሎታችን ሁሉ ከመ ቅጽበት ቢመለስልንና የጠየቅነው ሁሉ ቢደረግልን ማን ወደ እግዚአብሔር ደጅ ቀንና ሌሊት ይመላለሳል? ማንስ እርሱን በማገልገል ይጸና ይሆን? ስንቶች ችግራቸው እንዲፈታላቸው ወደ እግዚአብሔር ቤት መጥተው አገልጋይ ሆነው ቀሩ?.... ስንቶች ጭንቀታቸው እንዲቀልላቸው ወደ እግዚአብሔር ቀርበው የቅድስና ሕይወትን ያዙ?? ከእግዚአብሔር ጋር ያጣበቀችን የአንዲት ጸሎት አለመመለስ የሆነች ስንቶቻችን ነን? እግዚአብሔር ከእርሱ የምንርቅበትን መንገድ በችግሮች ያጥርብናል። ታዲያ ለዚህም ልናመሰግነው አይገባምን? እርሱን ደጅ የምንጠናበትን ችግርን፣ ጭንቀትን፣ ፈተናን ያላሳጣን እግዚአብሔር ስሙ የተመሰገነ ይሁን። . . ዲያቆን ዮሐንስ ደረጀ ሰኔ 18,2016 ዓ.ም አዲስ አበባ
إظهار الكل...
👏 1
🔔🔔🔔ተንሥኡ ለጸሎት 🔔🔔🔔 "ጸሎት፦ በሕይወት ማዕበል ውስጥ መጠጊያ ወደብ፤ ማእበል ለሚያንገላታቸው መልሕቅ፤ የድሃው ሐብት፤ የባለጸጋው ደህንነት፤ የታማሚው መዳኛ ወይም ጤና ማግኛ ነው። ጸሎት መጥፎ ነገሮችን ያስወግዳል መልካሙን ይጠብቃል።" (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ) ➱ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እደምን ቆያችሁ? በግቢ ጉባኤው የሚደረገው የዓርብ ጸሎት እንደቀጠለ ነው። ሀላችንም እህት ወንድሞቻችንን ቀስቅሰን እንገኝ! ⏰ሰዓት - ዓርብ ጠዋት 12:15 🏠ቦታ - ታች ቤት (ጽርሐ ጽዮን) 🔔🔔🔔Kadhannaaf ka'aa 🔔🔔🔔 "Kadhannaa: Buufata baqannaa obomboleettii jireenyaa keessatti; Warra obomboleettiidhaan dararamaniif dhabannadha.   Qabeenya hiyyeessaa.  Nageenya warra dureeyyii.   Fayyisaa dhukkubsata ykn fayyina argachutti.   Kadhannaan waan badaa ni buqqisa, waan gaarii ni eega." (Qulqulluu Yohaannis Afaan warqee) ➱Jaalatamtoota maatii waaqayyoo akkam turtan? Yaa'ii mooraatti kadhannan taasifamu akkuma itti fufeetti jira. Hundi keenyaa obbollewwan keenya walin wal waamne haa argamnu. ⏰Sa'aatti : Ganama 12:15 🏠Iddoo : Taachi beeti
إظهار الكل...
👍 1
🌻🌿🌺🌻🌿🌺🌻🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺            🥰🥰  ጽዋዓ  ዘማርያም ድንግል🥰🥰 "ኦ ምዕራግ ሐመረ ኖኅ እምድር እስከ ሰማይ ዉሉድኪ ተባረኩ ብኪ" ትርጉም:- ከምድር እስከ ሰማይ የምትደርሽ መሰላል የኖኅ መርከብ ሆይ ልጆችሽ ባንቺ ተመረቁ።             እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም  አመታዊ መታሰቢያ በዓል በሠላም አደረሳችሁ!!!__እያልን በአብነት ት/ት ክፍላችን ከተዘጋጀው የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጽዋዓ እንድትገኙ ስንል በእመቤታችን ስም ጠርተነዎታል። የዕለቱ መሰናዶዎች!     ። ጸሎት(ውዳሴ ማርያም ዜማ)   ፨የልምድ የሕይዎት ተሞክሮ ከተመራቂዎች ፨ ምስባክና ወንጌል  ፨ዝማሬ ፨ ያሬዳዊ ዝማሬ (ወረብ)እንዲሁም ሌሎች..... መርሐ ግብራት ተሰናድተዋል ኑ....🍷ቅመሱ ውድ የግ/ጉ ቤተሰቦች የዛሬው ጽዋ ዕንቁ የአብነት ንዑስ ክፍል ተመራቂ አባላትን የምንሸኝበት እና የአመቱ የመጨረሻ ጽዋችን በመሆኑ በይዘቱና በዓይነቱ ለየት ይላል።ቀርተው ከሚቆጩ በጊዜ መጥተው ይቋደሱ ማሳሰቢያ!ተመራቂዎች ተመራቂ ሁናቹ ኑልን(ደመቅ ብላቹ በሱፍና በቀሚስ) ቦታ ሐመረ ኖኅ ቁጥር 3 አዳራሽ ሰዓት  ምሽት 11:15 ቀን ዓርብ ሰኔ 21 አደራ እንዳያረፍዱ ጊዜ ወርቅ ሕይዎትም አይደል🤔 🌻🌿🌺🌻🌿🌺🌻🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺 ማርያም ድንግል ለነዳይ ንዋየ ወርቁ እመ ነገደ ርሑቀ ወሖረ ዕራቁ ኢየኀዝን ለሲሳዩ እስመ አንቲ ስንቁ(መልከአ ማርያም ለእንግድዓኪ) ትርጉም:-ድንግል ሆይ ለችግረኛ የወርቅ ገንዘቡ አንቺ ነሽ ሩቅ ሀገር ቢሄድ ቢራቆትም አያዝንም ልብስ እና ስንቁ አንቺ አለሽለትና። 🌻🌿🌺🌻🌿🌺🌻🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺 🌻🌿🌺🌻🌿🌺🌻🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺🌿🌻🌺
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
2
⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️ሥርዓተ ማኅሌት ዘሰኔ ሕንፀተ ቤታ"ሰኔ ፳፩" የማንኛውም ወርኃ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ (ሥርዓተ ነግሥ) ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገአርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ እዝነከ ኀቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል። ⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️          መልክዐ ሥላሴ ሰላም ለኲልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል: ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወጸ በሣኅል: እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል: ተፈጸመ ተስፋ አበው #በማርያም_ድንግል: ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል። ዚቅ በዕንቊ ሰንፔር ትትሐነጽ ወበመረግድ: ሃሌ ሉያ ለአብ: ሐጹር የዓውዳ: ትበርህ እምከዋክብት: ሃሌ ሉያ ለወልድ: ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ: #ጽዮን ቅድስት ቤተክርስቲያን: ደብተራ ፍጽምት ነግሥ ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ: ለወልድኪ አምሳለ ደሙ: መሠረተ ሕይወት #ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ: ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ: እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ። ዚቅ እግዚአብሔር ውእቱ ብርሃንኪ ለዓለም: ወመሠረትኪ ለትውልደ ትውልድ: ኢየኀልቅ ብዝኃ ሰላምኪ: ወነገሥት ይትቀነዩ ለኪ: ያመጽኡ አምኃኪ እምርኁቅ ብሔር። ወረብ እግዚአብሔር ውእቱ ብርሃንኪ ለዓለም እግዚአብሔር/፪/ "ወመሠረትኪ"/፪/ እግዚአብሔር/፪/ ⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️ መልክዐ ማርያም ሰላም ሰላም ለዝክረ ስምኪ ሐዋዝ: እምነ ከልበኔ ወቊስጥ ወእምነ ሰንበልት ምዑዝ: #ማርያም_ድንግል ለባሲተ ዓቢይ ትዕዛዝ: ይስቅየኒ ለለጽባሑ ወይነ ፍቅርኪ አዚዝ: ከመ ይሰቅዮ ውኂዝ ለሠናይ አርዝ። ዚቅ በሐ በልዋ ተሳለምዋ: ዕግትዋ #ለጽዮን ወሕቀፍዋ: ደዩ ልበክሙ ውስተ ኃይላ: እንተ ተሐንጸት በስሙ: ወተቀደሰት በደሙ: ወተአትበት በዕጸ መስቀሉ: ጌሡ ኃቤሃ እስመ ሃይለ እግዚአብሔር ላዕሌሃ። ወረብ "በሐ በልዋ"/፪/ ተሳለምዋ/፪/ ዕግትዋ ለጽዮን ወሕቀፍዋ ደዩ ልበክሙ ውስተ ሃይላ ለቤተክርስቲያን/፪/ መልክዐ ማርያም ሰላም ለሥዕርተ ርእስኪ ዘተንዕደ ጽፍሮሁ: ለአቡኪ በከናፍሪሁ: #ማርያም_ድንግል ለእግዚአብሔር ጽርሑ: ለገብርኪ እግዝእትየ እትኅድግኒ እላሁ: ከመ ኢይበሉኒ ፀር አይቴኑመ ምክሁ። ዚቅ ወሀለወት አሐቲ #ድንግል ጽርሐ ቅድሳቱ ይእቲ ለልዑል: መዓዛ አፉሃ ከመ ኮል: ወሥዕርታ ሜላት ፍቱል: ወዲበ ርእሳኒ አክሊል በትእምርተ መስቀል። ወረብ ወሀለወት አሐቲ "#ድንግል"/፪/ አሐቲ ድንግል/፪/ መዓዛ አፉሃ ከመ ኮል/፬/ መልክዐ ማርያም ሰላም ለእስትንፋስኪ ዘመዓዛሁ ሕይወት: ከመ መዓዛ ዕፅ ኅሩይ ዘውስተ ገነት: #ማርያም_ድንግል ቤተ ቅድሳት: ጽንሕኒ ውስተ ሠናይ ወሰውርኒ እሞት: በአክናፍኪ ርግብየ ኅሪት። ዚቅ ገነይነ ለኪ ኦ ወለተ ዳዊት: ጽርሐ ቅድሳቱ ለወልድ: ዘወርቅ ማኅፈድ: ወሡራሬሃ ዘመረግድ። ወረብ "ጽርሐ ቅድሳቱ #ማርያም"/፪/ ዘወርቅ ማኅፈድ/፪/ ወሡራሬሃ ዘመረግድ ዘወርቅ ማኅፈድ/፪/ መልክዐ ማርያም ሰላም ለገቦኪ ዘሐመልማለ ወርቅ ክዳኑ: በከመ ዳዊት ይዜኑ: #ማርያም_ድንግል ለያዕቆብ ሞገሰ ስኑ: በልኒ እግዝእትየ አፈቅረከ አኮኑ: እንዘ ረዳኢትከ አነ ዘይክለከ መኑ። ዚቅ ሃሌ ሃሌ ሉያ አዳም ሕንፄሃ: ሐመልማለ ወርቅ ገበዋቲሃ: #ጽዮንሃ አምኁ ኪያሃ። ወረብ ሕንፄሃ "አዳም"/፪/ ሕንፄሃ ለቤተክርስቲያን/፪/ "ሐመልማለ ወርቅ"/፪/ ገበዋቲሃ ሐመልማለ ወርቅ/፪/ መልክዐ ማርያም ሰላም ለማኅጸንኪ ለእግዚአብሔር ማኅፈዱ: ዘሐነጸኪ የማነ ዕዱ: #ማርያም_ድንግል ምዕዝት ዘእምናርዱ: ኀቤኪ ያንቀዓዱ ለረኪበ ኲሉ መፍቅዱ: ምስለ ካልኡ ዓይንየ አሐዱ። ዚቅ ሃሌ ሃሌ ሉያ: ለቤተክርስቲያን ልዑል ሐነፃ: በጽድቁ ሐወፃ: እምነ ፀሐይ ይበርህ ገፃ። ወረብ ሃሌ ሃሌ ሉያ ለቤተክርስቲያን/፪/ ሐነፃ ልዑል ለቤተክርስቲያን/፪/ መልክዐ ማርያም በዝንቱ ቃለ ማኅሌት ወበዝንቱ ይባቤ: ለዘይስዕለኪ ብእሲ ጊዜ ረከቦ ምንዳቤ: ብጽሒ ፍጡነ ትሰጠዊዮ ዘይቤ: #ማርያም ዕንቊየ ክርስቲሎቤ ወምዕዝተ ምግባር እምከርቤ: ዘጸገየ ማኅጸንኪ አፈወ ነባቤ። ዚቅ ኢይትአጸው አናቅጽኪ: ክቡራት ዕንቊ መሠረትኪ: ሠናይት ሰላማዊት: እንተ ናፈቅራ በጽድቅ: መዓዛ አፉሃ ከመ ኮል። ወረብ ኢይትአጸው አናቅጽኪ ክቡራት ዕንቊ መሠረትኪ/፪/ ሠናይት ሰላማዊት "እንተ ናፈቅራ"/፪/ በጽድቅ/፪/ ማኅሌተ ጽጌ በሠላስ አዕባን ገጸ ሥላሴሁ ለአምሮ: ሐኒጾ ቤትኪ #ድንግል ድኅረ ፈጸመ ሣርሮ: አመ ወረደ ለበዓል ምስሌኪ በአማኅብሮ: እንዘ ይብል ቃለ ለዘምሮ ልዑል ቀደሰ ማኅደሮ: ደናግል ለጽጌኪ ዘበጣ ከበሮ። ዚቅ በሥላሴሁ ሐነጸ ጥቅማ: #ቤተ_ማርያም ሰመየ ስማ: በሥላሴሁ ሐነጸ ጥቅማ። ወረብ በሥላሴሁ "ሐነጸ"/፪/ ጥቅማ #ለማርያም/፪/ ሰመየ ስማ #ቤተ_ማርያም/፪/ ምልጣን ተቀደሲ ወንስዒ ሃይለ ኦ ቤተ እግዚአብሔር: እስመ ናሁ ንጉሥኪ በጽሐ ዘያበርህ ለኪ በሃይሉ: ለዛቲ ቤት ሣረራ አብ ቀዲሙ ለዛቲ ቤት: ሐነጻ ወልድ ለዛቲ ቤት: ወፈጸማ መንፈስ ቅዱስ። አመላለስ፦ ለዛቲ ቤት ሐነጻ ወልድ/2/ ወፈጸማ መንፈስ ቅዱስ/4/ እስመ ለዓለም አመ ትትሐነጽ ኢየሩሳሌም: በዕንቊ ሰንፔር ወበከርከዴን በዕንቊ ክቡር: ዓረፋቲሃኒ ወማኅፈዲሃኒ በወርቅ ንጹሕ: ወመርህባሰ ለኢየሩሳሌም ዘቢረሌ: በዕንቊ አጶሮግዮን ወበዕንቊ ሦፎር ትትገበር: እንዘ ይብሉ በኲሉ ፍናዊሃ ሃሌ ሉያ: ይሴብሕዎ እንዘ ይብሉ: ይትባረክ እግዚአብሔር ዘአልዓላ ለጽዮን እምኲሉ ዓለማት። ➡ከያሬዳውያን ቻናል የተወሰደ መልካም ማኅሌት😊
إظهار الكل...
👍 4
🕊 [  †  እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ሕንጸተ ቤታ [ ሕንጸታ ] በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን። †  ] †  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! † 🕊   †   በዓለ ሕንጸታ    †   🕊 †  በዚሕች ቀን : በሐዲስ ኪዳን የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን በአምላክ እናት ስም ታንጻለች:: ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ :- ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን "ሑሩ ወመሐሩ ኩሎ አሕዛበ" [አሕዛብን ሁሉ ሒዱና አስተምሩ] [ማቴ.፳፰፥፲፱] (28:19) ባላቸው ቃል መሠረት ዓለምን በወንጌል ያርሷት ዘንድ በዕጣ ተካፍለዋታል:: የሰው ልጅ ድኅነቱ የሚፈጸመው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ሲቀበል ነውና [ዮሐ.፮፥፶፮] (6:56) አበው ሐዋርያት ቁርባንን በተመረጡ ሰዎች ቤት እያዘጋጁ ቀድሰው ያቆርቡ ነበር:: በመጀመሪያ በጽርሐ ጽዮን: ቀጥሎም በተለያዩ ሰዎች ቤት እንዲሕ ይከናወን ነበር:: ለጸሎት ሥራ ደግሞ አንዳንዴ ምኩራበ አይሁድን ይጠቀሙ ነበር:: እየቆየ ሲሔድ ግን ከአሕዛብ ያመኑ ሰዎች ቁጥር እጅጉን በዛ:: በተለይ ቅዱስ ጳውሎስ ያሳመናቸው ለጸሎት እያሉ ወደ ጣዖት ቤት መግባት አመጡ:: በዚሕ ምክንያት መምሕራን ሕዝቡን "ካመናችሁ በኋላ እንዴት ወደ ጣዖት ቤት ትገባላችሁ?" ቢሏቸው "እኛ ምን እናድርግ! የምንጸልይበት እንደሆን የለን" ሲሉ መለሱላቸው:: ነገሩ ሲያያዝ ከደጋጉ ሐዋርያት ጳውሎስና በርናባስ ደረሰ:: ወዲያውኑ አንዳንድ ወንድሞች "ለምን አናንጽም" ብለው ነበር:: ቅዱስ ጳውሎስ ግን "ሊቀ ሐዋርያቱ ሳይፈቅድ አይሆንም" አለ:: [ለዚሕ ነው ዛሬም ሊቀ ጳጳስ ካልፈቀደ ቤተ ክርስቲያን የማይታነጸው::] ከዚያ ቅዱሳን ጳውሎስና በርናባስ ሐዋርያቱ ወዳሉበት ሔደው ነገሩን ለቅዱስ ጴጥሮስ አስረዱ:: ሊቀ ሐዋርያቱም "የጌታችን ፈቃዱ መሆኑን እናውቅ ዘንድ ተያይዘን ሱባዔ እንግባ" ብሎ አዋጅ ነገረ:: በዓለም ያሉ ክርስቲያኖች ሁሉ በአንድ ልብ ሱባዔ ገቡ:: በሱባዔአቸው መጨረሻም ክብር ይግባውና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በግርማ ወደ እነርሱ ወረደ:: ሁሉንም ሐዋርያት በደመና ጭኖ ፊልጵስዩስ አደረሳቸው:: ከከተማ ወጣ ብሎ ባለ መሬት ላይም "ቤተ ክርስቲያንን በእናቴ ስም አንጹ" ብሎ አዘዛቸው:: ለቅዱስ ጴጥሮስም ሦስት ዓለቶችን ሰጠው:: እነዚያን መሬት ላይ ተክሎ : ጌታችን ቆሞለት : ሐዋርያቱ እየተራዱት : ግርምት የምትሆን ሦስት ክፍል ያላትን የመጀመሪያዋን ቤተ ክርስቲያን በ52 ዓ/ም በዚህች ቀን አንጿል:: ቤተ ክርስቲያኗን ነገ ጌታችን ቀደሳት የምንል ነንና ይቆየን:: † አምላካችን የድንግል እናቱን ፍቅር : የተቀደሰች ቤቱን ጸጋ : የቡሩካን ሐዋርያቱን በረከት ያሳድርብን:: 🕊 [  † ሰኔ ፳ [ 20 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ] ፩. እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፪. ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ፫. ቅዱሳን ሐዋርያት ፬. ቅዱስ ኤልሳዕ ነቢይ [ ዕረፍቱ ] [    † ወርኀዊ በዓላት     ] ፩. ቅዱስ ቴዎድሮስ ሊቀ ሠራዊት [ሰማዕት] ፪. ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር ፫. ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ ፬. ቅዱስ አፄ ካሌብ ጻድቅ [ ንጉሠ ኢትዮጵያ ] ፭. አባ አሞንዮስ ዘሃገረ ቶና ፮. ቅድስት ሳድዥ የዋሒት † " በድካም : አብዝቼ በመገረፍ : አብዝቼ በመታሠር : አትርፌ በመሞት ብዙ ጊዜ ሆንሁ:: በድካምና በጥረት : ብዙ ጊዜም እንቅልፍ በማጣት : በራብና በጥም : ብዙ ጊዜም በመጦም : በብርድና በራቁትነት ነበርሁ . . . የቀረውን ነገር ሳልቆጥር ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው:: " † [፪ቆሮ. ፲፩፥፳፫-፳፰] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር †
إظهار الكل...
1
ግሩም 😊 መጽሐፍ ነው ይነበብ🙏 ድንቅ ምክር ከመጽሐፋ የተቀነጨበ👇👇 እንደ እውነቱ ከሆነ አንተ ምንም ነህ ፣ ለምንም የማትገባም ነህ ፤ ያለህ ጸጋዎችና ተሰጥኦዎች ሁለ ከእርሱ ናቸውና ሁለም ነገርም ከእርሱ ነውና በአንተ መመካት ምክንያት ለእግዚአብሓር የሚገባውን ክብር አትስረቅ፡፡ ✞ከዕባብ የምትሸሸውን ያህል ከግብዝነት ሽሽ ፤ ከልብህም አውጥተህ ጣለው፡፡ ውጭህ እንደ ውስጥህ ይሁን ፤ …  ሁለን ሰው አክብር ፣ ስሜታቸው እንዲይጎዳም ጠብቅላቸው፡፡ ✞ትምክህት የመርዝ ተክል ፣ ቅናትን ፣ ጥሊቻንና በቀልን የሚያስከትል ወረርሽኝ ነው፡፡ የእግዚአብሔርን ክብር የሚነጥቅ የማይታይ ሌባ ነው፡፡ በሰውና በእግዚአብሓር ፊት የተናቀ የዱያቢልስ ግኝት ነው፡፡ ✞አንድ ሰው ሲያመሰግንህ የወደቅህባቸውን ብዙ ኃጢአቶችና ስኅተቶችህን አስታውስ ፤ ይህ ራስህን የምትቆጣጠርበት መንገድ ነው ፤ እንዲህ ካደረግህ ራስህን እየቀረበልህ ያለው ምስጋና የማይገባ ሆኖ ታገኘዋለህ፡፡ ✞የቱንም ያህል ጠንካራና ኃይለኛ ብትሆን ልትመካ አይገባም ምክንያቱም ይህን ጥንካሬ እግዚአብሔር ለእንስሳትም ሰጥቶአቸዋል፡፡ የነፍስ ጥንካሬ ግን እውነተኛ ክብር ነው፡፡ ሰዎች በአንተ ሊይ የሚናገሩትን ትንሽ ክፉ ቃል በመስማት የምትረበሽ ከሆነ እንዴት ነፍስ ጥንካሬ እንዲኖርህ ትጠብቃለህ? እውነተኛ ጠንካራ ከሆንክ ከባድ ችግርና ጥቃቶች ሲደርሱብህ አትታወክም፡፡ እንዲያውም ችግር ያደረሰብህን ሰው ይቅር ትለዋለህ፡፡ ችግር በሚደርስብህ ጊዜ የምትረበሽና ራስህን መግዛት የማትችል ከሆነ ግን ደካማና ራሱን መግዛት የማይችል ነህ ማለት ነው፡፡ በምኞትና በሕመም ከመሸነፍ በቀር ደካማነት የለም፡፡ ✞መከራና ፈተና ትዕቢትን ከእኛ ነቅለው ያወጡልናል፡፡ ከመታበይና ከከንቱ ውዲሴም ይጠብቀናል፡፡ እግዚብሔርንና ረዳትነቱንም እንድናውቅ ያደርጉናል፡፡ … ✞መከራዎች ቅድስናን ማግኘት እንድንችል ያለማምዱናል፡፡ ስለሚያነቁንም በጥልቅ እንቅልፍ አንወሰድም፡፡ መከራ ያነጻናል ፣ ያስተካክለናል ፤ ያጠራናል ፣ ያጥበንማል፡፡ ያለ #መከራ ራስን ማወቅ በጣም ከባዴ ነው፡፡… መከራ እግዚአብሔርን እንዴንፈሌግና ለእርሱም እንድንበረከክ ያደርገናል፡፡ ✞በሥጋዊ ውበት አትማረክ ፤ ይልቅስ ውስጣዊውን የነፍስ ውበት በመመርመር የሥጋን ውበት ከመንፈስ ውበት ለይ፡፡ የምትረዳው ነገር ሥጋ #የትል ምግብ መሆኑንና የሚበሰብስና ሽታን የሚያመጣ መሆኑን ነው፡፡ ውጪውን አትመልከት ፤ ውስጣዊውን ማንነት የሚቆጣጠረውን ውስጠኛውን ተመልከት እንጂ፡፡ እውነተኛውን ውበት የምትፈልግ ከሆነ ራስህን በበጎነትና በክርስቲያናዊ አኗኗር አስጊጠው፡፡ ክፉ ነገሮችን በማየትና በመጥፎ ጠባይ አትቆሽሽ፡፡ ✞ምናልባት አንድን ሰው ውብና ማራኪ ሆኖ ታየው ይሆናል፡፡ ነፍሱ ግን በክፋት ውስጥ ሰጥማለች ፣ በውስጡ ግን በኃጢአት እየታወከ ነው ፤ በብዙ ጥፋቶች ጥላሸትም ጠቁሮአል፡፡ በአንጻሩ የሚማርክ ገጽታ የሌለው ሰው ሌታይ ትችላለህ ፤ ነፍሱ ግን በበጎነት እና በቅድስና አኗኗር የተዋበች ልትሆን ትችላለች፡፡ ስለዚህ እባክህን ሁሌጊዜ ውስጣዊ ማንነትን መርምር እንጂ ውጪያዊ ውበትን አትመልከት፡፡
إظهار الكل...
👍 2
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.