Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 741
المشتركون
+224 ساعات
+37 أيام
-730 أيام
أرشيف المشاركات
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሀነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቱን ይገልፃል።
#መልካም_የትንሳኤ_በዓል
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
ለኢትዮ ጣሊያን የአይ.ሲ.ቲ አሰልጣኝ መምህራን የክህሎት ክፍተት ስልጠና ተሰጠ፤
በድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት የኮሌጆችን አቅም ለማሳደግና የአሰልጣኝ መምህራንን የክህሎት ክፍተት መሙላት የሚያስችል ስልጠና በተከታታይ በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል የዚሁ አካል የሆነ ለኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የአይ.ሲ.ቲ ትምህርት ክፍል አሰልጣኝ መምህራን window server 2008 ላይ መስጠት ተቸሏል፤
የዊንዶውስ ሰርቨር 2008 በዋናነት ዊንዶውስ ሰርቨር 2008 R2 የሰርቨር ቨርችዋልን ለመስራት ዋና አቅሞችን ይሰጣል ፣ይህም አንድ ድርጅት ፊዚካል ሰርቨሮችን ወደ ጥቂት ሆስት ሰርቨር ስርዓቶች የማዋሃድ አቅም በመስጠት አጠቃላይ የአይቲ ኦፕሬሽን ወጪን በመቀነስ ፋይዳው ከፍ ያለ ይሆናል፤
በዚህም በትምህርት ክፍሉ ከስልጠናው ጥራቱን የጠበቀ ስልጠና ለሰልጣኞች ለመስጠት፤ መምህራኑን በተሻለ ቴ/ጂ ስልጠና እንዲሰጡና እነርሱም የተሻለ ቴ/ጂ ክህሎት ባለቤት እንዲሆኑ በማስቻል ለሚሰሩ ተያያዥ ስራዎች አስፈላጊነቱ ከፍ ያለ መሆኑንና ስልጠናውም ከመምህራኑ ጥያቄ በመነሳት የተሰጠ በመሆኑ ትምህርትና ስልጠናን በተሻለ መልኩ ለመስጠት የሚያስችል እንደሚሆን በቢሮው የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ተናግረዋል፡፡
የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 3/2015 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ከመጋቢት 22 2015 ዓ.ም ጀምሮ በአስተዳደሩ የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር በሚገኘው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ/የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ 2015 ዓ.ም የክህሎት ውድድር ላይ በክላስተር ደረጃ የተደረገውን ውድድር በአሸናፊነት ያጠናቀቁ ተወዳዳሪዎች በቀጣይ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚካሄደው ውድድር የድሬዳዋ አስተዳደርን ለመወከል በክልል ደረጃ የተደረገውን የመጨረሻ ውድድራቸውን አካሂደዋል።
በክልል ደረጃ በተካሄደው ውድድርም ኮሌጃችን የተወከለባቸው ሰባት የሙያ ዘርፎች ሲሆኑ እነሱም:-
1,በኤሌትሪካል/ኤሌክትሮኒክስ
2, በማኑፋክቸሪንግ
3, በአውቶሞቲቭ
4,በኮንስትራክሽን
5,በውድ ዎርክ
6,በአይ.ሲ.ቲ
7,በሆቴልና ቱሪዝም የሙያ ዘርፎች ናቸው።
በውድድሩ ከሁለቱ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጆች አሸናፊ የሚሆኑ ተወዳዳሪዎች በቀጣይ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄደው ውድድር ላይ የድሬዳዋ አስተዳደርን ወክለው የሚሳተፉም ይሆናል።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
መጋቢት 28/2015 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከመጋቢት 22 ጀምሮ በክላስተር ደረጃ ባካሄደው የ2015 ዓ.ም የክህሎት ውድድር የተሳተፉ አስልጣኝ መምህራን እና ሰልጣኝ ተማሪዎች በውድድሩ ያስመዘገቡት ውጤት።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከመጋቢት 22 ጀምሮ እያካሄደ የሚገኘውን የ2015 ዓ.ም የክህሎት ውድድር በዛሬው እለትም ቀጥሎ በተቀሩት የሙያ ዘርፎች ውድድሩን በማካሄድ ላይ ይገኛል ።
በዛሬው ዕለት በተቋማችን በቀጠለው የክህሎት ውድድር በማኑፋክቸሪንግ ፣ በአውቶሞቲቭ ፣ በኤሌክትሪካል/ኤሌክትሮኒክስ እና በኮንስትራክሽን ሙያ ዘርፎች ላይ አሰልጣኝ መምህራንና ሰልጣኝ ተማሪዎች ለውድድሩ በተሰየሙ ዳኞች ፊት ውድድራቸውን አካሂደዋል።
የክህሎት ውድድሩ ሲጠናቀቅ ውድድሩን በበላይነት የሚያጠናቅቁ ተወዳዳሪዎች ኮሌጆቹን እንዲሁም አስተዳደሩን በመወከል በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄደው የክህሎት ውድድር ላይ የሚሳተፉም ይሆናል።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 25/2015 ዓ.ም
ድሬዳዋ
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
