ar
Feedback
EECMYMC-YM

EECMYMC-YM

الذهاب إلى القناة على Telegram

በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ፤ ሮሜ12:11 ለማንኛውም ጥያቄም ሆነ አስተያየት👇👇👇 @EECMYMC_YM_bot

إظهار المزيد
1 104
المشتركون
+124 ساعات
+187 أيام
+4730 أيام
أرشيف المشاركات
የመገናኛው ድንኳን እና የክህነቱ ስርአት ➡️የመገናኛው ድንኳን # በመገናኛው ድንኳን ውስጥ የኢየሱስን ጥላ በስፋት የምናይበት ነው። 👉የመታጠቢያ ሰን - ካህናቱ ወደ ቅድስተ ከመግባቸው በፊት እጅና እግራችውን የሚታጠቡበት - ወደ እግዚያብሔር ለመቅረብ   የመንጻት አስፈላጊነት - በቃሉ በኩል የቤተ ክርስቲያንመንጻት ዕብ 10:22 ኤፌ 5:25-28 👉ይሕብስት ጠረጴዛ - 12 የእስራኤል  ነገድ የሚወክል 12 ሕብስት የያዘ - ካህናት የሚመግብ እግዚአብሔር እንደሆነ - ክርስቶስ የሚያኖረን   " የሕይወት እንጀራ"  መሆኑን 👉የወርቅ መቅረዝ - ሰባት ቅርንጫፍ (ራስ) ያለው ዘወትር የሚበራ - ካህነት በቅድስት ውስጥ ለሚያደርጉት አገልግሎት ብርሀን የሚሰጥ - ኢየሱስ የአለም ብርሀን መሆኑን    ዩሐ 1:9  8:12 9:46 👉የወርቅ እጣን መሰዊያ - ሰባት ቅርንጫፍ ይለው የተቀመመ ዕጣን ዘወትር ይሚጨስበት - መዝ 141:2, ኢሳ 58:7 - በኢየሱስ በስሙ የምንጸለየውን ሁሉ ወደ እግዚአብሔር ይቀርባል   ዩሐ 14:13 ,ዕብ 7:25 👉የቃኪዳን ታቦት - እግዚአብሔርከሕዝብ ጋር ቃል ኪዳን መግባቱን የሚያመላክት - እግዚአብሔር ከሕዝብጋር መሆኑና ሀይሉን የሚገልው ዘጸ 25:22 - የአብ ፍቃድ የፈጸመ ዩሕ 6:38     ጽድቅ በክርስቶስ በኩል መገኘቱን    ሮሜ 3:20-22 👉የምሕረት መክደኛ ( ሁለቱ ኪሩብ የሚቀመጡቸው - የግዚአብሐርንበሕዝብ መካከል መገኘት የሚይመለክት; ሕዝቡ ከእግዚአብሔር ምህረት ለመቀበል ሊቀካህኑ በማስተሰሪይ ቀን የመሥዋት ደም የሚረጭበት - እግዚአብሔር የማቀመበት ዙፍንና በደመና መውረዱን ዘሌ16:2 - ምንም በኢየሱስያምነ ሰው ሁሉ ብምህረት እንደሚሸፍን ( ይቅርታ)   ዕብ 4:16👉በመገናኛው ድንኳን ውስጥ 3 ክፍሎች አሉት ። 1 አደባባዩ 2 ቅድስት 3 ቅድስተ ቅዱሳን    “ኢየሱስም እንዲህ አለው፤ “መንገዱ እኔ ነኝ፤ እውነትና ሕይወትም እኔው ነኝ፤ በእኔ በኩል ካልሆነ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።”   — ዮሐንስ 14፥6 (አዲሱ መ.ት) በመገናኛው ድንኳን ውስጥ አደባባዩ መንገድን የሚያመለክት ሲሆን ቅድስት ደግሞ እውነትን ቅድስተ ቅዱሳን ደግሞ ህይወት  የሚያመለክት ነው። በመገናኛው ድንኳን ወደ እግዚአብሔር መገኘት ለመግባት እነዚን ማለፍ ይጠበቅ ነበር ። ይሄ የተፈቀደው ግን ለሊቀ ካህኑ ብቻ ነው። አሁን ግን በኢየሱስ ክህነት በኩል ወደ አብ መግባት ሆኖልናል።

Track Title ፦ 04 ያ መስህ Volume(ቁጥር)፦ 03 Album Title፦ ያ መስህ Singer Name፦ መስከረም ጌቱ ዝቅ ብሎ መጣ አነሰ ስለኛ ክፋት እንዳረገ ወንበዴ ፍርደኛ የሰው ልጅ እርቃኑን በመስቀል ታየ በዚያ በጐልጐታ በቀራንዮ ቆየ ኧኸ ያ መሲህ ዝቅ አለ ኧኸ ያ ንጉስ ዝቅ አለ ኧኸ እግዚያብሔር ወልድ ሰው ሆነ ኧኸ የአለም ፈጣሪ ዝቅ አለ ተዋረደ ሆነ የተጠላ ኧኸ ተዋረደ መከራውን በላ እንዲያ ሲያናኝቁት አንዳች አልመለሰ ሲዘባበቱበት ሲሰድቡት ታገሰ በዚያ ድቅድቅ ለሊት በምጥ ተጨነቀ የህማም ሰው ሆነ በደዌ ደቀቀ ተንኮል የሌለበት ፃድቅ ሆኖ ሳለ ደዌአችን ወስዶ ስለኛ ቆሰለ የሁላችን በደል በእርሱ ላይ ሆነ ነፍሱን አሳልፎ ለሞት አቀረበ ኧኸ ያ መሲህ ዝቅ አለ ኧኸ ያ ንጉስ ዝቅ አለ ኧኸ እግዚያብሔር ወልድ ሰው ሆነ ኧኸ የአለም ፈጣሪ ዝቅ አለ ተዋረደ ሆነ የተጠላ ኧኸ ተዋረደ መከራውን በላ

#ሐሙስ_28_02_2017 #የአምላኬ_ቃል_አያረጅም ዘጸአት 25 ⁸ በመካከላቸውም አድር ዘንድ መቅደስ ይሥሩልኝ። ⁹ እኔ እንደማሳይህ ሁሉ፥ እንደ ማደሪያው ምሳሌ እንደ ዕቃውም ሁሉ ምሳሌ፥ እንዲሁ ሥሩት። “ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን።” — ዮሐንስ 1፥14 Exo 25 ⁸ Let them make me a sanctuary, that I may dwell among them. ⁹ According to all that I show you, the pattern of the tabernacle, and the pattern of all of its furniture, even so you shall make it. “The Word became flesh, and lived among us. We saw his glory, such glory as of the one and only Son of the Father, full of grace and truth.” — John 1፥14

የኢየሱስ ማዕከላዊነት በኦሪት መፅሀፍ ➡️ የብሉይ ኪዳን መፅሀፍት ሁሉ ስለ ኢየሱስ ያወራሉ ። ““ሕግና ነቢያት እስከ ዮሐንስ ድረስ ሲነገሩ ኖረዋል፤ ከዚያ በኋላ ግን የእግዚአብሔር መንግሥት የምሥራ
የኢየሱስ ማዕከላዊነት በኦሪት መፅሀፍ ➡️ የብሉይ ኪዳን መፅሀፍት ሁሉ ስለ ኢየሱስ ያወራሉ ። ““ሕግና ነቢያት እስከ ዮሐንስ ድረስ ሲነገሩ ኖረዋል፤ ከዚያ በኋላ ግን የእግዚአብሔር መንግሥት የምሥራች ተሰብኮአል፤ ሰውም ሁሉ ወደዚያ ለመግባት ይሻማል።”   — ሉቃስ 16፥16 (አዲሱ መ.ት) ~ጥላ:-የሚመጣውን አካል የሚናገር  ነው ። ነገር ግን በጥላው አካሉን ማወቅ አይቻልም። ጥለውን ለማወቅ ቀድሞ አካሉን ማወቅ ይጠይቃል። ➡️ ብሉይ ኪዳን በተለያየ ሁኔታና መንገድ ስለኢየሱስ ሲናገሩ ቆይተው በመጨረሻ አካሉ የሆነው ኢየሱስ ራሱ መጣ። ዕብራውያን 1 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እግዚአብሔር ከጥንት ጀምሮ በተለያየ ጊዜና በልዩ ልዩ መንገድ በነቢያት በኩል ለአባቶቻችን ተናግሮ፣ ² በዚህ መጨረሻ ዘመን ግን ሁሉን ወራሽ ባደረገውና ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ ለእኛ ተናገረን። ➡️ በኦሪት መፅሀፍት ኢየሱስ በብዙ መንገድ የተገፀ ሲሆን በጥቂቱ ልናያቸው የሞከርነው። 1.የሴቲቱ ዘር(The seed of the women ) 2.የመስዋፅቱ በግ (The Passover lamp ) 3.ህግና ፀጋ(ሙሴ እና ኢየሱስ) 4.የመገናኛው ድንኳን እና የክህነቱ ስርአት

#ረቡዕ_27_02_2017 #የአምላኬ_ቃል_አያረጅም ዕብራውያን 5 ¹ ሊቀ ካህናት ሁሉ ስለ ኃጢአት መባንና መስዋዕትን ሊያቀርብ ከሰው ተመርጦ ለእግዚአብሔር በሆነው ነገር ሁሉ ስለ ሰው ይሾማልና፤ ² እርሱ ራሱም ደግሞ ድካምን ስለሚለብስ፥ ላልተማሩትና ለሚስቱት ሊራራላቸው ይችላል፤ ³ በዚህም ምክንያት ስለ ሕዝብ እንደሚያቀርብ እንዲሁ ስለ ራሱ ደግሞ መስዋዕትን ስለ ኃጢአት ሊያቀርብ ይገባዋል። Heb 5 ¹ For every high priest, being taken from among men, is appointed for men in things pertaining to God, that he may offer both gifts and sacrifices for sins. ² The high priest can deal gently with those who are ignorant and going astray, because he himself is also surrounded with weakness. ³ Because of this, he must offer sacrifices for sins for the people, as well as for himself.

#ማክሰኞ_26_02_2017 #የአምላኬ_ቃል_አያረጅም “ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።” — ዮሐንስ 14፥6 “Jesus said to him, "I am the way, the truth, and the life. No one comes to the Father, except through me.” — John 14፥6

#ሰኞ_25_02_2017 #የአምላኬ_ቃል_አያረጅም ዕብራውያን 1 ¹ ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ ዓይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ፥ ² ሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን፤ Heb 1 ¹ God, having in the past spoken to the fathers through the prophets at many times and in various ways, ² has at the end of these days spoken to us by his Son, whom he appointed heir of all things, through whom also he made the worlds.

⚠️ማስታውቅያ⚠️ #ልዩ_የአምልኮ_ጊዜ #የትምህረት_ጊዜ #ትምህርት #ዝማሬ #አምልኮ ፕሮግራም በሰአቱ ይጀመራል ማንም እንዳያረፍድ ⏰ 10፡00 🗓 ጥቅምት 24 2017 Join us👇 Y.b - htt
⚠️ማስታውቅያ⚠️ #ልዩ_የአምልኮ_ጊዜ #የትምህረት_ጊዜ #ትምህርት #ዝማሬ #አምልኮ  ፕሮግራም በሰአቱ ይጀመራል ማንም እንዳያረፍድ  ⏰  10፡00 🗓  ጥቅምት 24 2017 Join us👇 Y.b - https://youtube.com/@eecmymcym Tm - https://t.me/EECMYMC_YM Fb - https://fb.me/EECMYMCY IG - https://ig.me/EECMYMCY Tk - http://tiktok.com/@EECMYMCY ለየትኛውም ጥያቄና አስተያየት👇 https://t.me/EECMYMC_YM_bot #MekanisaYouth #sundayservice

#ቅዳሜ_23_02_2017 #የአምላኬ_ቃል_አያረጅም ዕብራውያን 4 ¹⁵ ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነ ነው እንጂ፥ በድካማችን ሊራራልን የማይችል ሊቀ ካህናት የለንም። ¹⁶ እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበል በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ። Heb 4 ¹⁵ For we do not have a high priest who cannot be touched with the feeling of our infirmities, but one who has been in all points tempted like we are, yet without sin. ¹⁶ Let us therefore draw near with boldness to the throne of grace, that we may receive mercy, and may find grace for help in time of need.

#አርብ_22_02_2017 #የአምላኬ_ቃል_አያረጅም “እንግዲህ በሰማያት ያለፈ ትልቅ ሊቀ ካህናት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ስላለን፥ ጸንተን ሃይማኖታችንን እንጠብቅ።” — ዕብራውያን 4፥14 “Having then a great high priest, who has passed through the heavens, Jesus, the Son of God, let us hold tightly to our confession.” — Heb 4፥14

"To them we did not yield in submission even for a moment, so that the truth of the gospel might be preserved for you." Galatians 2:5 Preserving the Gospel Truth, guarding it against herecies, and guiding those who stray back to the Truth are Biblical thoughts of God. It's crucial for us to learn, understand, and safeguard the Gospel that has been preached to us, on which we stand, and through which we are saved. The history of the Church reformation was a significant struggle to uphold this Gospel within the Church. When teachings deviating from the eternal salvation by God's grace through faith in Christ alone (#Sola_Gratia #Solus_Christus #Sola_Fide) took place in the Church, the reformation was necessary to reject them. It demanded a commitment to assert that the Word of God is the ultimate Truth (#Sola_Scriptuta) rather than human trends. The Church reformation was a journey that balanced knowledge and passion, understanding and fervor, truth and love. It aimed not to tear down or divide the original Church, nor did it reject its positive aspects, but it always upheld the authority of God's Word (#Sola_Scriptura). Since its ultimate goal was to glorify God (#Soli_Deo_Gloria), the Lord worked effectively through it. God is still seeking a generation that is determined to maintain and defend the Gospel Truth in a balanced manner. Happy Church Reformation Day.

"ለእነዚህ ሰዎች ለአንድ አፍታ እንኳ አልተገዛንላቸውም፤ ይኸውም፣ የወንጌል እውነት ከእናንተ ጋር ጸንቶ እንዲኖር ነው።" ገላትያ 2:5 የወንጌልን እውነት መጠበቅ፣ ከአታላይና አሳች ትምህርቶች መከላ
"ለእነዚህ ሰዎች ለአንድ አፍታ እንኳ አልተገዛንላቸውም፤ ይኸውም፣ የወንጌል እውነት ከእናንተ ጋር ጸንቶ እንዲኖር ነው።" ገላትያ 2:5 የወንጌልን እውነት መጠበቅ፣ ከአታላይና አሳች ትምህርቶች መከላከል፣ የሳቱትን ወደ እውነት መመለስ የእግዚአብሔር መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሃሳብ ነው። ለራሳችንም እንዲሁ የተሰበከልንን፣ የተቀበልነውን፣ የቆምንበትን፣ የምንድንበትን ወንጌል መማር፣ መረዳትና አጥብቆ መያዝ ያስፈልገናል። የቤተክርስቲያን ተሀድሶ ታሪክ ይህንን እውነት ቤተክርስቲያን ዘንድ ጸንቶ እንዲኖር የተደረገ ትግል ነበር። ከእግዚአብሔር ጸጋ የተነሳ በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን ብቻ (#Sola_Gratia #Solus_Christus #Sola_Fide) የሚገኘውን የዘላለም ድነት በሰው ሥራ የሚተኩ ትምህርቶች ቤተክርስቲያን ቦታ ሲይዙ እምቢ ማለትን የጠየቀ ጀግንነት ነው። የእውነት መለኪያውና ምንጩ የእግዚአብሔር ቃል ብቻ (#Sola_Scriptura) እንጂ የሰው ልማዶች አይደሉም ብሎ ለመሟገት ቁርጠኝነትን የጠየቀ ክስተት ነበር። የተሀድሶ ታሪክ እውቀትንና ሙቀትን፣ መረዳትንና ቅንዓትን፣ እውነትንና ቅንነትን በማመዛዘን የተደረገ ጉዞ ነበር። የቀደመችውን ቤተክርስቲያን ለማደስ እንጂ ለማፍረስ ወይም ለመከፋፈል ያላለመ፣ በጎና አዎንታዊ ትውፊቶችን ያልጣለ፣ ነገር ግን በእግዚአብሔር ቃል ስልጣን ላይ ያላመቻመቸ (#Sola_Scriptura) ነበር። የጉዞው ሁሉ ዓላማ ለእግዚአብሔር ክብር ብቻ (#Soli_Deo_Gloria) ስለነበር እግዚአብሔር በሚገባ ሥራውን ሰርቶበታል። እንዲህ ባለ ሚዛናዊ አቋም ዛሬም የወንጌልን እውነት ለመጠበቅና ለመከላከል የሚያልም ትውልድን እግዚአብሔር ይፈልጋል። መልካም የቤተክርስቲያን ተሀድሶ በዓል።

#ሐሙስ_21_02_2017 #የአምላኬ_ቃል_አያረጅም “ስለዚህ የሕዝብን ኃጢአት ለማስተስረይ፥ ለእግዚአብሔር በሆነው ነገር ሁሉ የሚምርና የታመነ ሊቀ ካህናት እንዲሆን፥ በነገር ሁሉ ወንድሞቹን ሊመስል ተገባው።” — ዕብራውያን 2፥17 “Therefore he was obligated in all things to be made like his brothers, that he might become a merciful and faithful high priest in things pertaining to God, to make atonement for the sins of the people.” — Heb 2፥17

#ሰኞ_20_02_2017 #የአምላኬ_ቃል_አያረጅም “እንደዚህም በሌላ ስፍራ ደግሞ፦ አንተ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ካህን ነህ ይላል።” — ዕብራውያን 5፥6 “As he says also in another place,"You are a priest forever,after the order of Melchizedek."” — Heb 5፥6

#ማክሰኞ_19_02_2017 #የአምላኬ_ቃል_አያረጅም “አንተም ወንድምህን አሮንን ከእርሱም ጋር ልጆቹን ከእስራኤል ልጆች መካከል ለይተህ ካህናት ይሆኑልኝ ዘንድ ወደ አንተ አቅርብ፤ አሮንን የአሮንንም ልጆች፥ ናዳብን አብዮድንም አልዓዛርንም ኢታምርንም፥ አቅርብ።” — ዘጸአት 28፥1 “"Bring Aaron your brother, and his sons with him, near to you from among the children of Israel, that he may minister to me in the priest's office, even Aaron, Nadab and Abihu, Eleazar and Ithamar, Aaron's sons.” — Exo 28፥1

17/2/17 የወጣቶች ፕሮግራም አገልጋይ አስቻለው #ሊቀ_ካህን Join us👇 Y.b - https://youtube.com/@eecmymcym Fb - https://fb.me/EECMYMCY IG - https://ig.me/EECMYMCY Tk - http://tiktok.com/@EECMYMCY #MekanisaYouth

#ሰኞ_18_02_2017 #የአምላኬ_ቃል_አያረጅም “እንዲሁ ክርስቶስ ደግሞ ሊቀ ካህናት ሊሆን ራሱን አላከበረም ነገር ግን፦ አንተ ልጄ ነህ እኔ ዛሬ ወልጄሃለሁ ያለው እርሱ ነው፤” — ዕብራውያን 5፥5 “So also Christ did not glorify himself to be made a high priest, but it was he who said to him,"You are my Son.Today I have become your father."” — Heb 5፥5

Repost from EECMYMC-YM
⚠️ማስታውቅያ⚠️ #ልዩ_የአምልኮ_ጊዜ #የትምህረት_ጊዜ #ትምህርት #ዝማሬ #አምልኮ 🛑🛑 ፩. "የክርስቶስ ማዕከላዊነት" ትምህርት ፫ ፪. "አዳዲስ ሰዎችን መጋበዝ አትርሱ።" 🛑🛑 ፕሮግራም በሰ
⚠️ማስታውቅያ⚠️ #ልዩ_የአምልኮ_ጊዜ #የትምህረት_ጊዜ #ትምህርት #ዝማሬ #አምልኮ 🛑🛑 ፩. "የክርስቶስ ማዕከላዊነት" ትምህርት ፫ ፪. "አዳዲስ ሰዎችን መጋበዝ አትርሱ።" 🛑🛑  ፕሮግራም በሰአቱ ይጀመራል ማንም እንዳያረፍድ  ⏰  10፡00 🗓  ጥቅምት 17 2017 Join us👇 Y.b - https://youtube.com/@eecmymcym Tm - https://t.me/EECMYMC_YM Fb - https://fb.me/EECMYMCY IG - https://ig.me/EECMYMCY Tk - http://tiktok.com/@EECMYMCY ለየትኛውም ጥያቄና አስተያየት👇 https://t.me/EECMYMC_YM_bot #MekanisaYouth #sundayservice

⚠️ማስታውቅያ⚠️ #ልዩ_የአምልኮ_ጊዜ #የትምህረት_ጊዜ #ትምህርት #ዝማሬ #አምልኮ 🛑🛑 ፩. "የክርስቶስ ማዕከላዊነት" ትምህርት ፫ ፪. "አዳዲስ ሰዎችን መጋበዝ አትርሱ።" 🛑🛑 ፕሮግራም በሰ
⚠️ማስታውቅያ⚠️ #ልዩ_የአምልኮ_ጊዜ #የትምህረት_ጊዜ #ትምህርት #ዝማሬ #አምልኮ 🛑🛑 ፩. "የክርስቶስ ማዕከላዊነት" ትምህርት ፫ ፪. "አዳዲስ ሰዎችን መጋበዝ አትርሱ።" 🛑🛑  ፕሮግራም በሰአቱ ይጀመራል ማንም እንዳያረፍድ  ⏰  10፡00 🗓  ጥቅምት 17 2017 Join us👇 Y.b - https://youtube.com/@eecmymcym Tm - https://t.me/EECMYMC_YM Fb - https://fb.me/EECMYMCY IG - https://ig.me/EECMYMCY Tk - http://tiktok.com/@EECMYMCY ለየትኛውም ጥያቄና አስተያየት👇 https://t.me/EECMYMC_YM_bot #MekanisaYouth #sundayservice

EECMYMC-YM - إحصائيات وتحليلات قناة تيليجرام @eecmymc_ym