2 485
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-157 أيام
-5230 أيام
أرشيف المشاركات
2 485
የዛሬ 16/01/24 free ods
98% sure odds
ያለምንም ቅድመ ክፍያ በነፃ odd የሚሰጣችሁ የትኛውም ቻናል የለም አብዛኛው ሌባ ነው ብራችሁን ከመበላት ተቆጠቡ !
አንድ ነገር ብቻ ነው የማስቸግራችሁ ቻናሉን Share አርጉት
@old tips
2 485
Todays free bet 15/01/24
ያለምንም ክፍያ ነፃ የሆኑ ኦዶችን በየቀኑ እሰጣቸዋለሁ ከናንተ የሚጠበቀው ቻናሉን ለሁሉም አዳርሱ!
@oldtips
2 485
Todays free bet 15/01/24
ያለምንም ክፍያ ነፃ የሆኑ ኦዶችን በየቀኑ እሰጣቸዋለሁ ከናንተ የሚጠበቀው ቻናሉን ለሁሉም አዳርሱ!
@oldtips
2 485
🔴 “የሰላም ሚኒስቴር ‘አስፈላጊነት አይታየንም’ የሚሉ ኃይሎች ተበራክተዋል” - የፓርላማ አባል
🔴 “ተቋሙ ‘አሁን ያስፈልጋል ወይም አያስፈልግም?’ የሚለውን ፓርላማው ራሱ ቢያየው ነው ትክክል የሚሆነው” - የሰላም ሚኒስትር
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ትላንት ሐሙስ ጥር 2፤ 2016 ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው፤ የሰላም ሚኒስትሩ አቶ ብናልፍ አንዷለም ከፓርላማ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች የሰጡትን ምላሽ እና ማብራሪያ አዳምጧል። በዚሁ ስብሰባ ላይ ጥያቄያቸውን ካቀረቡ የፓርላማ አባላት ውስጥ ሁለቱ፤ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሰላምን የማረጋገጥ ተልዕኮውን በአግባቡ አልተወጣም ሲሉ ተችተዋል።
ሉባባ ሰኢድ የተባሉ የተወካዮች ምክር ቤት አባል “የሰላም ሚኒስቴር ሲባል ከመቼውም [ጊዜ] በላይ ያላሰለሰ የህዝብ ውይይት በማድረግ ችግሩን በመቀነስ፣ ህዝባችን የናፈቀውን እንከን የለሽ ሰላም ያረጋግጣል የሚል ትልቅ እምነት ቢጣልበትም፤ እንዳለመታደል ሆኖ ችግሮች እየተባባሱ መጥተው ወደ ጦርነት እያመሩ ህዝባችንን የበለጠ የጨለመ ተስፋ ላይ እንዲወድቅ አድርጎታል” ብለዋል።
ተቃዋሚውን የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄን (አብን) ወክለው ፓርላማ የገቡት አቶ አበባው ደሳለውም፤ “የሰላም ሚኒስቴር ያለውን አስተዋጽኦ ስናይ በጣም የሚያሳዝን ሁኔታ ነው ያለው” ሲሉ ተመሳሳይ አስተያየት ሰንዝረዋል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ “ርዕዩን እና ተልዕኮውን አልተወጣም። ስልጣን እና ተግባሩን አንዳቸውንም በአግባቡ አልፈጸመም” ሲሉ የነቀፉት የፓርላማ አባሉ፤ “ለዚህ ተቋም የሚውለው ሃብት ለሌሎች የልማት፣ የዲሞክራሲያዊ ተቋማት መዋል አለበት” ብለዋል።
* ለእነዚህ ጥያቄዎች የሰላም ሚኒስትሩ ብናልፍ አንዷለም የሰጡትን ምላሽ ይህን ሊንክ ተጭነው ያድምጡ፦ https://youtu.be/PxSg3BOc6F0
@EthiopianInsider1
2 485
አንድም ተማሪ ለዩኒቨርስቲ ማሳለፍ ያልቻለው ትምህርት ቤት ተግዳሮቶች
ቪዲዮ፦ በኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ፈተና ካስፈተኑ 3,106 መደበኛ ትምህርት ቤቶች መካከል 1,328ቱ አንድም ተማሪ ወደ ዩኒቨርስቲ አለመሳለፋቸው ይታወሳል። በአፋር ክልል አሚባራ ወረዳ የሚገኘው ባድሃሞ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከእነዚህ ትምህርት ቤቶች አንዱ ነው።
ከተመሰረተ ዘንድሮ አምስተኛ ዓመቱን የያዘው ባድሃሞ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፤ ሶስት መቶ ገደማ የሚጠጉ ተማሪዎች በአሁኑ ወቅት የሚማሩበት ነው። ትምህርት ቤቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ተማሪዎቹን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ያስፈተነው ባለፈው ዓመት ነበር። በወቅቱ ፈተናውን ከወሰዱ 75 የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች ውስጥ ሁለት ተማሪዎች ብቻ ናቸው ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት (ሬሚዲያል) ማለፍ የቻሉት። ከትምህርት ቤቱ ወደ ዩኒቨርስቲ ለመግባት የሚያስችለውን ነጥብ ያመጣ ተማሪ የለም።
በአፋር ክልል ደረጃም ቢሆን የተመዘገበው ውጤት በጣም ዝቅተኛ ከሚባሉት የሚመደብ ነው። ባለፈው ዓመት በክልሉ የ12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል፤ ለዩኒቨርስቲ ትምህርት የሚያሳልፈውን 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ ተማሪዎች 19 ብቻ ናቸው። በክልሉ የሚገኙ እንደ ባድሃሞ ያሉ ትምህርት ቤቶች፤ ያለባቸው የመማሪያ ቁሳቁስ እጥረት፣ የአስተማሪዎች ቁጥር ማነስ፣ የቤተ መጽሐፍት እና የቤተ ሙከራ ያለመኖር ችግሮች፤ ለተመዘገበው አነስተኛ ውጤት የትምህርት ባለሙያዎች በምክንያትነት የሚጠቅሷቸው ናቸው። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
* ሙሉ ቪዲዮውን ለመመልከት ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://youtu.be/X4vKMkR_e
@EthiopianInsider1
2 485
Repost from Ethiopia Insider
አንድም ተማሪ ለዩኒቨርስቲ ማሳለፍ ያልቻለው ትምህርት ቤት ተግዳሮቶች
ቪዲዮ፦ በኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ፈተና ካስፈተኑ 3,106 መደበኛ ትምህርት ቤቶች መካከል 1,328ቱ አንድም ተማሪ ወደ ዩኒቨርስቲ አለመሳለፋቸው ይታወሳል። በአፋር ክልል አሚባራ ወረዳ የሚገኘው ባድሃሞ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከእነዚህ ትምህርት ቤቶች አንዱ ነው።
ከተመሰረተ ዘንድሮ አምስተኛ ዓመቱን የያዘው ባድሃሞ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፤ ሶስት መቶ ገደማ የሚጠጉ ተማሪዎች በአሁኑ ወቅት የሚማሩበት ነው። ትምህርት ቤቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ተማሪዎቹን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ያስፈተነው ባለፈው ዓመት ነበር። በወቅቱ ፈተናውን ከወሰዱ 75 የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች ውስጥ ሁለት ተማሪዎች ብቻ ናቸው ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት (ሬሚዲያል) ማለፍ የቻሉት። ከትምህርት ቤቱ ወደ ዩኒቨርስቲ ለመግባት የሚያስችለውን ነጥብ ያመጣ ተማሪ የለም።
በአፋር ክልል ደረጃም ቢሆን የተመዘገበው ውጤት በጣም ዝቅተኛ ከሚባሉት የሚመደብ ነው። ባለፈው ዓመት በክልሉ የ12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል፤ ለዩኒቨርስቲ ትምህርት የሚያሳልፈውን 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ ተማሪዎች 19 ብቻ ናቸው። በክልሉ የሚገኙ እንደ ባድሃሞ ያሉ ትምህርት ቤቶች፤ ያለባቸው የመማሪያ ቁሳቁስ እጥረት፣ የአስተማሪዎች ቁጥር ማነስ፣ የቤተ መጽሐፍት እና የቤተ ሙከራ ያለመኖር ችግሮች፤ ለተመዘገበው አነስተኛ ውጤት የትምህርት ባለሙያዎች በምክንያትነት የሚጠቅሷቸው ናቸው። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
* ሙሉ ቪዲዮውን ለመመልከት ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://youtu.be/X4vKMkR_e7g
@EthiopiaInsiderNews
2 485
በሃዲያ ዞን ለሚገኙ መምህራን ደመወዝ በወቅቱ ባለመከፈሉ፤ 100 ሺህ ገደማ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን ኢሰመኮ ገለጸ
በአዲስ መልክ በተደራጀው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሃዲያ ዞን ለሚገኙ መምህራን “ተገቢው ደመወዝ በወቅቱ ባለመከፈሉ ምክንያት” የመንግስት ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውን እና 100 ሺህ ገደማ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ። በዞኑ ከደመወዝ አለመከፈል ጋር በተያያዘ “ቅሬታ እና ተቃውሞ ባሰሙ” ሰዎች ላይ፤ “ማስፈራራት፣ ዛቻ፣ ድብደባ” እንዲሁም በተለያዩ ጊዜያት “እስራት ጭምር” እንደደረሰባቸው ኮሚሽኑ ገልጿል።
ኢሰመኮ ይህን የገለጸው፤ አዳዲስ የክልል አደረጃጀቶችን ተከትሎ በተለያዩ አካባቢዎች ተከስተዋል የተባሉ የደመወዝ መዘግየት እና መቋረጥን አስመልክቶ ያካሄደውን የሰብአዊ መብቶች ክትትል ምርመራ ውጤት ይፋ ባደረገበት መግለጫው ነው። ኮሚሽኑ የቀረቡለትን አቤቱታዎችን ጥቆማዎች መነሻ በማድረግ፤ በሃዲያ ዞን ስር በሚገኙት የሾኔ እና ሆሳዕና ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም የምሥራቅ ባድዋቾ፣ ምዕራብ ባድዋቾ እና ጎምቦራ ወረዳዎች በመገኘት የመስክ ምልከታ ማድረጉን በመግለጫው ተመልክቷል።
የኢሰመኮ ምርመራ በሸፈናቸው የሃዲያ ዞን አካባቢዎች ያሉ ከ9 ሺህ በላይ የመንግስት ሰራተኞች፤ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ “የተቆራረጠ ክፍያ” ይደርሳቸው እንደነበር መግለጻቸውን ኮሚሽኑ ጠቅሷል። ካለፈው ነሐሴ ወር ጀምሮ ምርመራው እስከ ተከናወነበት ጊዜ ድረስ ደግሞ ደ”መወዝ ሙሉ በሙሉ በመቋረጡ ምክንያት”፤ የመንግስት ሰራተኞቹ “ለከፋ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ችግሮች መጋለጣቸውን” መረዳቱን ኮሚሽኑ በመግለጫው አስታውቋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/12222/
2 485
የህዝብ በዓላትን አከባበር ለመወሰን የተዘጋጀ አዋጅ ለፓርላማ ተመራ
የሚኒስትሮች ምክር ቤት የህዝብ በዓላትን፣ የዕረፍት ቀናትን እና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን በቀረበለት የአዋጅ ረቂቅ ላይ ግብዓቶችን በማከል እንዲጸድቅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መራ። ምክር ቤቱ ከዚህም በተጨማሪ በኢትዮጵያ ህገ መንግስት የተደነገገውን የሜዳይ፣ የኒሻን እና የሽልማት አሰጣጥ ስርዓት ተግባራዊ ማድረግ በሚያስችል የአዋጅ ረቂቅ ላይ ከተወያየ በኋላ በተመሳሳይ ለፓርላማ እንዲተላለፍ ወስኗል።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔውን ያሳለፈውን ዛሬ ረቡዕ ታህሳስ 10፤ 2016 ባደረገው መደበኛ ስብሰባው ነው። ምክር ቤቱ በዛሬው ስብሰባው፤ ከሁለቱ አዋጆች በተጨማሪ ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበትን፣ ካሳ የሚከፈልበትን እና ተነሺዎች መልሰው የሚቋቋሙበትን ሁኔታ ለመወሰን በቀረበለት ማሻሻያ የአዋጅ ረቂቅ ላይም ተወያይቷል።
የአምራች ኢንዱስትሪውን ለማበረታት ባለመ ረቂቅ ፖሊሲ ላይም ተወያይቶ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል ውሳኔ ማሳለፉ ተገልጿል። ምክር ቤቱ ከተወያየባቸው የአዋጅ ረቂቆች አንዱ የሆነውና የህዝብ በዓላትን አከባበር የሚመለከተው ድንጋጌ የተዘጋጀው፤ “ለዜጎች ስነ-ምግባርና ስነ-ልቦና ግንባታ እንዲሁም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦቸው ከፍተኛ በመሆኑ” ምክንያት እንደሆነ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ያወጣው መረጃ ያመለክታል።
ለህዝብ በዓላት እና የእረፍት ቀናት “ሕጋዊ እውቅና መስጠት እና ኃይማኖታዊ፣ ባህላዊ እና ታሪካዊ ሥርዓታቸውን ጠብቀው በብሔራዊ ደረጃ እንዲከበሩ ማድረግ የሚገባ በመሆኑ” አዋጁ መዘጋጀቱን በመረጃው ተጠቅሷል። የአዋጅ ረቂቁ፤ የህዝብ በዓላት “የዜጎችን የእርስ በእርስ መልካም ግንኙነት እና መተሳሰብ የሚያጎለብቱ እንዲሆኑ የሚያስችል” ነው ተብሎለታል።
2 485
ኢቢሲ “ኢትዮጵያን አይመስልም” የሚል ትችት በፓርላማ አባላት ቀረበበት
በዛሬው የተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ አዲስ ዋና ስራ አስፈጻሚ የተሾመለት የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ)፤ “ኢትዮጵያን አይመስልም” የሚል ትችት በፓርላማ አባላት ቀርቦበታል። አንድ የፓርላማ አባል “ኢቢሲ የተወሰነ ብሔር ያለበት ነው” ሲሉ ነቅፈዋል።
ከኦሮሚያ ክልል መቱ ወረዳ ተመርጠው ወደ ፓርላማ የገቡት ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ፤ ኢቢሲ “ከለውጡ ወዲህ ብዙ መሻሻሎች “ ቢያደርግም “አሁንም ግን ብዙ የሚቀሩት ነገሮች አሉ” ብለዋል። “ኢቢሲ ይከተላቸው የነበራቸው ፓተርኖች እንደየጊዜው ይለያያሉ” ያሉት ኡስታዝ ካሚል፤ በቅርብ ጊዜያት በነበሩ ስርዓቶች “የሚንጸባረቅበት እና የሚሄድባቸው ሂደቶች በብዛት ኢትዮጵያን የሚመስሉ አልነበሩም” ሲሉ ተደምጠዋል።
“ብዝሃነታችንን የሚገልጹት፣ የሚያንጸባርቁት፣ የሚሳዩት ሚዲያዎቻችን ናቸው። ስለዚህ የሆነን ማህብረሰብን ብቻ በየጊዜው የሚያንጸባርቁ፣ የሚያሳዩ ሲሆኑ፤ ያ ኢትዮጵያ አይደለም” ያሉት የፓርላማ አባሉ፤ አዲሱ ዋና ስራ አስፈጻሚ “ተቋሙን በትክክል ከላይ ታች መፈተሽ እንደሚገባቸው” አሳስበዋል። ኢቢሲ “ከሰራተኛው፣ ከሚያቀርበው ፕሮግራም፣ ከሃይማኖት እና ከሌሎችም” አንጻር “ኢትዮጵያን የሚመስል ተቋም እንዲሆን አመራሩ ይሰራል” የሚል ተስፋ እንዳላቸውም ኡስታዝ ካሚል ገልጸዋል።
ከኦሮሚያ ክልል ላሎ የምርጫ ክልል የተመረጡት የሆኑት አቶ አየለ ነገሪም ይህንኑ ሃሳብ አስተጋብተዋል።ኢቢሲ ላይ እዚህ ቤት ብዙ ጊዜ ተነጋግረናል። ለምን አነሳችሁ ተብለን ተገምገምናል። የተወሰነ ብሔር ብሔረሰብ ያለበት ነው። የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰብ የለበትም” ሲሉ ተችተዋል።
* ሙሉ ቪዲዮውን ለመመልከት፦ https://youtu.be/6-xyqxTDBmw
@EthiopiaInsiderNews
2 485
አዲሷ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ማናቸው?
ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ዓመታት ያህል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጽህፈት ቤትን በኃላፊነት የመሩት ሜላት ወርቅ ኃይሉ፤ አምስት አባላት ያሉበትን የምርጫ ቦርድ የስራ አመራር ቦርድ በሰብሳቢነት እንዲመሩ በዛሬው ዕለት በፓርላማ ተሹመዋል። የቦርዱ ሰብሳቢ ሹመታቸው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጸደቀላቸው በአንድ ጽምጸ ተዐቅቦ ነው።
ምርጫ ቦርድን ለአራት ዓመት ከመንፈቅ በሰብሳቢነት የመሩት ብርቱካን ሚደቅሳን የተኩት ሜላትወርቅ ኃይሉ፤ ከ30 ዓመት በላይ ሀገራቸውን በተለያዩ የስራ መስኮች ያገለገሉ መሆናቸው በዛሬው የፓርላማ ስብሰባ ላይ ተገልጿል። ተሿሚዋ በሙያቸው ካገለገሉባቸው ተቋማት መካከል መንግስታዊው የጉሙሩክ ባለስልጣን እና የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የሆነው ኒው ጄኔሬሽን ዩኒቨርስቲ ይጠቀሳሉ።
ሜላትወርቅ በኢትዮጵያ ጉምሩክ ባለስልጣን በነበራቸው የአስር ዓመታት ቆይታ፤ የመስሪያ ቤቱን የኦፕሬሽን መምሪያ እንዲሁም የህግ አፈጻጸም መምሪያን በኃላፊነት እስከ መምራት ተጉዘዋል። ኒው ጄኔሬሽን ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ በተቋቋመበት ወቅት፤ የተለያዩ የትምህርት መስኮችን ስርዓተ ትምህርት ቀረጻ የመምራት ሚና መጫወታቸው እና የዩኒቨርስቲ ኮሌጁ የሴኔት አባል ሆነው ማገልገላቸው ተነግሯል።
* ዝርዝሩን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/12198/
* በቪዲዮ ለመመልከት፦ https://youtu.be/j3an7ktzh5o
@EthiopiaInsiderNews
2 485
አዲሱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 36.2 ቢሊዮን ብር የተሻሻለ በጀት አጸደቀ
ባለፈው ዓመት ነሐሴ በይፋ የተመሰረተው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፤ በስሩ ያሉ መዋቅሮቹ ያደረጉትን የአደረጃጀት ለውጥ ታሳቢ ያደረገ የተሻሻለ በጀት አጸደቀ። የክልሉ ምክር ቤት ዛሬ ሐሙስ ታህሳስ 4 ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው፤ ለክልሉ መንግስት የ2016 እቅድ ማስፈጸሚያ የሚሆን 36.2 ቢሊዮን ብር በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በህዝበ ውሳኔ ከቀድሞው የደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችን እና ህዝቦች ክልል በተነጠለበት ወቅት፤ ለነባሩ ክልል ተመድቦ ከነበረው በጀት ውስጥ 54.24 በመቶ ድርሻ እንዲያገኝ ከስምምነት ተደርሶ ነበር። በዚህ ክፍፍል መሰረት ክልሉ 11 ቢሊዮን ብር ያህል በጀት ይዞ ይፋዊ ምስረታውን አከናውኗል።
በነባሩ ክልል የተደረገው የድርሻ ክፍፍል ከዚህ ቀድም የነበሩ መዋቅሮችን ታሳቢ ያደረገ መሆኑ እና የአዲሱ ክልል ማዕከል ድርሻ በግልጽ አለመለየቱ፤ የበጀት ማስተካከያውን ለማድረግ ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸው በዛሬው የምክር ቤት ስብሰባ ላይ ተገልጿል። ከዚህ በተጨማሪ በአዲሱ ክልል ስር ያሉ የተዋቀሩ አዲስ ዞኖች የገቢ እቅዳቸውን ለማሻሻል መፈለጋቸው እና ነባር ዞኖች በበኩላቸው “የገቢ አቅማቸውን አሟጠው ለመጠቀም” በመወሰናቸው የበጀት ማስተካከያው መዘጋጀቱ ተነግሯል።
* ዝርዝሩን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/12179/
* በቪዲዮ ለመመልከት፦ https://youtu.be/gxv3sfFzeUg
@EthiopiaInsiderNews
2 485
አቶ ታዬ ደንደአ “ለጥፋት ተልዕኮ በህቡዕ ሲሰሩ ነበር” በሚል ተወንጅለው በቁጥጥር ስር ዋሉ
በትላንትናው ዕለት ከስልጣናቸው የተነሱት የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታዬ ደንደአ “ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከሚንቀሳቀሱ ጸረ-ሰላም ኃይሎች ጋር በመተሳሰር ለጥፋት ተልዕኮ በህቡዕ ሲሰሩ ነበር” በሚል በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የጸጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ዛሬ ማክሰኞ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ። አቶ ታዬ በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ሲፈጸሙ በቆዩ “የሽብር ተግባራት” በተለይም በእገታዎች ላይ “እጃቸው አለበት” ሲል ግብረ ኃይሉ ወንጅሏል።
ላለፉት ሁለት ዓመታት ገደማ የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ በመሆን ሲሰሩ የቆዩት አቶ ታዬ፤ በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በተጻፈ ደብዳቤ ከኃላፊነታቸው የተነሱት ትላንት ሰኞ ታህሳስ 1፤ 2016 ነበር። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ደብዳቤ ሚኒስትር ዴኤታው ከስልጣናቸው የተነሱበትን ምክንያት ባይጠቅስም፤ ይህንኑ ተከትሎ አቶ ታዬ በይፋዊ የፌስቡክ ገጻቸው ባወጡት ጹሁፍ ግን ከስልጣናቸውን የተነሱት “የወንድማማቾች መገዳደል ይቆም ዘንድ ለሰላም በመወገናቸው” መሆኑን አስፍረው ነበር።
በኢትዮጵያ “በሀገር ህልውና ስም ሲካሄድ ነበር” ያሉትን ጦርነት “ኢትዮጵያውያንን ከማገዳደል አልፎ ሀገሪቷን ያደቀቃት” መሆኑን በጹፋቸው የገለጹት አቶ ታዬ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን “በሰዉ ደም የሚጫወቱ አረመኔ” ሲሉ ወርፈዋቸዋል። የጸጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ በዛሬው መግለጫው፤ አቶ ታዬ በተመደቡበት ከፍተኛ የመንግስት ስልጣን ላይ ሆነው መንግስትን “ገዳይ እና ጨፍጫፊ” እያሉ “በተደጋጋሚ ሲወቅሱ” መደመጣቸውን ጠቅሷል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
* ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/12147/
@EthiopiainsiderNews
