ar
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد
2 485
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-157 أيام
-5230 أيام
أرشيف المشاركات
የዘንድሮውን የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና ያለፉ ተማሪዎች 40 በመቶ ገደማ መሆናቸው፤ ትምህርት ሚኒስቴር ከገመተው አንጻር እንዴት እንደሚመለከቱት ከ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ጥያቄ የቀረበላቸው ዶ/ር ሳሙኤ
የዘንድሮውን የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና ያለፉ ተማሪዎች 40 በመቶ ገደማ መሆናቸው፤ ትምህርት ሚኒስቴር ከገመተው አንጻር እንዴት እንደሚመለከቱት ከ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ጥያቄ የቀረበላቸው ዶ/ር ሳሙኤል “ከነበረው ስጋት አንጻር 40 ከመቶ ተማሪ በመጀመሪያው ዙር በማለፉ በጣም የሚያስደንግጥ ውጤት ነው ብዬ አልወሰድኩም” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል። ይሁንና ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች ብዛት ትምህርት ሚኒስቴር ከጠበቀው አንጻር “ትንሽ ዝቅ ያለ” መሆኑን አልሸሸጉም። የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተናውን ከወሰዱ አጠቃላይ ተማሪዎች ውስጥ 59.3 በመቶው ለመውደቃቸው “አንድ ብቸኛ ምክንያት” እንደሌለ የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ምክንያቶቹን ለማወቅ “ዝርዝር የውጤት ትንተና” እንደሚሰራ ተናግረዋል። የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ያሳለፏቸው ተማሪዎች ብዛት፤ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ካሳለፏቸው አንጻር ከፍተኛ ልዩነት ያለው መሆኑን በተመለከተ ትምህርት ሚኒስቴር ምን አይነት ግምገማ እንዳለው ከ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ለቀረበላቸው ጥያቄ ግን “ቀድሞም ግምት” የነበረ መሆኑን አስረድተዋል። * * ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11471/ @EthiopiaInsiderNews

የቀድሞው የብአዴን ከፍተኛ አመራር አቶ ታደሰ ካሳ በነጻ በእስር እንዲለቀቁ በፍርድ ቤት ተወሰነላቸው ከተፈረደባቸው ስምንት ዓመት ከአምስት ዓመት ወር እስር ውስጥ ግማሽ ያህሉን ያጠናቀቁት የቀድሞው
የቀድሞው የብአዴን ከፍተኛ አመራር አቶ ታደሰ ካሳ በነጻ በእስር እንዲለቀቁ በፍርድ ቤት ተወሰነላቸው ከተፈረደባቸው ስምንት ዓመት ከአምስት ዓመት ወር እስር ውስጥ ግማሽ ያህሉን ያጠናቀቁት የቀድሞው የብሔር አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) ከፍተኛ አመራር አቶ ታደሰ ካሳ፤ ከእስር እንዲፈቱ የፌደራል ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ አስተላለፈ። የሰበር ሰሚ ችሎቱ ይህንን ውሳኔ ያስተላለፈው፤ የአማራ ክልል ጠቅላይ እና ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች እንዲሁም የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጧቸውን ውሳኔዎች በመሻር ነው። ከሌላኛው የብአዴን ጎምቱ ፖለቲከኛ አቶ በረከት ስምኦን ጋር በቀረበባቸው ክስ ተፈርዶባቸው የነበሩት አቶ ታደሰ፤ ከቀረበባቸው ክስ ነጻ ያደረጋቸው ውሳኔ በፌደራል ሰበር ሰሚ ችሎት የተላለፈው ትላንት ሐሙስ ሐምሌ 6፤ 2015 እንደሆነ ጠበቃቸው ህይወት ሊላይ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ሰበር ሰሚ ችሎቱ በትላንትናው ዕለት ውሳኔ ለመስጠት ቀጥሮ የነበረው፤ አቶ ታደሰ ለችሎቱ ያቀረቡትን ቅሬታ ሲመረምር ከቆየ በኋላ መሆኑን ጠበቃቸው ገልጸዋል። አቶ ታደሰ በ2011 ዓ.ም በአማራ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ የቀረበባቸው፤ በስራ አስፈጻሚነት ሲመሩት ከነበረው ጥረት ኮርፖሬት ጋር በተያያዘ ነው። ከቀድሞው የአማራ ክልል ገዢ ፓርቲ ብአዴን ጋር ግንኙነት የነበረው ጥረት ኮርፖሬት፤ “በቂ ጥናት ሳይደረግ ከሌሎች ኩባንያዎች ጋር ለመስራት ውል ገብቷል። በዚህም ድርጅቱ ጉዳት ደርሶበታል” በሚል ነበር አቶ ታደሰ የተከሰሱት። * * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11461/ @EthiopiaInsiderNews

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በታጣቂዎች በተሰነዘረ ጥቃት ስምንት ሰዎች መገደላቸውን ኢሰመኮ አስታወቀ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተከል ዞን ግልገል በለስ ከተማ፣ ባለፈው ሳምንት አርብ ሰኔ 30 በታጣቂ
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በታጣቂዎች በተሰነዘረ ጥቃት ስምንት ሰዎች መገደላቸውን ኢሰመኮ አስታወቀ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተከል ዞን ግልገል በለስ ከተማ፣ ባለፈው ሳምንት አርብ ሰኔ 30 በታጣቂዎች በተሰነዘረ ጥቃት፤ ሶስት የአካባቢ ሚሊሺያዎችን ጨምሮ ስምንት ሰዎች  መገደላቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ። ሌሎች 16 ሰዎች ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸው ህክምና ላይ መሆናቸውን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋሙ ገልጿል።  ኢሰመኮ በታጣቂዎች ጥቃት የሰዎች ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት መድረሱን የገለጸው፤ ትላንት ሐሙስ ሐምሌ 6፤ 2015 ምሽት ባወጣው መግለጫ ነው። ኮሚሽኑ ከጥቃቱ በኋላ አደረግኩት ባለው ክትትል፤ ድርጊቱን የፈጸሙት “ከመንግሥት ጋር በተደረገው ስምምነት መሠረት ትጥቅ ለማስፈታት በሚል አንድ ካምፕ ውስጥ እንዲሰፍሩ የተደረጉ የጉሙዝ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉህዴን) ታጣቂ ቡድን አባላት” መሆናቸውን እንደደረሰበት ገልጿል። ኢሰመኮ የአካባቢውን ነዋሪዎች እና የአስተዳደር ኃላፊዎች በማናገር “ጥቃቱን ያደረሱት የጉህዴን ታጣቂዎች ናቸው” ይበል እንጂ፤ የጉህዴን ምክትል ሊቀመንበር አቶ ደርጉ ፈረንጅ ግን “እነሱ እንደሚያወሩት አይደለም” ሲሉ የኮሚሽኑን መግለጫ ተቃውመዋል። “የጉህዴን ታጣቂ ተብለው የሚጠሩት ታጣቂዎች “ትጥቃቸውን እንዲፈትቱ አድርገናል” የሚሉት አቶ ደርጉ፤ በሌሎች የመተከል ዞኖች የገቡ የጉህዴን ታጣቂዎች ትጥቅ መፍታታቸውን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። * * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11453/ @EthiopiaInsiderNews

የኢሰመኮ ዓመታዊ የሰብዓዊ መብቶች ሪፖርት አሳሳቢ ያላቸው ጥሰቶች ምንድናቸው? ኢሰመኮ በሪፖርቱ ሶስተኛ እና መጨረሻ ክፍል ላይ ክትትል የሚሹ ያላቸውን ጉዳዮች እና ምክረ ሃሳቡን አቅርቧል። ኮሚሽኑ
የኢሰመኮ ዓመታዊ የሰብዓዊ መብቶች ሪፖርት አሳሳቢ ያላቸው ጥሰቶች ምንድናቸው? ኢሰመኮ በሪፖርቱ ሶስተኛ እና መጨረሻ ክፍል ላይ ክትትል የሚሹ ያላቸውን ጉዳዮች እና ምክረ ሃሳቡን አቅርቧል። ኮሚሽኑ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች “በሲቪል ሰዎች ላይ” እየደረሰ ነው ያለውን “ግድያና አካል ጉዳት” በተመለከተ ምክረ ሃሳብ ሰጥቷል። ይህን የሰብዓዊ መብት ጥሰት በተመለከተ የኦሮሚያ ክልል “መጠነ ሰፊ ምርመራን” እንዲያደርግ የጠየቀው ኢሰመኮ፤ የፌደራል እና የክልሉ መንግስት “አፋጣኝ እርምጃ እና ተጨባጭ ዘላቂ መፍትሔ መዘርጋት አለባቸው” ሲል አሳስቧል። ኮሚሽኑ የሰብዓዊ መብቶች ላይ “እጅግ አሉታዊ ተጽዕኖ የሚኖራቸው” ተብለው የተጠቀሱትን ተግባራት “መንግስት በአፋጣኝ ተገቢውን እርምጃ በመውሰድ ሊያስቆመው የሚገባ ነው” ብሏል። ኮሚሽኑ “አሉታዊ ተጽዕኖ የሚኖራቸው” በሚል የዘረዘራቸው ተግባራት፤ አስገድዶ መሰወር፣ የጭካኔ፣ አዋራጅ እና ኢ-ሰብዓዊ አያያዝ መጨመር፣ የኢ-መደበኛ ማቆያዎች መበራከት፣ እንዲሁም የዘፈቀደ እስሮች ናቸው። ዋና ኮሚሽነሩ ዶ/ር ዳንኤል በቀለ በትላንቱ መግለጫው “በዘንድሮው በጀት ዓመት በተለይ ከሰላም ስምምነቱ እና ከሽግግር ፍትህ ሂደቱ በተጨማሪ ሀገራዊውን የሰብዓዊ መብቶችን ሁኔታ ሰፋ ባለ መልኩ የሚያሻሻል ለውጥ እምብዛም አለመኖሩ እና አልፎ አልፎ ከሰብዓዊ መብቶች አጠባበቅ አንጻር ወደ ኋላ የመንሸራተት አደጋ ምልክቶች መታየታቸው፤ ለተስፋ መቁረጥ እና ከሚደረጉ ጥረቶች ለማፈግፈግ ምክንያት ሊሆኑ አይገባም ብለን ለማስታወስ እንወዳለን” ሲሉ ተናግረዋል። * * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11446/ @EthiopiaInsiderNews

ከአዲስ አበባ የመሬት ሊዝ ጨረታ አሸናፊዎች ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ውል ባለመፈጸማቸው፤ ሁለተኛ ለወጡ ተጫራቾች ጥሪ ቀረበ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከአንድ ወር በፊት የመሬት ሊዝ ጨረታ ባካሄ
ከአዲስ አበባ የመሬት ሊዝ ጨረታ አሸናፊዎች ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ውል ባለመፈጸማቸው፤ ሁለተኛ ለወጡ ተጫራቾች ጥሪ ቀረበ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከአንድ ወር በፊት የመሬት ሊዝ ጨረታ ባካሄደባቸው ቦታዎች ላይ ተጫርተው አንደኛ ከወጡ አሸናፊዎች ውስጥ፤ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት በተሰጣቸው ጊዜ ውስጥ ውል አለመፈጸማቸውን የከተማዋ መሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው ውል ካልፈጸሙት አሸናፊዎች ውስጥ “የጨረታ ሂደቱን ለማዛባት ተልዕኮ ተሰጥቷቸው የተጫረቱ” ሊኖሩ ይችላሉ የሚል ግምት እንዳለው ገልጿል። የአዲስ አበባ ከተማ መሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ከአራት ዓመት በኋላ የተደረገውን የመሬት ሊዝ ጨረታ ያወጣው በግንቦት 2015 መጀመሪያ ላይ ነበር። በአስራ አንዱም ክፍለ ከተሞች የሚገኙ 297 ቦታዎች በቀረቡበት በዚህ ጨረታ፤ ተወዳዳሪዎች ለአንድ ካሬ ሜትር መሬት እስከ 700 ሺህ ብር በሚጠጋ የመወዳደሪያ ዋጋ ተጫርተዋል። የከተማይቱ ቢሮ በግንቦት ወር መጨረሻ የ287 ቦታዎች አሸናፊዎች በለየበት ወቅት፤ ለአንድ ካሬ ሜትር 414 ሺህ ብር ካቀረቡ ተጫራች ከፍተኛው የማሸነፊያ ዋጋ መመዝገቡ ይፋ ተደርጓል። የጨረታ አሸናፊዎቹን ዝርዝር ሰኔ 11፤ 2015 ያሳወቀው የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ፤ ተጫራቾች በአስር የስራ ቀናት ውስጥ በጨረታ ሰነዳቸው ላይ ያቀረቡትን ቅድመ ክፍያ ፈጽመው ውል እንዲያስሩ ጥሪ አቅርቦ ነበር። ሆኖም በተሰጣቸው ቀነ ገደብ ውስጥ ውል የፈጸሙት የጨረታ አሸናፊዎች 131 ያህሉ ብቻ መሆናቸውን የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮው የለማ መሬት ማስተላለፍ ቡድን መሪ አቶ ሀብታሙ ተስፋዬ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11441/ @EthiopiaInsiderNews

የአካባቢ ምርጫን በቀጣዩ ዓመት ለማካሄድ፤ በጀትን ጨምሮ ሌሎች “አስፈላጊ ነገሮች” መመቻቸት እንዳለባቸው ምርጫ ቦርድ ገለጸ ለመጨረሻ ጊዜ በ2005 ዓ.ም የተካሄደውን የአካባቢ ምርጫ፤ ገንዘብን ጨም
የአካባቢ ምርጫን በቀጣዩ ዓመት ለማካሄድ፤ በጀትን ጨምሮ ሌሎች “አስፈላጊ ነገሮች” መመቻቸት እንዳለባቸው ምርጫ ቦርድ ገለጸ ለመጨረሻ ጊዜ በ2005 ዓ.ም የተካሄደውን የአካባቢ ምርጫ፤ ገንዘብን ጨምሮ “አስፈላጊ ነገሮች” ከተመቻቹ በሚቀጥለው ዓመት ለማካሄድ መታቀዱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ውብሸት አየለ ተናገሩ። የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች በበኩላቸው በአካባቢያዊ ምርጫ አሸንፈው የታችኛው መዋቅር ምክር ቤቶችን መያዝ እንደሚፈልጉ ገልጸዋል። የአካባቢ ምርጫ በፌደራል መንግስት የ2016 በጀት ዝርዝር ውስጥ ባይካተትም፤ ትላንት ማክሰኞ ሐምሌ 4፤ 2015 በምርጫ ቦርድ አዘጋጅነት በተካሄድ ውይይት ላይ ግን አንድ የመወያያ አጀንዳ ሆኖ ተነስቷል። በአዲስ አበባው ኢንተርሌግዠሪ ሆቴል በተካሄደው በዚሁ ውይይት ላይ፤ የአርጎባ ብሔረሰብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ሀሰን መሃመድ “የአካባቢ ምርጫ በጣም ሊታሰብብት የሚገባ ነው” ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። የቦሮ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ የሆኑት የሆኑት ዶ/ር መብራቱ አለሙ፤ የአካባቢ ምርጫ በቀጣዩ 2016 ዓ.ም እንዲካሄድ እንደሚፈልጉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። ዶ/ር መብራቱ “እኛ በጣም እንፈልገዋለን። ቢያንስ የታችኛው ምክር ቤት በተፎካካሪ ፓርቲዎች እንዲያዝ እንፈልጋለን” ሲሉ የአካባቢ ምክር ቤት በተቃዋሚ ፓርቲዎች ዘንድ ያለውን አስፈላጊነት አብራርተዋል። * * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11436/ @EthiopiaInsiderNews

የ51 የሽብር ወንጀል ተከሳሾችን ጉዳይ የሚመለከቱ ዳኛ በሌላ መተካት፤ በችሎት ቅሬታ አስነሳ አምስት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችን ጨምሮ የ51 የሽብር ወንጀል ተከሳሾችን ጉዳይ ከሚመለከቱት ዳኞች መ
የ51 የሽብር ወንጀል ተከሳሾችን ጉዳይ የሚመለከቱ ዳኛ በሌላ መተካት፤ በችሎት ቅሬታ አስነሳ አምስት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችን ጨምሮ የ51 የሽብር ወንጀል ተከሳሾችን ጉዳይ ከሚመለከቱት ዳኞች መካከል አንዱ መቀየራቸው በተከሳሾች እና ጠበቆቻቸው በኩል ቅሬታን አስነሳ። ጉዳዩን በተለመከተ በጽህፈት ቤት ቅሬታ የቀረበላቸው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት፤ “ዳኞችን መቀየር የፍርድ ቤቱ አስተዳደር ስልጣን ነው” ሲሉ ለጠበቆች ምላሽ ሰጥተዋል ተብሏል። የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሶስተኛ የጸረ ሽብር እና ህገ መንግስታዊ ችሎት ለዛሬ ሰኞ ሐምሌ 3፤ 2015 ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው፤ ተከሳሾች ባቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ላይ ትዕዛዝ ለመስጠት ነበር። ሆኖም በመቅረጸ ድምጽ የተቀዳው የባለፈው የችሎት ውሎ ሂደት ዘግይቶ በመገልበጡ እና አንዱ የችሎት ዳኛ በመቀየራቸው ትዕዛዙ አለመድረሱን ተናግረዋል። በሃምሳ አንዱ ግለሰቦች ላይ በይፋ ክስ ከተመሰረተበት ከሰኔ 1፤ 2015 ጀምሮ መዝገቡን ሲመለከቱ የቆዩት ሶስት ዳኞች ሲሆኑ፤ ከእነርሱ መካከል የግራ ዳኛው በዛሬው ችሎት በሌላ ዳኛ ተተክተው ታይተዋል። ዛሬ በአካል ችሎት ፊት ከቀረቡት 23 ተከሳሾች መካከል የመናገር ዕድል የተሰጣቸው አምስት ተከሳሾች፤ ባቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ላይ ፍርድ ቤቱ ዛሬ ትዕዛዝ ሊሰጥ አለመቻሉ እንዳሳዘናቸው ገልጸዋል። 🔴 ዝርዝሩን ለማድመጥ፦ https://youtu.be/n795FI3lpy8 🔴 ዘገባውን በጹሁፍ ለማንበብ ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11427/ @EthiopiaInsiderNews

ለአዲስ አበባ ከተማ 140.2 ቢሊዮን ብር ጸደቀ የአዲስ አበባ ከተማ የ2016 በጀት 140.29 ቢሊዮን ብር ሆኖ በከተማዋ ምክር ቤት ጸደቀ፡፡ በዘንድሮው የ2016 በጀት ዓመት ለከተማ አስተዳደሩ የተያዘው በጀት ካለፈው በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ40.2 ቢሊዮን ብር ብልጫ አለው፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የከተማዋን በጀት ያጸደቀው ዛሬ እሁድ ሐምሌ 2፤ 2015 ለሁለተኛ ቀን ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው ነው፡፡ በዛሬው የምክር ቤቱ ውሎ ትላንት ለተጀመረው የ2016 በጀት ዓመት የሚውል የበጀት ዝርዝር የያዘ አዋጅ ለምክር ቤት አባላቱ ቀርቧል፡፡ የከተማ ምክር ቤቱ በበጀት አዋጁ ላይ ውይይት ካደረገ በኋላ በ87 ድጋፍ እና በሁለት ድምጸ ተዐቅቦ በአብላጫ ድምጽ የ2016ን በጀት ጸድቋል፡፡ 🔴 በአዲሱ በጀት ዓመት ለአዲስ አበባ ከተማ የተያዘውን በጀት ዝርዝር የተያያዘውን ቪዲዮ ተጭነው ይመልከቱ፡፡ @EthiopiaInsiderNews

የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል በአዲስ አበባ በርካታ “የአማራ ተወላጆች ታስረዋል” አሉ “ጽንፈኛ” እና “ጸረ ሰላም” በሚል ከታሰሩ ከአስር ሺህ በላይ ግለሰቦች መካከል፤ “አብዛኞቹ የአማራ ተወላጆች
የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል በአዲስ አበባ በርካታ “የአማራ ተወላጆች ታስረዋል” አሉ “ጽንፈኛ” እና “ጸረ ሰላም” በሚል ከታሰሩ ከአስር ሺህ በላይ ግለሰቦች መካከል፤ “አብዛኞቹ የአማራ ተወላጆች” መሆናቸውን አንድ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባል ተናገሩ። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በበኩሉ “የምንይዘው ብሔር ለይተን አይደለም” ፤ “የታሰሩ ሰዎች ብዛትም እንደተባለው አይደለም” ሲል የምክር ቤት አባሉን አስተያየት አስተባብሏል። ከየካ ክፍለ ከተማ ገዢው ብልጽግና ፓርቲን ወክለው የከተማይቱን ምክር ቤት የተቀላቀሉት ዶ/ር ካሳ ተሻገር ይህን ያሉት፤ ዛሬ ቅዳሜ ሐምሌ 1፤ 2015 እየተካሄደ በሚገኘው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ላይ በሰጡት አስተያየት ነው። ዶ/ር ካሳ “የታሳሪዎች አያያዝ ሰብዓዊነትን ታሳቢ ያደረገ አይደለም” ሲሉም ተችተዋል፡፡ 🔴 የዶ/ር ካሳ ተሻገርን አስተያየት እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው ምላሽን ይህን ሊንክ ተጭነው ያድምጡ፦ https://youtu.be/OCmrkjeEPDk 🔴 ዘገባውን በጹሁፍ ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11420/ @EthiopiaInsiderNews

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 22.5 ቢሊዮን ብር የኮንዶሚኒየም ግንባታ ብድር መክፈሉን አስታወቀ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለኮንዶሚኒየም ግንባታ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከወሰደው ብድር ውስጥ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 22.5 ቢሊዮን ብር የኮንዶሚኒየም ግንባታ ብድር መክፈሉን አስታወቀ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለኮንዶሚኒየም ግንባታ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከወሰደው ብድር ውስጥ 22.5 ቢሊዮን ብር ያህሉን መክፈሉን የከተማይቱ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታወቁ። የከተማ አስተዳደሩ አሁን ያለበት የኮንዶሚኒየም ቤቶች ብድር 41.5 ቢሊዮን ብር እንደሆነ ከንቲባዋ ገልጸዋል። አዳነች አቤቤ ይህንን ያስታወቁት፤ የከተማዋ ምክር ቤት ዛሬ ቅዳሜ ሐምሌ 1፤ 2015 እያካሄደ ባለው መደበኛ ጉባኤ ላይ ነው። በዚህ ጉባኤ ላይ የከተማ አስተዳደሩን የ2015 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት ከንቲባዋ፤ ባለፉት 12 ወራት የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን አንስተዋል። በከንቲባዋ ሪፖርት ውስጥ የተካተተው አንዱ ጉዳይ፤ የአዲስ አበባ የቤት አቅርቦትን የተመለከተ ነው። 🔴 ዘገባውን በቪዲዮ ለመመልከት👉 https://youtu.be/Hd6f9ao-nIA 🔴 በጹሁፍ ለማንበብ 👉 https://ethiopiainsider.com/2023/11413/ @EthiopiaInsiderNews

በትግራይ ክልል በጦርነት ምክንያት ተቋርጠው የነበሩ ፕሮጀክቶች ውል እንዲታደስ ተወሰነ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ፤ ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በፊት በክልሉ ተጀምረው በስራ ላይ የነበሩ
በትግራይ ክልል በጦርነት ምክንያት ተቋርጠው የነበሩ ፕሮጀክቶች ውል እንዲታደስ ተወሰነ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ፤ ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በፊት በክልሉ ተጀምረው በስራ ላይ የነበሩ ፕሮጀክቶች ውል እንዲታደስ ወሰነ። በጊዜያዊ አስተዳደሩ ቅድሚያ የማይሰጣቸው ፕሮጀክቶች ሊሰረዙ እንደሚችሉ የክልሉ የከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ቢሮ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስታውቋል። በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ፤ የፕሮጀክቶች ውል “በጥናት መሰረት” እንዲታደስ ውሳኔ ያሳለፈው ትላንት ሐሙስ ሰኔ 29፤ 2015 ባካሄደው ስብሰባ ነው። “ውሎቹ የጊዜ ገደብ አላቸው፤ የዋጋ ልዩነት አለ። ስለዚህ [ፕሮጀክቶቹን] አሁን ባለው ሁኔታ እንዴት ማስቀጠል እንችላለን የሚለውን ነው የወሰንነው” ሲሉ የጊዜያዊ አስተዳደሩ የከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ አልማዝ ገብረጻዲቅ የካቢኔውን ውሳኔ ዋና ጭብጥ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስረድተዋል። 🔴 በቪዲዮ ለመመልከት፦ https://www.youtube.com/watch?v=kq-rWp7GkkM 🔴 በጹሁፍ ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11407/ @EthiopiaInsiderNews

+1
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለዶ/ር ደሳለኝ ምን ምላሽ ሰጡ ? ኢትዮጵያ ቀውስ ውስጥ መሆኗና ለዚህም ተጠያቂው ገዢው ብልፅግና ፓርቲና የጠቅላይ ሚኒስትሩ የወደቀ አመራር በመሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከስልጣናቸውን #እንዲለቁና ስልጣናቸውን ለሚቋቋም ጊዜያዊ ሲቪል አስተዳደር እንዲያስረክቡ ፤ ፓርላማውም ተበትኖ ለምርጫ መንገድ እንዲጠርግ በሚል በዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ለተጠየቀው ጥያቄ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ምላሽ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፓርቲያቸውና መንግሥታቸው ላይ ከታቃዋሚ ፓርቲ በኩል የቀረበውን ክስ በተመለከተ " እንዲህ ያለው ንግግር ለዛሬ #ፌስቡክ፣ ለዛሬ #ዩትዩብ ጥሩ ነው ፤ አቶ እንትና እንትና እንዲህ አደረጉ ለሚለው ለፌስቡክ ፍጆታ ጥሩ ነው ለትውልድ እና ሀገር ግን አይጠቅምም " ብለዋል። " ቆም ብለን እኛ ማናየውን በማሳየት ለኢትዮጵያ ህዝብ የሚጠቅመውን ሃሳብ ብናቀርብ ጠቃሚ ነው " ሲሉ ተደምጠዋል። " በኢኮኖሚ፣ በሰላም እና በአንዳንድ ጉዳዮች የቀረቡትን የምንወስዳቸውና የምንሰራባቸው እንደሆነ ምንም ጥያቄ የለውም " ያሉት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ " በጥቅሉ ኢትዮጵያ ጨለማ ውስጥ ናት ከተባለ ግን ከሰሀራ በታች ካሉ ሀገራት በኢኮኖሚ 3ኛ ናት፣ ከምስራቅ አፍሪካ አንደኛ ናት ፣ ትላልቅ ተቋማትን እየገነባች ያለች ሀገርናት የሚል መልስ ሆኖ ያልቃል " ሲሉ ተናግረዋል። ምርጫን በተመለከተ ፤ " ምርጫ ይካሄድ የሚለውን ሃሳብ በጣም አደንቃለሁ ፤ ብዙ ጊዜ የተቃዋሚዎች ችግር ምርጫ አይፈልጉም ዝም ብላችሁ ልቀቁና እኛ እንያዝ ነው የሚሉት ፤ አሁን ምርጫ ይደረግ የሚለው በጣም ጠቃሚ ነው ግን ሶስት ዓመት #መታገስ አለብን " ብለዋል። " በየሳምንቱ ምርጫ ስለማይደረግ ፤ ሶስት አመት ታግሰን ያለንን ሃሳብ ይዘን ቀርበን እኛም ይዘን ቀርበን የኢትዮጵያ ህዝብ የሚፈርደውን ፍርድ በፀጋ መቀበል ነው ፤ የዛሬ ሁለት ዓመት የፈረደውን ፍርድ አልተቀበልኩምና አሁን ፓርላማው ፈርሶ ምርጫ ካልተካሄደ አሁንም ፈርሶ ቢካሄድና ቢመረጥ ካልተመረጥን ይቀጥላል ጉዳዩ በየሁለት አመቱ ምርጫ ለማካሄድ አቅም ስለሚያንሰን በተቀመጠው መንገድ በ5 ዓመት እናደርጋለን " ብለዋል። " ምርጫ ሲደረግ ያሉ ሀሳቦች ለህዝብ ቀርበው እኛ ህዝቡ በሚፈልገው ልክ ካላገለገልንና ካልጠቀምን ህዝቡ በምርጫው ሲቀጣን እጅ ስመን፣ ባንስምም እጅ ነስተን እናስረክባለን ፤ እስከዛ መታገስ ጥሩ ነው ፤ ፍርዱን ለህዝብ እንተወው " ሲሉ መልሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገሪቱ ከገባችበት ቀውስ ጋር በተያያዘ ስልጣናቸውን እንዲለቁ በአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ህዝብ በመረጣቸው የምክር ቤት አባላት ሲጠየቁ የዛሬው ሁለተኛ ነው። የምክር ቤት አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ ከወራት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልጣን በመልቀቅ " ላለው ችግር የመፍትሄው አካል ለመሆን አላሰቡም ወይ ? በሰብዓዊነት ላይ በተፈፀሙ እንዲሁም በማንነት ተኮር የዘር ማጥፋት ፣ የዘር ማፅዳት እና የማንነት ማሳሳት ወንጀሎች ተጠያቂ ለመሆን ምን ያህል ዝግጁ ኖት ? " የሚል ጥያቄ አቅርበው የነበረ። በወቅቱ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ ኃላፊነት መውሰድ ካለብን በጋራ ቢሆን መልካም ስለሆነ " ስልጣን ብንለቅ " ነው የሚባለው ምክንያቱም መንግስት ማለት አስፈፃሚ ብቻ አይደለም የሚል ምላሽ ሰጥተዋቸው ነበር። የዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ንግግር : https://t.me/tikvahethiopia/79527 #TikvahEthiopia @tikvahethiopia

የህዳሴ ግድብ አራተኛ ዙር ሙሌት ከነሐሴ ወር መጨረሻ በፊት እንደማይጠናቀቅ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አስታወቁ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አራተኛ ዙር ሙሌት ከነሐሴ ወር መጨረሻ በፊት እንደማይጠና
የህዳሴ ግድብ አራተኛ ዙር ሙሌት ከነሐሴ ወር መጨረሻ በፊት እንደማይጠናቀቅ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አስታወቁ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አራተኛ ዙር ሙሌት ከነሐሴ ወር መጨረሻ በፊት እንደማይጠናቀቅ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። የዘንድሮው የግድቡ ሙሌት “ለሱዳን እና ለግብጽ በቂ ውሃ መሄዱ እየተረጋገጠ” የሚከናወን መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ይህንን ያሉት ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 29፤ 2015 በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው በሰጡት ማብራሪያ ላይ ነው። በዛሬው የፓርላማ ውሎ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ከተነሱላቸው ጥያቄዎች ውስጥ የህዳሴው ግድብን የተመለከተው ይገኝበታል። ይህንን ጥያቄ ያነሱት ወ/ሮ ጀማነሽ ወልደሚካኤል የተባሉ የምክር ቤት አባል፤ የህዳሴው ግድብ ግንባታ “ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ በጥሩ ሁኔታ እየተሰራ” መሆኑን አንስተው፤ በአጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም አሁን በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ማብራሪያ እንዲሰጥበት ጠይቀዋል። ለፓርላማ አባሏ ጥያቄ ምላሽ የሰጡት አብይ “ህዳሴ በጣም መልከ መልካም ነው። ውብ ነው፤ በጣም ቆንጆ ነው። እንደዚያ ሆኖ ይቀጥላል” ብለዋል። የፕሮጀክቱ ግንባታን በተመለከተ ግን ዝርዝር ምላሽ ሳይሰጡ የቀሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “ወሳኝ milestone” ሲሉ ስለጠሩት የእዚህ ዓመት የግድቡ ውሃ ሙሌት አካሄድ ግን ጥቂት ማብራሪያ አስደምጠዋል። * ሙሉ ዘገባውን ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11394/ @EthiopiaInsiderNews

ምርጫ ቦርድ፤ የወላይታ ዞን ህዝበ ውሳኔን በድጋሚ ለመሰረዝ የሚያስገድዱ ችግሮች አጋጥመውት እንደነበር የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ተናገሩ ድጋሚ በተደረገው የወላይታ ዞን ህዝበ ውሳኔ ላይ፤ የኢትዮጵያ ብ
ምርጫ ቦርድ፤ የወላይታ ዞን ህዝበ ውሳኔን በድጋሚ ለመሰረዝ የሚያስገድዱ ችግሮች አጋጥመውት እንደነበር የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ተናገሩ ድጋሚ በተደረገው የወላይታ ዞን ህዝበ ውሳኔ ላይ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ሂደቱን በድጋሚ “እንዲሰረዝ” የሚያስገድዱ ተግባራት በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ሲፈጸሙ እንደነበር የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ውብሸት አየለ ተናገሩ። የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በህዝበ ውሳኔው ዕለት፤ ምርጫ ቦርድ “ሌላ ውሳኔ እንደሰጠ” አድርገው መልዕክት ሲያስተላልፉ እንደነበርም አቶ ውብሸት ገልጸዋል። የምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ይህንን ያሉት፤ ዛሬ ረቡዕ ሰኔ 28፤ 2015 በተካሄደ የፌዴሬሽን ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ላይ ተገኝተው በሰጡት ማብራሪያ ነው። አቶ ውብሸት በንባብ ለምክር ቤቱ ባቀረቡት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ህዝበ ውሳኔ አጠቃላይ ሪፖርት፤ ምርጫ ቦርድ ህዝበ ውሳኔውን ለማካሄድ ያለፋቸውን ሂደቶች፣ የተገኘውን ውጤት እንዲሁም ያጋጠሙትን ችግሮች ዘርዝረዋል። በ26 ገጾች በተዘጋጀው በዚሁ ሪፖርት ውስጥ በችግርነት ከተጠቀሱ ጉዳዮች ውስጥ፤ በወላይታ ዞን ተከስተው ነበር የተባሉ የህግ ጥሰቶች ይገኙበታል። በወላይታ ዞን ባለፈው ጥር ወር የተካሄደው ህዝበ ውሳኔ እንዲሰረዝ ምክንያት የሆኑ የህግ ጥሰቶችን አጽንኦት ሰጥተው ያነሱት ምክትል ሰብሳቢው፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ 94 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት ተናግረዋል። ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12፤ 2015 በወላይታ ዞን በድጋሚ ህዝበ ውሳኔ ሲያካሄድም ችግሮች እንዳጋጠሙት አቶ ውብሸት በዛሬው ሪፖርታቸው ጠቁመዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11382/ @EthiopiaInsiderNews

የፌዴሬሽን ምክር ቤት “የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል” የፌዴሬሽኑ 12ኛ ክልል ሆኖ እንዲደራጅ ወሰነ የፌዴሬሽን ምክር ቤት “የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል” የኢፌዲሪ 12ኛ ክልል ሆኖ እንዲደራጅ በሙሉ ድምጽ ወሰ
የፌዴሬሽን ምክር ቤት “የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል” የፌዴሬሽኑ 12ኛ ክልል ሆኖ እንዲደራጅ ወሰነ የፌዴሬሽን ምክር ቤት “የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል” የኢፌዲሪ 12ኛ ክልል ሆኖ እንዲደራጅ በሙሉ ድምጽ ወሰነ። የነባሩ የደቡብ ክልል፤ በህዝበ ውሳኔ መሰረት ለሚመሰረተው ለአዲሱ ክልል የስልጣን ርክክብ እንዲያደርግ እና ሂደቱንም እንዲያስፈጽም ምክር ቤቱ ዛሬ ረቡዕ ሰኔ 28፤ 2015 ባካሄደው መደበኛ ጉባኤ ውሳኔ አሳልፏል። በነባሩ ክልል የቀሩ መዋቅሮች፤ ራሳቸውን መልሰው በማደራጀት ባሉበት እንዲቀጥሉም ውሳኔ ተላልፏል።  በዛሬው ዕለት በፌዴሬሽን ምክር ቤት በጸደቀው የህዝበ ውሳኔ ውጤት መሰረት አዲስ ክልል በጋራ የሚያቋቋሙት፤ በነባሩ የደቡብ ክልል የሚገኙት የጌዲኦ፣ የወላይታ፣ የጋሞ፣ ጎፋ፣ የኮንሶ፣ የደቡብ ኦሞ ዞኖች እንዲሁም የቡርጂ፣ የአማሮ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ እና የአሌ ልዩ ወረዳዎች ናቸው። እነዚህ መዋቅሮች በየምክር ቤቶቻቸው ባደረጉት ስብሰባ ያሳለፉትን በክልልነት የመደራጀት ጥያቄ፤ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ያቀረቡት ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ላይ ነበር።  የመዋቅሮቹን ጥያቄ በወቅቱ ባካሄደ ጉባኤ በአብላጫ ድምጽ ያጸደቀው የፌዴሬሽም ምክር ቤት፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ ህዝበ ውሳኔ እንዲያደራጅ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል። በዚህ ውሳኔ መሰረት ምርጫ ቦርድ በአስራ አንዱም የነባሩ የደቡብ ክልል መዋቅሮች ባለፈው ጥር ወር ህዝበ ውሳኔ አካሄዷል። ምርጫ ቦርድ በወቅቱ ይፋ ባደረገው የተረጋገጠ የህዝበ ውሳኔ ውጤት፤ ከወላይታ ዞን ውጭ ያሉት መዋቅሮች ከነባሩ ደቡብ ክልል ወጥተው አንድ የጋራ ክልል ለመመስረት ይሁንታቸውን ሰጥተዋል።  * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11371/ @EthiopiaInsiderNews

የጉራጌ ዞን የደቡብ ክልል ምክር ቤት ተወካይ፤ “በመታወቂያ ዋስ” ከእስር ተለቀቁ ለሁለት ቀናት በእስር የቆዩት የደቡብ ክልል ምክር ቤት አባሉ አቶ ታረቀኝ ደግፌ፤ ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 27፤ 2015 አ
የጉራጌ ዞን የደቡብ ክልል ምክር ቤት ተወካይ፤ “በመታወቂያ ዋስ” ከእስር ተለቀቁ ለሁለት ቀናት በእስር የቆዩት የደቡብ ክልል ምክር ቤት አባሉ አቶ ታረቀኝ ደግፌ፤ ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 27፤ 2015 አመሻሽ ላይ “በመታወቂያ ዋስ” ከእስር መፈታታቸውን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። አቶ ታረቀኝ ዛሬ ረፋድ ላይ፤ የደቡብ ክልል ፖሊስ አባላት ወዴት እንደሆነ ወደ አላወቁት ቦታ “ሊወስዷቸው” ሞክረው እንደነበርም ገልጸዋል። የጉራጌ ዞንን በመወከል የደቡብ ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ታረቀኝ፤ በአዲስ አበባ ከተማ ኮልፌ ቀራኒዮ አካባቢ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በፌደራል ፖሊስ የተያዙት ባለፈው ቅዳሜ ሰኔ 24 ምሽት 2፡30 ገደማ ነበር። አቶ ታረቀኝ ከመኖሪያ ቤታቸው “ትፈለጋለህ” ተብለው ከተያዙ በኋላ፤ በአዲስ አበባ ሜክሲኮ አካባቢ በሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ መወሰዳቸውን ገልጸዋል። አቶ ታረቀኝ በቁጥጥር ስር ሊያውሏቸው የመጡትን የፌደራል ፖሊስ አባላት የፍርድ ቤት የእስር ትዕዛዝ ይዘው እንደሆነ መጠየቃቸውን አስታውሰዋል። ለዚህ ጥያቄያቸው ምላሽ አለማግኘታቸውን የሚናገሩት አቶ ታረቀኝ፤ የደቡብ ክልል ምክር ቤት አባልነት መታወቂያቸውን በማሳየት “ያለመከሰስ መብት ያላቸው” መሆኑን ማስረዳታቸውን ጠቅሰዋል። ያለመከሰስ መብታቸው የተነሳበት “ወረቀት” እንዳለ ቢጠይቁም፤ በተመሳሳይ መልኩ ምላሽ እንዳልተሰጣቸው አብራርተዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11366/ @EthiopiaInsiderNews

የመንግስት ሰራተኞች የደመወዝ ጭማሪ “ለወደፊት በሂደት የሚታይ” መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትሩ አስታወቁ የመንግስት ሰራተኞች የደመወዝ ጭማሪ “ለወደፊት በሂደት የሚታይ” መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ
የመንግስት ሰራተኞች የደመወዝ ጭማሪ “ለወደፊት በሂደት የሚታይ” መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትሩ አስታወቁ የመንግስት ሰራተኞች የደመወዝ ጭማሪ “ለወደፊት በሂደት የሚታይ” መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 27፤ 2015 በተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ተናገሩ። መንግስት የደመወዝ ጭማሪን “ወደፊት የሚያየው”፤ ሊተገብር ካሰበው “የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም” ጋር በተያያዘ መሆኑንም አቶ አህመድ ገልጸዋል። የገንዘብ ሚኒስትሩ ዛሬ በፓርላማ የተገኙት፤ የፌደራል መንግስት ባቀረበው የ2016 በጀት ረቂቅ ሰነድ ላይ ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ነበር። በዚህም መሰረት ሚኒስትሩ ከፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ እንዲሁም ከሌሎች የተወካዮች ምክር ቤት አባላት ጥያቄዎች ቀርበውላቸዋል። ከፓርላማ አባላት የተነሱ አብዛኛዎቹ ጥያቄዎች፤ የቀጣዩ ዓመት በጀት ረቂቅ ለምክር ቤቱ ከቀረበበት ጊዜ አንስቶ በተደጋጋሚ ሲነሱ ከነበሩት ከካፒታል በጀት መቀነስ፣ ከመንገድ ፕሮጀክቶች በጀት ማነስ እንዲሁም ለክልሎች ከሚደረግ የፌደራል መንግስት ድጎማ ጋር የተያያዙ ናቸው። የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በአንጻሩ፤ የመንግስት ሰራተኞችን ደመወዝ ጭማሪ ጉዳይ አንስቷል። * ዝርዝሩን ለማንበብ👉 https://ethiopiainsider.com/2023/11362/ * በቪዲዮ ለመመልከት👉 https://youtu.be/uzIm1ZRphuA @EthiopiaInsiderNews

ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ ተቋማት እገዛ እንድታገኝ፤ የአሜሪካ መንግስት ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቱን የገንዘብ ሚኒስትሩ ተናገሩ የኢትዮጵያ መንግስት እንደ ዓለም ባንክ እና አይ ኤም ኤፍ ካሉ ዓለም አ
ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ ተቋማት እገዛ እንድታገኝ፤ የአሜሪካ መንግስት ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቱን የገንዘብ ሚኒስትሩ ተናገሩ የኢትዮጵያ መንግስት እንደ ዓለም ባንክ እና አይ ኤም ኤፍ ካሉ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት የሚፈልገውን እገዛ እንዲያገኝ፤ የአሜሪካ መንግስት ጠንካራ ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ተናገሩ። መንግስት በዓለም አቀፍ ተቋማት በኩል “የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ለመደገፍ” የፕሬዝዳንት ጆ ባይደን መንግስት በቅርቡ “ጠንካራ አቋሙን” እንደገለጸ የገንዘብ ሚኒስትሩ ለፓርላማ አባላት አስረድተዋል። አቶ አህመድ ይህን የተናገሩት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለ2016 በተዘጋጀው የበጀት ረቂቅ ላይ ላቀረቧቸው ጥያቄዎች ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 27፤ 2015 ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነው። “ከአሜሪካ መንግስት ጋር ያለው የዲፕሎማሲ ግንኙነት እጅግ የተሻለ” ደረጃ ላይ እንደሚገኝ በዚሁ ማብራሪያቸው የገለጹት የገንዘብ ሚኒስትሩ፤ በጦርነቱ ምክንያት የተቋረጠው የአውሮፓ ህብረት የልማት እርዳታ ሊቀጥል እንደሚችል ጥቆማ ሰጥተዋል። ህብረቱ ለኢትዮጵያ የልማት እርዳታ የሚሰጥበትን “multi-annual development program” እንደገና ለማስጀመር “ከጥቂት ወራት በኋላ” ስምምነት እንደሚፈረም አቶ አህመድ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ከዓለም አቀፍ አጋሮች የሚጠብቀው እገዛ በበጀት ረቂቁ ውስጥ እንዳልተካተተ ያረጋገጡት የገንዘብ ሚኒስትሩ፤ ይሁንና መንግስታቸው “የተሻለ ሁኔታ እንደሚኖር” ተስፋ ማድረጉን በንግግራቸው ጠቁመዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11352/ @EthiopiaInsiderNews

“ለቤተ መንግስት ግንባታ የተጠየቀ በጀት የለም፤ እየጸደቀ ያለ በጀትም የለም” የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ቪዲዮ፦ የፌደራል መንግስት “ለአዲስ ቤተ መንግስት ግንባታ ያቀረበው የበጀት ጥያቄም ሆነ እያጸደቀ ያለው በጀት አለመኖሩን” የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ተናገሩ፡፡ አቶ አህመድ ይህንን የተናገሩት ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 27፤ 2015 በተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው፡፡ በዛሬው መደበኛ ስብሰባ የፌደራል መንግስት ባቀረበው 2016 በጀት ላይ ከምክር ቤቱ የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ እንዲሁም ከሌሎች የምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች የገንዘብ ሚኒስትሩ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በዚህ ስብሰባ ላይ ከተነሱ ጥያቄዎች ውስጥ “ለቤተመንግስት እና ገበታ ለሀገር” ፕሮጀክቶች “እየተሰበሰበ ነው” የተባለን “500 ቢሊዮን ብር” የተመለከተው ይገኝበታል፡፡ ይህንን ጥያቄ ያነሱት የተቃዋሚው የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አባል የሆኑት አቶ አበባው ደሳለው፤ የገንዘብ አሰባሰቡ “የመንግስትን አሰራር እና መመሪያ” ተከትሎ እየተፈጸመ ነው ወይ ብለዋል፡፡ እኚሁ የፓርላማ አባል፤ “ይህ ብር የመንግስት ቋት ውስጥ አለ ወይ?” ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ ማብራሪያ እንዲሰጡ ጠይቀዋል፡፡ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ለዚህ ጥያቄ የተወሰነ ማብራሪያ እየሰጡ ባሉበት ወቅት ከሌላው የአብን የፓርላማ አባል አቶ ክርስቲያን ታደለ ተቋርጧል፡፡ “የስነ ስርዓት ጥያቄ” ያነሱት አቶ ክርስቲያን፤ የገንዘብ ሚኒስትሩ የሚሰጡት ምላሽ የምክር ቤቱን “የህግ እና የስነ ስርዓት ጉዳዮችን የጣሰ” እንደሆነ ገልጸው “እርምት እንዲደረግ” ጠይቀዋል፡፡ @ethiopianinsider1

በአማራ ክልል፣ ምስራቅ ጎጃም ዞን የምትገኘው የደጀን ወረዳ ፖሊስ አዛዥ እና ምክትላቸው በተከፈተባቸው ተኩስ ሲገደሉ ሁለት ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የወረዳው የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት ለ“
በአማራ ክልል፣ ምስራቅ ጎጃም ዞን የምትገኘው የደጀን ወረዳ ፖሊስ አዛዥ እና ምክትላቸው በተከፈተባቸው ተኩስ ሲገደሉ ሁለት ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የወረዳው የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስታወቀ። ለወረዳዋ ፖሊስ አዛዦች ህልፈት ምክንያት የሆነውን ተኩስ ከፍቷል የተባለ ተጠርጣሪን ለመያዝ ፍለጋ እየተከናወነ መሆኑንም ጽህፈት ቤቱ ገልጿል። የደጀን ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ዘውዱ ታደለ እና ምክትላቸው ኢንስፔክተር ወርቁ ሽመልስ ጥቃት የተፈጸመባቸው ዛሬ ሰኞ ሰኔ 26፤ 2015 ከቀኑ ስምንት ሰዓት ገደማ እንደሆነ የወረዳው የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታሁን ጋሻዬ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። የፖሊስ አዛዦቹ ላይ ተኩስ የተከፈተባቸው፤ በዛሬው ዕለት በተለያዩ አካባቢዎች እየተሰጠ ያለውን “የስምንተኛ ክፍል ፈተና ደህንነት ለመከታተል ወደ አባይ ሸለቆ ትምህርት ቤት በመኪና እየተጓዙ በነበረበት ወቅት” መሆኑን የኮሚዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት ኃላፊው አስረድተዋል። ሁለቱ የፖሊስ አዛዦች “ግልገሌ” የተባለች ቀበሌ ላይ ሲደርሱ “መንገድ ላይ ሲጠብቃቸው ነበር” በተባለ ግለሰብ ተኩስ እንደተከፈተባቸው አቶ ጌታሁን ተናግረዋል። በዚህ ጥቃት በጥይት የተመቱት የፖሊስ አዛዡ ኢንስፔክተር ዘውዱ እና ምክትላቸው ኢንስፔክተር ወርቁ ወዲያው ህይወታቸው ሲያልፍ፤ ሹፌራቸው “እግሩ ላይ ተመትቶ” ጉዳት እንደደረሰበት ኃላፊው አክለዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11344/ @EthiopiaInsiderNews

AIRDROP ROOM - إحصائيات وتحليلات قناة تيليجرام @oldtips