cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ፍቅር እስከ ጀነት👉👉

#be Allah fkad islamawi tmhrt enmarbetaln✔️ Allah tetekamiwoch yargen Amin🙏 @fkir_fkir Asteyayet kalachu @Fkirrbot

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدلم يتم تحديد اللغةالفئة غير محددة
مشاركات الإعلانات
200
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

አሰላሙ አለይኩም👋 በዚህ ቻናል የሌለ ነገር የለም❌ ሁሉም እዚህ ያገኛሉ ✅መሳጭ አጫጭር ኢስላማዊ ታሪኮች ✅ኢስላሚክ ሳይኮ ✅ቴክኖሎጂ ነክ ነገሮች በቅርብ ቀን ይጠብቁን ✍መረጃ ቶሎ እንዲደርስዎ ለወዳጅዎ share ያርጉ Groupu 👉 @fkir_fkir2 Chanelu👉 @fkir_fkir comment👉 @Fkirrbot
إظهار الكل...
💫ጀግንነት ማለት አለመፍራት አይደለም ጀግንነት ማለት ፍርሀት እንዲያስቆምህ አለመፍቀድ ነው። 💫 🌿🌿🌿🌿🌿🌿 🌿 @fkir_fkir 🌿 🌿 @fkir_fkir 🌿 🌿 @fkir_fkir 🌿 🌿🌿🌿🌿🌿🌿
إظهار الكل...
️አላህን የምትረሳበት ሀብት ድህነትነው ነገር ግን አላህን የምታወሳበት ድህነት ግን ሀብትነው ምክንያቱም አላህን ማውሳት ትልቅ ሀብትነው አላህ እንድያወሳህ አንተም እሱን በደንብ አውሳው። 🌿🌿🌿🌿🌿🌿 🌿 @fkir_fkir 🌿 🌿 @fkir_fkir 🌿 🌿 @fkir_fkir 🌿 🌿🌿🌿🌿🌿🌿
إظهار الكل...
😭ወሏሂ ይሄን ፅሁፍ አይቼ ራሴን መቆጣጠር አልቻልኩም😭 አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ አላህን ፍሩ አላህን ፍሩ ኢተቂላህ ሙሉውን ካላነበቡ አይጀምሩት❗️❗️ አንድ ቀን ጂብሪል(ዐ.ሰ) ያለወትሮው ረሱል ሰዐወ ዘንድ ፊቱ ጠቁሮ መጣ። ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) በዚህ ሁኔታ ሲያዩት ግዜ፦"አንት ጅብሪል ምነው ፊትህ እኮ ተቀየሯል?" አሉት። ጅብሪልም፦"አንተ ሙሀመድ አሁን የመጣሁበት ሰዐት አላህ(ሱ.ወ) የጀሀነም አቀጣጣዮችን እንዲያቀጣጥሏት ባዘዛቸው ሰዐት ነው። ጀሀነም እውነት መሆኗን ላወቀ፣እሳትም እውነት መሆኗን ላወቀ፣የቀብር ቅጣት እውነት መሆኑን ላወቀ፣የአላህ ቅጣት ትልቅ መሆኑን ላመነ ሰው ከሷ መትረፉን ሳያረጋግጥ መረጋጋት የለባትም" ብሎ መለሰላቸው። ረሱል (ሰ.ዐ.ወ)፦"አንተ ጅብሪል እስቲ ስለጀሀነም ንገረኝ" አሉት። ጅብሪልም(ዐ.ሰ)፦"አዎ አላህ ጀሀነምን 1ሺህ አመታት አቀጣጠላት ቀይ እስክትሆን ድረስ ከዚያም 1ሺህ አመታት አቀጣጠላት ነጭ እስክትሆን ድረስ ከዚያም 1ሺህ አመታት አቀጣጠላት ጥቁር እስክትሆን ድረስ.....አሁን /ጀሀነም ጥቁር ጨለማማ ናት።ነበልባሏ እና ፍሟ አይጠፋም። ያ በዕውነት ነብይ አድርጎ በላከህ አላህ እምላለሁ.... የመርፌ ቀዳዳ ያህል ጀሀነም ብትከፈት ዱንያ ላይ ያለ ነገር ሁሉ ከሙቀቷ ብዛት ይቃጠል ነበር። ያ በዕውነት ነብይ አድርጎ በላከህ አላህ እምላለሁ....ከጀሀነም ሰዎች ልብስ አንዷ በሰማይና በምድር መሀከል ብትንጠለጠል ከግማቱ የተነሳ ምድር ላይ ያለ ፍጥረት ሁሉ ይሞት ነበር። ያ በዕውነት ነቢይ አድርጎ በላከህ አላህ እምላለሁ....አላህ ቁርአን ላይ የጠቀሰው የጀሀነም ሰንሰለት አንዷ እንኳን በተራራ ላይ ብትቀመጥ ተራራው እስከ ሰባተኛው መሬት ድረስ ይቀልጣል። ያ በዕውነት በላከህ አላህ እምላለሁ....በምዕራብ አንድ ሰውዬ በጀሀነም ቢቀጣ ኖሮ በምስራቅ ያለው ሰው ከሙቀቷ ብዛት ይቃጠል ነበር። ሙቀቷ ጠንካራ ነው፣ጥልቀቷ እሩቅ/ስምጥ ነው፣ጌጧ ብረት ነው፣መጠጧም የፈላ ውሀ እና ምግል ሲሆን፣ልብሷም ከእሳት የተለካ ነው። 7 በሮች አሏት።ለያንዳንዱ በር የተለያዩ በሮችም አሏቸው ለሴቶችም ለወንዶችም" ብሎ መለሰላቸው። ረሱልም(ሰ.ዐ.ወ)፦"እኛ እንደምንጠቀመው አይነት በር ነው?" ብለው ...ሲጠይቁት ጅብሪልም(ዐ.ሰ)፦" አይ አይደለም ከላይ ወደ ታች የተደረደረ በር ነው።ከአንደኛው በር ወደ ሌላኛው በር ያለው ርቀት 70 አመት ያስኬዳል። እያንዳንዱ በር ከሌላኛው በር ግለቱ በ70 እጥፍ ይበልጣል።የአላህ ጠላቶች ወደጀሀነም ይነዳሉ። ልክ በሯ ላይ እንደደረሱ ዘባኒያ የተባሉ የጀሀነም ወታደሮች በሰንሰለት ይቀበሏቸዋል። ሰንሰለቱን በአፋቸው አስገብተው በመቀመጫዎቻቸው ያስወጡታል። ግራ እጁ ከአንገቱ ጋር ይጠፈራል ቀኝ እጁም ከልቡ ጋር ተጠፍሮ ይታሰራል። እያንዳንዱ ሰው ከሸይጧን ቁራኛው ጋር በሰንሰለት ይጠፈራል።ከዚያምሕ በፊቶቻቸው እየተጎተቱ መላዕክት ደግሞ ከብረት በሆነ መዶሻ ይመቷቸዋል።ከዚህ ጭንቀት ለመውጣት ሲሞክሩ ወደዛው ይመልሷቸዋል"ብሎ መለሰላቸው። ነቢያችንም(ሰ.ዐ.ወ)፦"በነዚህ በሮች የሚገቡት እነማን ናቸው?"ብለው ጠየቁት። ጅብሪልም(ዐ.ሰ)፦ "በታችኛው በር የሚገቡት 1፦ሙናፊቆች 2፦በዒሳ ዐሰ ማዕድ የካዱት 3፦"የፊርዐውን ቤተሰቦች...ሲሆኑ የ አንደኛው በሩ ስም ሀዊያ ይባለል። ሁለተኛው በር ስሙ ጀሂም ሲሆን በሱ የሚገቡት ሙሽሪኮች ናቸው። ሶስተኛው በር ሳብያኖች ነው የሚገቡበት ስሙም ሰቀር ይባላል። በአራተኛው በር ኢብሊስ እና ተከታዮቹ መጁሶችም ይገቡበታል ስሙም ለዟ ይባላል። አምስተኛው በር የሁዶች የሚገቡበት ሲሆን ስሙም ሁጠማ ይባላል። ስድስተኛው በር ስሙ ዐዚዝ ሲሆን የሚገቡበት ክርስቲያኖች ናቸው።"ብሎ ከዘረዘረላቸው በኋላ ሰባተኛውን ለመጥቀስ ፍርሀት ያዘው። ነቢያችንም(ሰ.ዐ.ወ)፦"ሰባተኛውን በር ለምን አትነግረኝም?" ብለው ሲጠይቁት ጂብሪልም(ዐ.ሰ)፦"በሱ በር የሚገቡት ካንተ ዑመት የሆኑ ትላልቅ ወንጀሎችን ሰርተው ሳይቶብቱ/ሳይፀፀቱ የሞቱ ናቸው" ብሎ ሲመልስላቸው ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) እራሳቸውን ስተው ወደቁ። ከዚያም ጅብሪልም የረሱልን(ሰ.ዐ.ወ)ጭንቅላት ታፋው ላይ አሳረፈ።ልክ ሲነቁ ቀና አሉና፦"አንተ ጅብሪል ችግሬ በዛ ሀዘኔም በረታብኝ ከኔ ኡመት ጀሀነም ሚገባ አለ እንዴ?" ብለው ሲጠይቁት ጅብሪልም(ዐ.ሰ)፦" አዎን ካንተ ኡመት የትላልቅ ወንጀል ባለቤቶች ይገባሉ"ብሎ መለሰላቸው፣ የዐይናችን ማረፊያ ከእናት ከአባት በላይ ለኛ አዛኝ የሆኑትም ነቢይ ይሄን ሲሰሙ ተንሰቅስቀው ማልቀስ ጀመሩ።ጅብሪልም አብሯቸው አለቀሰ። 😭😭😭😭/ፊዳከ አቢ ውኡሚ ያ ረሱለላህ/😭😭😭😭 ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) ይህኔ፦"ያጅብሪል አንተም ታለቅሳለክ?" አሉት ። ጅብሪልም(ዐ.ሰ)፦"እንዴት አላለቅስ የኔንስ መጨረሻ በምን አውቃለሁ? እብሊስ እኮ ከመላእክት በላይ አላህን ይገዛ ነበር አላቸው 😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭 ያ አሏህ ያ ረህማን ሙስሊሞች አድርገህ እንደፈጠርከን ሙስሊሞች አድርገህ ውሰደን 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 ይህን ሀዲስ አንተ ጋር ወይም አንቺ ጋር እንዲቀር አታድርጉ ቢያንስ ለ 10 ሰው እንላከው ሼር በማድረግ ለወዳጅ ዘመድዎ ያዳርሱ በማይቋረጠው አጅር ተካፋይ ይሁኑ _-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_- ቻናላችን ለመቀላቀል👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 🌿🌿🌿🌿🌿🌿 🌿 @fkir_fkir 🌿 🌿 @fkir_fkir 🌿 🌿 @fkir_fkir 🌿 🌿🌿🌿🌿🌿🌿
إظهار الكل...
ረመዷን ሚያዝያ 5 ይጀምራል ኢንሻአላህ ነብያችን (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ አንድ ሰው ለሌላው ሰው ረመዷንን ለመጀመሪያ ጊዜ ካሳወቀ እሳት በሱ ላይ ሀራም ትሆንበታለች ስለዚ ሼር እናድርግ አላህ ፆሞ ከሚጠቀሙት ያድርገን ያረብብብብ 🌿🌿🌿🌿🌿🌿 🌿 @fkir_fkir 🌿 🌿 @fkir_fkir 🌿 🌿 @fkir_fkir 🌿 🌿🌿🌿🌿🌿🌿
إظهار الكل...
ምርጥ ትውልዶች ============ ‌ በዑመር (ረድየሏሁ አንሁ) ዘመን ሶስት ወጣቶች አንድ ስውዬን ጎትተው በማምጣት ያዐሚረል ሙእሚኒን ይህ ሰው አባታችንን ገድሏል ሀድ/ ቅጣት/ እንደትወስንበት እንሻለን በማለት ተናገሩ። ‌‌ ለምን ገደልክ ? ሲሉ ዑመር ጠየቀ ‌‌ ‹‹ እኔ የግመል እረኛ ነኝ አንደኛው ግመሌ የአባታቸው መሬት ላይ ካለ ዛፍቅጠል ቀንጥሶ ሲበላ አባታቸው ድነጋይ ወርውሮ ሲመታው ግመሌ ሞተ እኔም እሱ የወረወረውን ድንጋይ አነስቼ ስወረውር መታሁትና ሞተ… ሲል ተናገረ። ‌‌ ‹‹እንደዛ ከሆነ ቅጣት እወስንብሃለሁ! አሉ ዑመር ። ‌‌ ‹‹እሺ ሦስት ቀናትን አቆየኝ …… አባቴ ሲሞት ለኔና ለወንድሞቼ የተወው ከንዝ/የተደበቀ ሃብት/አለ እኔ አሁን እዚሁ ከሞትኩ ከንዙም ይጠፋል ወንድሞቼም ይጠፋሉ (ይቸገራሉ) ስለዚህ ፍቀድልኝና ሄጄ ልምጣ አለ። ‌‌ ታዲያ እሰክትመለስ ዋስ የሚሆንሀ ማነው? በማለት ዑመር (ረድየሏሁ አንሁ) ጠየቁ። ‌‌ ሰውዬው የተሰበሰቡትን ሰዎች ተመለከተ የሚያውቀው የለም…… የእያንዳንዱን ፊት ተመለከተ እና ያ ሰውዬ ሲል ጠቆመ። ‌‌ ያ አባ ዘር ለዚህ ሰው ዋስ ትሆናለህ? በማለት ዑመር (ረድየሏሁ አንሁ) ጠየቁ ‌‌ አዎን ያ አሚረል ሙእሚኒን በማለት መለሰ። ‌‌ ይህ ሰው ካመለጠ ቅጣቱ አንተ ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆን አታውቅም እንዴ? ሲል ዑመር ተገርሞ ጠየቁ ግድ የለም ያአሚረል ሙእሚኒን እኔ ዋስ እሆነዋለሁ …. ሲል አቡዘር መለሰ። ሰውየው ሄደ። ‌‌ አንድ ቀን አለፈ….ሁለተኛው ቀን ተከተለ…በሦስተኛው ቀን ሰውየው ካልመጣ ቅጣቱ አቡዘር ላይ ስለሚፈፀም ሰዎች ተጨነቁ ……… ሆኖም የዛን ቀን ከመግሪብ በፊት ያሰው እያለከለከ መጣ እንደደከመው ገፅታው መስካሪ ነበር። ከዑመር (ረድየሏሁ አንሁ) ፊት ለፊት መጥቶ በመቆም ‌‌ ‹‹ከንዙን ለወንድሞቼ እና ለእናቴ ወንድሞች አስረክቤ መጣሁ አሁን በቁጥጥርህ ስር ሆኛለሁ ቅጣቱን ፈፅምብኝ በማለት ተናገረ። ‌‌ ዑመር (ረድየሏሁ አንሁ) ተገረመ በዚያው ማምለጥ የምትችል ሆነህ እንዴት ተመለስክ? ሲል ጠየቀው። ‌‌ ‹‹ ሰዎች ዘንድ ቃል አክባሪነት/ጠባቂነት/ጠፋ እንዳይባል ፈርቼ ነው›› በማለት መለሰ። ‌‌ ዑመር ወደ አቡዘር ዞሮ ይህን ሰው እንዴት ዋስ ሆነከው? በማለት ጠየቀ ‌‌ ‹‹እኔማ ዋስ የሆነኩት በሰዎች ዘንድ ኸይር (መልካም ስራ) ጠፋ እንዳይባል ፈርቼ ነው›› ሲል አቡ ዘር መለሰ። በሁኔታው የሟች ልጆች ልብ ተነካ በቃ አፉ ብለነዋል ቅጣቱ እንዳይፈፀምበት ሲሉ ተናገሩ ‌‌‌ ዑመር (ረድየሏሁ አንሁ) ለምን? ሲል ጠየቃቸው…..‹‹እኛ ደግሞ በሰዎች መሃል ይቅር መባባል ጠፋ እንዳይባል እንፈራለን›› አሉ ሱብሃነላህ ‌‌ እኔ ደግሞ ሰዎች የሰሙትን አያደርሱም እንዳይባል ሰጋሁ እና ነገርኳችሁ፡፡ 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 🌿 @fkir_fkir 🌿 🌿 @fkir_fkir 🌿 🌿 @fkir_fkir 🌿 🌿🌿🌿🌿🌿🌿
إظهار الكل...
اسلام عليكم وراحمةالله وبركاته ለሰለምቴ እህታችን የእርዳታ ጥሪ فَمَن يَعْمَلْ مِثْقَالَ ذَرَّةٍ خَيْرًا يَرَهُ የብናኝ ክብደት ያክልም መልካምን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡ እህታችን በመስለሟ ምክኒያት ብቻ በደረሰባት በደል ስቃይ ታማ እርዳታችንን ትፈልጋለች ■እህቷ ቁርአን አቃጥላባታለች በምትሰግድበት ቦታ ውሻ እያስገቡ ያሸኑበታል ስድብ ግልፍጫ የዘወትር ቀለቧ የሆነችው ሰለምቴ እህታችን ■አቅፍ ያሳደገችው ታነሽ ወንድሟ አንድ ቀን በአስራ አንደኛው ሰአት እቤታችን በሂወት እያለን አትሰግጅም በማለት በምሳር 🪓ሊቆርጣት ሲል እስር ቤት እንዳትገባ ብለው ተረባርበው በግድያ ወንጀል እንዳይጠየቅ ብቻ ማሀል በመግባት ሂወቷን አትርፈዋል ሰለምቴዋ እጅግ አቋመ ቆራጥ የሆነችው ዙልፍ ግን አላህን ሳላመልከው አንገቴ አይቆረጥም በማለት ከቤት አምልጣ ቤት ተከራይታለች ■በዚህ ሁኔታ ሂወቷን ስትመራ አባቷ በቆራጥነቷ በእጇ ሰለመ አብሯት ተቀመጠ ቅድመ ማወቅ ያለበትን ነገረሮች ካስተማረችው በኃላ ትንሽ ቆይተው በሞት ተለዯት የአባቷን ሀዘን ቻል አድርጋ ንሮዋን እየገፍች ነው ግን በመንገድ የግድያ ሙከራዎችና ዛቻዎች ከቤተሠብ ይሰነዘርባታል በመሆኑም ግን ታመመች አስም ያዛት አሁን እጅ ሰጠች የቤት ክራይም መክፈል አልቻለችም መታከማም የላትም እንረባረብ እንርዳት የሴቶችን ጉዳይ አደራ እንወጣ إِن تُبْدُوا الصَّدَقَاتِ فَنِعِمَّا هِيَ ۖ وَإِن تُخْفُوهَا وَتُؤْتُوهَا الْفُقَرَاءَ فَهُوَ خَيْرٌ لَّكُمْ ۚ وَيُكَفِّرُ عَنكُم مِّن سَيِّئَاتِكُمْ ۗ وَاللَّهُ بِمَا تَعْمَلُونَ خَبِيرٌ “ምጽዋቶችን ብትገልጹ እርሷ ምንኛ መልካም ናት፡፡ ብትደብቋትና ለድኾች ብትሰጧትም እርሱ ለናንተ በላጭ ነው፡፡ ከኃጢአቶቻችሁም ከእናንተ ያብሳል፡፡ አላህም በምትሠሩት ሁሉ ውስጠ ዐዋቂ ነው።” (አል-በቀራ ፡ 271) ኢብኑል ቀዪም ረሂመሁሏህ እንዲህ ይላሉ:- "ሰደቃ የሚሰጥ የሆነ ሰው የሚሰጠውን ሰደቃ በምስኪኑ እጅ ከማረፉ በፊት በአላህ እጅ ላይ እንደሚያርፍለት ቢያውቅ ኖሮ ተቀባዩ ከሚያገኘው የደስታ ስሜት የበለጠ ሰጪው ይደሰት ነበር::" ( مدارج السالكين) የአላህ መልክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- "ሰደቃ ማውጣት ገንዘብን አይቀንሰውም። አንድ የአላህ ባርያ ይቅር ባይነቱ ልቅና እንጂ ሌላን አይጨምረውም። ማንኛውም ሰው ለአላህ ሲል አይተናነስም አላህ ከፍ ቢያደርገው እንጂ።" 【ሙስሊም ዘግበውታል】 ኢብኑ ተይሚያ ረሒመሁላህ ተዓላ እንዲህ ብለዋል፦ "ሰደቃ ልክ እንደ ውጊያ ነው። ፈሪ ሲርገፈገፍበት ጀግና ይፀናበታል።" الَّذِي خَلَقَ الْمَوْتَ وَالْحَيَاةَ لِيَبْلُوَكُمْ أَيُّكُمْ أَحْسَنُ عَمَلًا ۚ وَهُوَ الْعَزِيزُ الْغَفُورُ ያ የትኛችሁ ሥራው ይበልጥ ያማረ መኾኑን ሊሞክራችሁ ሞትንና ሕይወትን የፈጠረ ነው፡፡ እርሱም አሸናፊው መሓሪው ነው፡፡ ከዕብ ብን ዑጀር (ረዐ) ባስተላለፉት መሰረት ነቢዩ ﷺ ‹‹ውሃ እሳትን እንደሚያጠፋ ሁሉ ሰደቃ ኃጢአትን ያጠፋል፡፡›› [በትርምዚ የተዘገበ] ብለዋል፡፡ ከአቡ ሁረይራ (ረዐ) በተላለፈው መሰረት የአላህ መልእክተኛ ﷺ ‹‹ከጥሩ ሥራ የተገኘ - አላህ መልካሙን እንጂ አይቀበልምና - አንዲት የተምር ፍሬ ያህል ምጽዋት የሰጠን ሰው አላህ በቀኝ እጁ ይቀበለዋል፤ከዚያም አንዳችሁ የፈረሱን ግልገል ተንከባክቦ እንደሚያሰድገው ሁሉ (የተምር ፍሬ ምንዳው) ተራራን እስኪያክል ድረስ ያሳድገዋል፡፡›› [በቡኻሪና ሙስሊም የተዘገበ] ብለዋል አካውቷ ኢትዮጵያ ንገድ ባንክ 100033918918 @ihlas_tube @ihlas_tube
إظهار الكل...
إظهار الكل...
4_5992480818264545759.mp313.30 MB
የባል ―እና ―ሚስት― የሀላል ፍቅር ጨዋታ በግጥም 💞💞💞💞💞💞💞💞💞💞💞💞💞💞💞💞 ❤ባል :― አንቺ የኔ ፍቅር የህይወት ጨረቃ ልቤ ይከፋዋል ሳጣሽ ለደቂቃ ሴቶች ብዙ ናቸው አንቺ ግን ልዩ ነሽ ህይወቴን አድሻት ካጠገቤ ሁነሽ ❤ሚስት― አንተ የኔ ፍቅር የህይወት ነፀብራቅ ፍቅርክ ምግቤ ነው ከጎኔ አትራቅ ወንዶች ብዙ ናቸው አንተ ግን ልዩ ነክ ፍቅርከን መግበኝ ካጠገቤ ሁነክ። ❤ባል:― የትዳር አጋሬ የልጆቼ እናት ደስታዬ አለሜ የሀላል ሚስቴ ነች ጌታየ ይመስገን እሷን አድሎኛል ውዴን የመሰለ ከቶ የት ይገኛል ❤ሚስት:― የልጆቼ አባት የትዳሬ አጋር ተስፋዬ ብሩህ እስካለሁ ካንተ ጋር መኖርክ መኖሬ መጥፋትክ መጥፋቴ ሳጣክ ቅር ይለኛል አትጥፋ ከፊቴ ❤ባል:― የሽቶ መኣዛ የቴምር ጭማቂ ሁቢ ማር ወለላ ሁሌም ተናፋቂ ጣፈጭ ነገር ሁሉ አንቺን ይመስሉኛል ብቻ ምን ልበልሽ… ቃላቶች ያጥሩኛል! ❤ሚስት:― የዐይኔ ማረፊያ የህይወቴ ፀደይ የፊትክ ብርሃን ይበልጣል ከፀሐይ የረህማን ፅጦታ የጀሊሉ ኒዕማ አንጀቴ ይርሳል ድምፅክን ስሰማ ❤ባል:― ሚስቱን የሚመታ የትዳር አጋሩን የፍቅር አይደለም ሳስበው ነገሩን ውዷ ባለቤቴ ክብርሽ ይከበር አንቺን የመታው ቀን እጄ ይሰበር ❤ሚስት:― እኔ እንክትክት ልበል እኔ ልሰባበር እሾክ አይውጋብኝ እንኳንስ መሰበር የፍቅር አርበኛ ፊትአውራሪ ጀግና አንተ መውድድ እንጂ ዱላ መች ታውቅና ❤ባል: እኔ እዚህ ጎራ አንቺ ወዲያ ማዶ ልቤ አረረልሽ በፍቅርሽ ማገዶ የልቤ በረዶ መዳኒቴ ነሽ ውዷ ባለቤቴ ሁቢ እንዴት ነሽ ❤ሚስት:― ፈረስ አይጋልበው በበቅሎ አይደረስ በርሬ እንዳልመጣ ያለክበት ድረስ ውዱ ባለቤቴ ፍቅርክ ለበለበኝ አሁንስ ከብዶኛል በዱአክ አስበኝ @fkir_fkir @fkir_fkir
إظهار الكل...
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.