ar
Feedback
EECMY - School (online class)

EECMY - School (online class)

الذهاب إلى القناة على Telegram

This channel is created with the thought of teaching students by supplying important files. Please pay attention.

إظهار المزيد
487
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+17 أيام
+230 أيام
أرشيف المشاركات
በእንጦጦ ወንጌላዊት አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት ከወረዳ -2 በመጡ የደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ስለ ቆሻሻ አወጋገድና የቅጣት ህጎችም ጭምር በ11/3/2017ዓ .ም.ጧት የሰንደቅ ዓላማ ሰልፍ ስነ-ሥርዓት ላይ ለት/ቤቱ ማሕበረሰብ በሙሉ ግንዛቤ የማስጨበጥ ተግባር በጥሩ ሁኔታ በባለሙያው ተሰጥቷል።የፎቶግራፉ መግለጭም ሲታይ -

የተከበራችሑ የተማሪዎቻችን ወላጆች/አሣዳጊዎች ከሕዳር 16 እስከ ሕዳር 19/2017 ዓ.ም የ1ኛ ሩብ አመት ለተማሪዎች ፈተና ሥለሚሠጥ በወጣው መርሐግብር መሠረት ልጆች እንዲያጠኑ እንዲከታተሉልን እያሣሠብን የሕዳር ወር የትምህርት ክፍያም በማጠናቀቅ ተማሪዎች በነፃነት እንዲፈተኑ እንዲያደርጉልን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡ ት/ቤቱ

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia ከፍተኛ ክርክር የተደረገበት የፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች ረቂቅ አዋጅ ከነማሻሻያ አዋጁ ትላንትና ፀድቋል። የምክር ቤቱ አባላት ረቂቅ አዋጁንና ማሻሻያ ሪፖርቱን አስመልከተው የተለያዩ
+1
#Ethiopia ከፍተኛ ክርክር የተደረገበት የፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች ረቂቅ አዋጅ ከነማሻሻያ አዋጁ ትላንትና ፀድቋል። የምክር ቤቱ አባላት ረቂቅ አዋጁንና ማሻሻያ ሪፖርቱን አስመልከተው የተለያዩ የድጋፍና የተቃውሞ ሐሳብና አስተያየቶችን ሰጥተዋል፡፡  የምክር ቤት አባልት ምን አሉ ? - ማሻሻያው ከአሁን ቀደም ከሥራ ባህሪያቸው አንፃር ለየት ባለ የአደረጃጀትና የአሠራር መዋቅር ተደራጅተው የነበሩ የፍርድ ቤቶችን መሰል አዋጆችን መሻሩን የወቀሱ ነበሩ፡፡ - ማሻሻያ አዋጁ ልክ ለገቢዎችና ለጉምሩክ ኮሚሽን ሠራተኞች እንደሰጠው ሁሉ፣ ለፌዴራል ፍርድ ቤቶች የአስተዳደር ሠራተኞች ተገቢውን ትኩረት ሊሰጥ ይገባ እንደነበርም ተገልጿል። - ሥራ ፈላጊ ኢትዮጵያውያን በየትኞቹ የአገሪቱ አካባቢዎች በሚወጡ የሥራ ማስታወቂያዎች በእኩልነትና በፍትሐዊነት ሊወዳደሩ የሚችሉበት አስገዳጅ ሁኔታ በግልጽ በረቂቅ አዋጁ ማሻሻያ አለመቅረቡ ተነስቷል። - የውስጥ ዝውውርን በተመለከተ አንድ የተቋም ኃላፊ ለውጤታማነት በሚል ሠራተኞችን ወደ የሚፈልግበት ቦታ አዛውሮ ማሠራት፣ ይህንን የማይቀበሉ ሠራተኞች ደግሞ መልቀቅ ይችላሉ መባሉም ጥያቄዎችን አስነስቷል፡፡ የአሠራር ክፍተቶችን የሚፈጥር እንደሆነም ተመላክቷል። የአብን የምክር ቤት አባል ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ፦ " እንዲህ ዓይነት አዋጆች ሲዘጋጁ ሰፊ ዝግጅትና ውይይት ይፈልጋሉ። እንዲሁም የሠራተኞችን ሥጋት ማካተት ይገባል። የረቂቅ አዋጁ መንደርደሪያ በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ኢትዮጵያን የሚመስል የሠራተኞች ስብጥር እንዲኖር ነው በሚል መገለጹ ችግር አለበት። ' ሲቪል ሰርቪሱ በአንድ ብሔር የበላይነት ተይዟል ' በሚል የቀረበ ነው። ያን ለማለት ደግሞ በሚያስችል መንገድ ተዘጋጅቶ ቀርቧል። ሲቪል ሰርቪሱ ብቃትንና አቅምን መሠረት አድርጎ ሊገነባ ይገባል። ኮታን ወደ ማከፋፈል አይወስደንም ወይ ? ሥራን በኮታ ማደላደሉ ማቆሚያው የት ነው ? አንድ ሠራተኛ አፈጻጸሙ ምንም ይሁን ምን ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን እስከፈለገ ድረስ አንስቶ ሌላ ተቋም ላይ በተመሳሳይ ደረጃና ደመወዝ መመደብ ይችላል። ያን የማይፈልግ ከሆነ ሠራተኛው መልቀቅ ይችላል መባሉ የሠራተኞችን መብት የሚጋፋና ዕጣ ፋንታቸውን በአለቆቻቸው እንዲወሰን የሚያደርግ ነው። እንዲሁም ከሥራ እንዲለቁ የሚገፋፋ ነው። የሠራተኞች የትርፍ ሰዓት ጉዳይ ከ39 ወደ 48 ሰዓታት እንዲያድግ መደረጉም አግባብነት የሌለው ነው " ብለዋል። የኢዜማ አባል አወቀ አምዛዬ (ዶ/ር) ምን አሉ ? " በረቂቅ አዋጁ ' ዘመናዊና ኢትዮጵያን የሚመስል ' መባሉ በዘወርዋራው የኮታ ሥርዓትን የሚመለከት ነው። ' ዘመናዊ አገርና ዘመናዊ ቢሮክራሲ እንፈጥራለን ' እያልን የመንግሥት ሠራተኞችን ከችሎታና አቅም ይልቅ በብሔር ኮታ እንቅጠር ማለት እርስ በርሱ የሚቃረን ሐሳብ ነው። ማይክሮሶፍትን መሰል ዓለም አቀፍ ተቋማት በአሜሪካውያን ሳይሆን በህንዳውያንና በቻይናውያን የሚመሩና የሚተዳደሩ ናቸው። የመንግሥት ተቋማት የሃይማኖት የስብከት ቦታዎች እየሆኑ ነው። ይህ በጥብቅ ሕግ ጭምር ሊከለከል ይገባል። አንድን ሠራተኛ መሥሪያ ቤቱ ወይም የበላይ ኃላፊው በፈለገው ቦታ መድቦ ማሠራት ይችላል የሚለው ሰው በሙያ (ፕሮፌሽን) እንዳያድግና የካበተ ልምድ እንዳይኖረው እንደሚያደርግ፣ ይህ ደግሞ በተቃራኒው ቢሮክራሲውን የበለጠ የሚጎዳ ነው። የበላይ አመራሩ የመጨረሻ ወሳኝ መሆኑ ከሕግና ከሥርዓት የሚፃረርና ሰብዓዊ መብትንም የሚጋፋ ነው። ይህ ከሆነ ባርነትን እንደገና በሕግ እያፀደቅን ነው ማለት ነው ? ውሳኔውን ፍርድ ቤት መስጠት አለበት " ብለዋል። የምክር ቤት አባል አቶ ለማ ተሰማ ምን አሉ ? " ረቂቅ አዋጁ ሠራተኞች በትምህርት መስክና ደረጃቸው እንዲሁም በልምዳቸው እንጂ፣ ከዚያ ውጪ የሚመደቡበትን አሠራር አይፈጥርም። የሚነሱ ሥጋቶች ቀጥለው ሊወጡ በሚችሉ ደንቦች ሊመለሱ ይችላሉ። በረቂቅ አዋጁ የተካተቱ አንዳንድ ጽንሰ ሐሳቦች በጥርጣሬ ሊታዩ አይገባም። ሲቪል ሰርቪሱ መለወጥ አለበት። ትናንት የነበረው አግላይ ነበር። ዕድልንም አይሰጥም ነበር። ረቂቅ አዋጁ ሁሉንም ጠርጎ የሚያስወጣ ሳይሆን፣ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በብቃቱ ተወዳድሮ ሠራተኛ መሆን የሚችልበትን ዕድል የሚፈጥር ነው። " ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የሰው ሀብት ልማት ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ምን አሉ ? 🔴 ብዙዎቹ ጥያቄዎች በውይይት ወቅት ተነስተው ምላሽ ተሰጥቶባቸው ነበር። 🔴 ፍርድ ቤቶች በልዩ ሁኔታ መታየት ነበረባቸው መባሉ በረቂቅ አዋጁ በሚቋቋመው በጠቅላይ ሚኒስትሩ በሚመራው የሜሪትና የደመወዝ ቦርድ በኩል ራሱን ችሎ ምላሽ ሊያገኝ ይችላል። 🔴 በረቂቅ አዋጁ ውስጥ ኮታ የሚል ነገር የለም። ኮታ ተቀባይነት እንደሌለው በረቂቅ አዋጁ ውስጥ ተቀምጧል። 🔴 ረቂቅ አዋጁ የሥራ አመራር ኢንስቲቲዩትን እንደ አዲስ የብቃትና ሥራ አመራር ኢንስቲቲዩት በሚል ስያሜ አቋቁሞ ሠራተኞችን በብቃታቸውን ለመመዘን ያስችላል። 🔴 ሠራተኞችን የማዘዋወሩ ኃላፊነት በማኔጅመንት እንጂ በበላይ ኃላፊዎች ብቻ አይወሰንም። የሠራተኛው ምክንያት የሚደመጥበትና መብቱ የሚጠበቅበት አሠራር በረቂቅ አዋጁ ተካቷል። ከፍተኛ ክርክር የተደረገበት ይህ ረቂቅ አዋጅ የፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1353/2017 ሆኖ በ3 ተቃውሞ በአራት ድምፀ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምፅ ፀድቋል፡፡#ሪፖርተር @tikvahethiopia

በት/ቤታችን በ06/03/2017ዓ.ም.ዓለም አቀፍ የሕፃናት ቀን የወረዳ-2 የሕፃናትና ወጣቶች ቢሮ ተወካዮች በተገኙበት የተከበረውን በዓል የሚያሳይ ፎቶግራፍ

በት/ቤታችን በ06/03/2017ዓ.ም.ዓለም አቀፍ የሕፃናት ቀን የወረዳ-2 የሕፃናትና ወጣቶች ቢሮ ተወካዮች በተገኙበት የተከበረውን በዓል የሚያሳይ ፎቶግራፍ

ሕዳር 6/2017 ዓ.ም የአለም ሕፃናት ቀን በእንጦጦ ወንጌላዊት ትምሕርት ቤት ከወረዳው 02 ሤቶችና ሕፃናትና Hope for children ከተባለ ግብረሠናይ ድርጅት ጋር በድምቀት አክብረናል፡፡ በእ
+7
ሕዳር 6/2017 ዓ.ም የአለም ሕፃናት ቀን በእንጦጦ ወንጌላዊት ትምሕርት ቤት ከወረዳው 02 ሤቶችና ሕፃናትና Hope for children ከተባለ ግብረሠናይ ድርጅት ጋር በድምቀት አክብረናል፡፡ በእለቱም ተማሪዎች ድራማ፡ መጣጥፎችንና ግጥሞችን ያቀረቡ ሢሆን የወረዳ 02 ሤቶችና ሕፃና ፅ/ቤት ሐላፊም ልጆች የሚሉት አላቸው እናድምጣቸው በሚል መሪ ቃል መልእክት አሥተላልፈዋል፡፡ ት/ቤቱ

በት/ቤታችን በ06/03/2017ዓ.ም.ዓለም አቀፍ የሕፃናት ቀን የወረዳ-2 የሕፃናትና ወጣቶች ቢሮ ተወካዮች በተገኙበት የተከበሰውን በዓል የሚያሳይ የፎቶግራፍ መገለጫ

በት/ቤታችን በ6/3/2017ዓ.ም. ዓለም አቀፍ የሕፃናቶች ቀን በተማሪዎች ከፍተኛ ዝግጅት መከበሩን የሚያሳይ የፎቶግራፍ መግለጭ