እውነት ይነገረን
አቅምን አትገድብ
إظهار المزيدلم يتم تحديد البلدلم يتم تحديد اللغةالفئة غير محددة
144
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
معدل نمو المشترك
جاري تحميل البيانات...
ማኪ የእርሱ:
እግዚአብሔር እጅግ መልካም የሆነዉ ነገር ከመስጠቱ በፊት ያበጃጀዋል።
ዘፍ 1፥2
👉በዚህ ስለ ምድር ስለ ሰው አፈጣጠር የመጽሐፍ ቅዱስ መገለጥ ባሰፈረበት ሁለተኛ ዐ/ነገር ላይ ምድር አንዳች አልነበረባትም/ቅርጽ የሌላት/ እንደነበረች ይናገራል። ይህም ማለት ምድር ነገቢ ከሆነ ስርሃት ውጭ ነበረች ማለት ነው።
👉 አንዳች አልነበረባትም/ቅርጽ የሌላት/ የሚለው ቃል በዕብራይስጥ ቃል #ቶው ሲባል ቀጥተኛ ትርጉም #ግራ መጋባት የነገሮች ስርዓት አለመያዝ የሚናገር ነው። ቃሉ የትኛውም ነገር በትክክል ስርዓት ውስጥ እንዳልነበረ የሚናገር ነው።
👉#ባዶ የሚለው ቃል ደግሞ በዕብራይስጥ ቃል #ቦው ሲሆን ቀጥተኛው ትርጉም #የተራቆተ ወይም #ባዶ ስፍራ ማለት ነው። ትርምስና ፍርስራሽ ያሳያል።...........
ይቀጥላል
👇👇👇👇👇👇👇
join ያርጉ
ወንድማቹ ማኪ/በቃሉ
Join us 👇👇👇
👉 @sileewnetyinegeren👈👈
👉 @sileewnetyinegeren👈👈
share to your friends
👨👩👧👨👩👦👦
. በዘመኔ አያለው
ዘማሪት አስቴር አበበ
ለወዳጆ share ያድርጉ
Share share share share
መዝሙርRINGTONE
Share share share share
✅ @mezemurringtone ✅
✅ @mezemurringtone ✅
በዘመኔ_አያለሁ ll አስቴር አበበ.mp39.45 MB
👑👑በጸጋው፤ በነፃ ጸድቃችኋል👑👑
ፓስተር ክሪስ
በኢየሱስ ክርስቶስ በሆነው ቤዛነት እንዲያው በጸጋው ጸድቀዋል፤ (ሮሜ 3:24)
በዮሐንስ 15:25 ላይ ኢየሱስ “ያለ ምክንያት ጠሉኝ ተብሎ በሕጋቸው የተጻፈው ቃል እንዲፈጸም ነው።” ብሏል፡፡ “ያለ ምክንያት” የሚለው አገላለጽ “ድሪያን” ከሚለው የግሪክ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም በነፃ ፣ ሳያስፈለግ፣ ያለምንም ነገር ፣ ወይም በከንቱ እንደማለት ነው። በሌላ አገላለጽ ፣ ኢየሱስ ለጥላቻቸው ምክንያት የሚሆን ምንም ስህተት አላደረገም፡፡ ምንም እንኳን ለእነሱ የገለጸው ፍቅር ተወዳዳሪ የሌለው ቢሆንም እንኳን፣ እነሱ ግን ጠሉት።
ይህም ሆኖ ግን፣ በመክፈቻ ጥቅሳችን ላይ እንዳነበብነው፣ እግዚአብሔር በማያልቅ ፍቅሩ፣ ሰውን በጸጋው በነፃ በማጽደቅ ከራሱ ባህሪ ጋር በሚስማማ መልኩ ምላሹን ሰጠ። “በነፃ” የሚለው ቃል “ድሪያን” ከሚለው የግሪክኛ ቃል ጋር ተመሳሳይ ነው። ኢየሱስ የዓለም ጥላቻ ለማትረፍ ምንም ነገር እንዳላደረገ ሁሉ፤ በተመሳሳይ መንገድ በእግዚአብሔር ዘንድ ለመጽደቅ ምንም ነገር ማድረግ እንደሌለባችሁ እያሳወቃችሁ ነው።
መጽደቅ ማለት ጥፋተኛ እንዳልሆነ መታወቅ፤ በነፃ መለቀቅ፤ ፣ ጻድቅ ተብሎ መጠራት ማለት ነው፡፡ ሃሌሉያ! ይህ ሁሉ ሆነው ደግሞ እናንተ ለዚህ ብቁ ለመሆን ምንም ማድረግ ሳያስፈልጋችሁ፤ ያለ ምንም ምክንያት ነው፤ እየሱስ ክርስቶስን በማመናችሁ ብቻ ይህ ሆኖላችኋል፤ “እንግዲህ በእምነት ከጸደቅን…” (ሮሜ 5:1)፡፡
እግዚአብሔርን በማመን ብቻ እንጂ፣ በስራችሁም ሆነ በምታከናውኑት በጎ ተግባር አይደለም። መጽሐፍ ቅዱስ በኤፌሶን 2:8-9 እንዲህ ይላል፡- “ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም። ” የሚያስፈልገው ነገር ለእግዚአብሔር ጽድቅ መገዛት ብቻ መሆኑን ማወቅ እንዴት አስደናቂ ነው! በዚህ መረዳት ተመላለሱና በሕይወት ንገሡ፤ “በአንዱም በደል ሞት በአንዱ በኩል ከነገሠ፥ ይልቁን የጸጋን ብዛትና የጽድቅን ስጦታ ብዛት የሚቀበሉ በአንዱ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በሕይወት ይነግሣሉ።” (ሮሜ 5:17)፡፡ እግዚአብሔር ይባረክ!
የእምነት አዋጅ
በእርሱ ፀጋ በነፃ ጽድቅን አግኝቻለሁ! በፊቱ የመመላለስ ፍቃድ ብቻ ሳይሆን አዲስ ፍጥረት ሆኜአለሁ። የሽንፈት ስሜት፣ የድህነት፣ የበሽታ፤ የኃጢአት እና ከሰይጣን ጋር የተዛመደ የማንኛውም ነገር አስተሳሰብ የለኝም። ክርስቶስ ጽድቄ ፣ ንጽህናዬ እና ቤዛዬ ነው። ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን!
ለተጨማሪ ጥናት:
ሮሜ 3:24-28;
ሮሜ 11:6
____
@EmmanulG
@EmmanulG
📚በማይመጥንህ ሰፈር አትገኝ፡፡📕
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
አንድ አባት ከመሞቱ በፊት ለልጁ እንዲህ አለው፡"የሄን ሰአት አያትህ ነው የሰጠኝ በትንሹ 200 አመት ይሆነዋል አሁን ላንተ ከመስጠቴ በፊት "እዚ ሰፈር ያለው የሰአት መሸጫ ሱቅ ሂድና ስንት እንደሚያወጣ ጠይቀህ ና አለዉ"
ልጁም ደርሶ መጣና ለአባቱ፡"አባዬ ሰአት ሻጩ ሰዉዬ አሮጌ ሰአት ነው አልገዛም አለኝ" አለው
አባቱም አሁን ደግሞ ወደ ካፌ ብቻ ሰዎች ሰብሰብ ያሉበት ቦታ ሄደህ የገዙህ እንደሆን ጠይቅ አለው! ልጁም ደርሶ መጣና አባዬ አንድ ሰውዬ 100 ብር ልግዛህ አለኝ
አሁን ደግሞ ሙዚየም ሄደህ ጠይቅ አለው ደርሶም መጣና 100,000 ብር እንግዛህ አሉኝ አለው፡፡
አባትየውም እንዲህ አለው "ያንተን ዋጋ የሚወስነው ትክክለኛ ቦታ ላይ ስትገኝ ብቻ እንደሆነ እንድታውቅ ነው እንዲህ ያረኩት፡፡
እራስህን ባልተገባ ቦታ ለማስገባት አትግፋው ትርፉ መናደድ እና መማረር ብቻ ነው።ዋጋህን የሚያዉቁት የሚያውቁህ ናቸው እና አንተን በማይመጥንህ ሰፈር አትገኝ፡፡
ዋጋህ ውድ ነው የተገዛኸው በክርስቶስ ደም ነው ስለዚህ ዋጋህን በማይመጥን ሰፈር አትገኝ፡
💟💟💟💟💟💟💟💟💟💟💟💟
@EmmanulG
@EmmanulG
ምን ታያለህ ?
👉ሊስትሮ ሁልጊዜ የእግርህን ጫማ ይመለከታል
👉 ቁራሌው ሁልጊዜ መንገድ ላይ ብረት ይፈልጋል
👉ዶክተሩ ህይወቱ በበሽተኞች የተከበበ ነው
👉 ኮንስትራክተር መንገድ ላይ ፎቆችን ይመለከታል።
ታድያ አንተ ምን እያየህ ነው? ህይወትህን ልትመራ የምትችለው በምታየው ልክ ነው🤷♂። ላንተ ተብሎ ከሌላው ተለይቶ የሚፈጠር ነገር የለም።
ካልሠራህ ካለፋህ ምንም መፍጠር አትችልም። ለህይወትህ መበላሸት ማንንም ተጠያቂ አታድርግ😡።
👉 ጨለማ ምታይ ከሆነ ሁሌም ህይወትህ ጨለማ ነው።
👉 ድህነትን ምትመለከት ከሆነም በድህነት ትሞታለህ።
👉ደደብ መሆንህን አምነህ ከተቀበልክም በድድብናህ ትቀጥላለህ።
ጨለማን ለማባረር ሻማ መለኮስ በቂ ነው ። ህይወትህን ለመለወጥ አመለካከትህን መለወጥ መቻል አለብህ😎።
🌼 አበባ ማሽተት እየቻለክ እሾክ ስር መመላለስ ምን ፋይዳ ይፈጥራል።
ላለህበት ነገር ለውድቀትህ ቤተሠብህን ፣ ጓደኞችህን ፣ ፈጣሪን ምትወቅስ ከሆነ ችግር የለውም እየወቀስካቸው ትሞታለህ 👌።
👉ህይወት ምትቀየረው ሌላውን በመውቀስ እና ተጠያቂ በማድረግ አይደለም።
👉ህይወት ምትቀየረው በማልቀስም አይደለም።
👉ህይወትህን መቀየር የምትፈልግ ከሆነ የእይታህን አቅጣጫ አስተካክል ።
👉 ምን እንደምታይ እወቅ ። ተስፋ ይኑርህ። ጠንክረህ ስራ ትለወጣለህ ።🙏🙏
እወዳችሁዋለው ደህና እደሩልኝ😘😘😘😘።
Its Me Jonah 🙏🙏🙏
ተመርጫለው እኔ
ተወድጃለው እኔ
ጸድቄለሁ በእርሱ
እንድኖርለት ለእርሱ
ጸጋው በእምነት አድኖኝ
ኢየሱስ ጽድቁን አልብሶኝ
ስለእኔ በአብ ፊት ታይቶ
.....
____
ዘማሪት ሰላም ደስታ
ከአልደራደርም አልበም የመዝሙር ግብዣችን
ሙሉ አልበሙን በመግዛት ይባረኩበት
ለሌሎች #ሼር
▷ @markenzema_bot ◁
▷ @markenzema_bot ◁
ተመርጫለው_TEMERCHALEW_ሰላም_ደስታ_SELAM_DESTA_NEW_GOSPEL_SONG_low.mp32.32 MB
#ዘረኝነት_ተወኝ
ዘረኝነት ተወኝ ......ሠላሜን አትንሳኝ
አማራ ኦሮሞ........ትግሬ ነህ አትበለኝ
ባምሳሉ የሰራኝ.......የክርስቶስ ልጅ ነኝ
ዘረኝነት ተወኝ
ቀዳሚዋን ሴት.......ሄዋንን ጠይቃት
አፋር ነሽ ሡማሌ......ሀረሪ ነሽ በላት
አዳምን ጠይቀው.......ዘርህ የት ነው በለው
የስላሴ ባሪያ........የእግዚአብሄር ጥበብ ነው
ዘረኝነት ተወኝ
አማራ ኦሮሞ.........ትግሬ ነው አትበለው
እኔም አልልህም........አዳም ጓንደሬ ነው
ፈጣሪ ሰራ እና........በገነት አኖረው
ብሄር ዘሩን ሳይለይ ........አዳም ብሎ ጠራው
ወደድንም ጠላንም ......... ዘራችን አንድ ነው
ብሄር ዘር ቀለም ግን........ያንተው መላ ምት ነው
ታዲያ አንዴ ኖረን ........ማለፋችን ላይቀር
ብንኖር ምን አለ........በሰላም በፍቅር
ዘረኝነት ተወኝ
ሞትም እጁን ላይሰጥ .......መቃብሩም ላይቀር
ዘር እየመረጡ ........ማጥፋት የሰው ፍጡር
ለትቢያው ስጋችን.......ለሚበላው አፈር
ተዋደን ተፋቅረን.........በሰላም ብንኖር
አምላክ ይጠብቃት......ኢትዬጵያችን ትክበር
#Mickey
እንደተጸነሰ አይወለድም!
በሕይወታችን አብዛኛዎቹ ነገሮች ልክ እንደጽንስ ናቸው፡፡ ጽንስ ገና እንደተፈጠረ ወይም የመወለጃው ወቅት ሳይደርስ አይወለድም፣ ቢወለድም ወይ ጎዶሎ ሆኖ ይኖራል ወይም ደግሞ ካለጊዜው ስለተወለደ ካለጊዜው ይሞታል፡፡ ጽንስ በጽንስነት ዘመኑ በቂ ጊዜን ካሳለፈ በኋላ እውነተኛውን አለም ለመቋቋም የሚችልበት ደረጃ ሲደርስ ነው መወለድ ያለበት፡፡ ጊዜው ሲደርስ ደግሞ እኛ ሳንገፋው ራሱ ገፍቶ መምጣቱ አይቀርም፡፡
ብዙ ነገራችን የሚበላሽብን ካለጊዜው ለመውለድ ስለምንሞክር ነው፡፡ ጓደኛን እንይዛለን፣ ጓደኝነቱ ፍቅርን ጸንሶ፣ ጽንሱ ደግሞ ጊዜውን ወስዶ በተፈሯዊው መንገድ እንዲወለድ ጊዜ አንሰጠውም፡፡ ስለዚህም እናጣድፈዋለን፣ ቶሎ እንዲፈጠር እንፈልጋለን፣ እንወልደዋለን፡፡ የተፈጥሮን ሂደት ተከትሎ አድጎ እንዲወለድ ጊዜን ከመስጠት ይልቅ አዋክበን ወደመኖር ልናመጣው እናግለበልበዋለን፡፡ ከዚያም ካለጊዜው የተወለደን አንካሳ፣ ሰባራና ጤናቢስ ነገር ይዘን መላው ይጠፋብናል፡፡
ያለን ማሕበራዊ ግንኙነት፣ ስራ፣ ንግድም ሆነ ሌሎች ነገሮቻችን የዚህ መርህ ተገዢ ናቸው፡፡ አንድን ነገር ከጀመርን በኋላ ነገሩ ተፈጥሯዊውን ሂደት እስኪጨርስ መታገስ አስፈላጊ ነው፡፡ ይህንን የተፈጥሮ ሂደት መከተል እውነተኛውን ከውሸተኛው ሕይወት ያለውን ከሌለው የምንለይበት ብቸኛ መንገድ ነው፡፡
በጀመርከው ቁጥር መልሶ የሚቋረጥ፣ ሕይወት በሰጠኸው ቁጥር ተመልሶ የሚሞት፣ በጠገንከው ቁጥር ተመልሶ የሚሰበርን ጉዳይ ጽንሱ ሳያድግ የተወለደ ነገር እንዳይሆን ሊታሰብበትና እስኪያድግ ድረስ ጊዜ ሊሰጠው ይገባል!!!
ምንጭ:- ከዶ/ር ኢዮብ ማሞ ቴሌግራም ፔጅ የተወሰደ
Join us 👇👇👇
👉 @sileewnetyinegeren👈👈
👉 @sileewnetyinegeren👈👈
share to your friends
👨👩👧👨👩👦👦
Gospel singer Robi Temesgen - YouTube
https://m.youtube.com/channel/UCo8vFASpby-byaJjG0QhcPQ
from Vidmate
اختر خطة مختلفة
تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.