cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

Fast newes

Fast news about ethiopia

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدلم يتم تحديد اللغةالفئة غير محددة
مشاركات الإعلانات
491
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

በኢትዮጵያ ለምትገኙ የመንግስትም የግልም ሚዲያዎች እንዳትቀሩ ስንል በቀድሞ የሰራዊታችን አባሎች ስም እንጠይቃለን! #Ethiopia : እንደ ቀልድ እኔና ጏደኞቼ በኢንስታግራም አማካኝነት ጧሪ ቀባሪ ለበአል አስታዋሽ የሌላቸውን ከ150 በላይ የቀድሞ ሰራዊት አባላትን ለአበአል እንኳን አደረሳችሁ ብለን ለማስታወስ እስካሁን በሁለት ቀን ከሀገር ውጪ ከ5 ሺህ ዶላር በላይ ስናሰባስብ በሀገር ውስጥም አርቲስቶች ባለሀብቶች የቻሉትን ሰተውናል እየሰጡም ከሀገር ቤት ነው ማን ም ሰጠ ስማቸውን በዝርዝር እንገልጻለን በዚህ በጎ ተግባር መካፈል መርዳት የምትፈልጉ አርቲስቶች ባለሀብቶች በውስጥ መስመር አናግሩኝ ዝግጅቱን የፊታችን እሁድ ነው የምናደርገው! ገንዘብ የምሰባሰብ ስራው ዛሬም ይቀጥላል
إظهار الكل...
ሰበር ዜና‼️ የ3ኛ መብረቅ ኮማንዶ ሻለቃ የግዳጅ ውሎ ‼️ #Ethiopia : የጁንታው ብርጌድ አዛዥ ኮ/ል በህረ ተበጄ እና የሻለቃው ዋና አዛዥ ሻምበል ተክለወይኒ ታረቀኝን ጨምሮ 100 ታጣቂ ማርኳል ቀሪዎቹ በተደረገው ውጊያ ሙሉ በሙሉ ተደምስሰዋል:: 103 ዘመናዊና አዲስ ሞቶሬላ ወታደራዊ መገናኛ ከእና ሙሉ አክሰሰሪና ቅያሪ ባትሪ 01 አይኮም ፤ ቶሪያ ስልክ 01 ፣ አለም አቀፍ ጥሪ ተቀባይ ሳምሰንግ ስልክ 02 ፣ ብሬን 01 ፣ ክላሽ 05 ፣ ማካሮቭ ሽጉጥ 01 ፣ በርካታ ጥይቶችና የህክምና ቁሳቁሶች በቁጥጥር ስር አውሏል::
إظهار الكل...
#Ethiopia : Breaking news loading….
إظهار الكل...
መከላከያ ሰራዊቱ ደብረ ዘቢጥን አልፎ ኮኪትን ተቆጣጠረ! የአገር መከላከያ ሰራዊት ደብረ ዘቢጥን አልፎ ኮኪትን ሙሉ ለሙሉ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ፡፡ በሰሜን ምዕራብ እዝ የኮር አንድ አዛዥ ብርጋዴል ጄኔራል ብርሀኑ ጥላሁን፤ የአሸባሪው ሕወሓት ቡድን ታጣቂዎች በአውደ ውግያ የሞቱባቸውን ህጻናት አስክሬን እንኳን ሳያነሱ፣ ትጥቅና መሳሪያቸውን ጥለው እየፈረጠጡም "እያሸነፍን ነው" ብለው የትግራይን ሕዝብ እያታለሉ ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡ በደብረ ዘቢጥ ግንባር ያለው የኢትዮጵያ ሠራዊት መልከዓምድሩና የአየር ጸባይ ሳይበግረው ድል እየተቀዳጀ ወደ ፊት እየገሰገሰ ይገኛልም ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ደብረ ዘቢጥን አልፎ ኮኪትን ሙሉ ለሙሉ በቁጥጥር ስር አውሏል ነው ያሉት፡፡ የሽብር ቡድኑ መሪዎች “እያሸነፍን ነው ካሉ ደብረ ዘቢጥ ሆነው መግለጫ መስጠት በቻሉ ነበር” በማለትም ሕዝቡ በአሸባሪው የሀሰት ወሬ መደናገር እንደሌለበት ስለመጠየቃቸው ኢፕድ ዘግቧል፡፡
إظهار الكل...
#Ethiopia : የወያኔን የውሸት ዜና እየሰማችሁ አታደንቁሩን እባካችሁ አንዳንዱ ጦርነት ላይ ያለንም አይመስለውም:: ጁመዓ እና ሀይቅ መስተጋብራቸው የተለየ ነው !!! የገበያ ቀን በመሆኑ ገበያተኛውም ፍፁም ሠላማዊ በሆነ መንገድ የተለመደ ገበያውን እየተገበያየ ነው ። ሀይቅ ምንም የተፈጠረ ነገር የለም! ወደ ተሁለድሬ እና ወረባቦ እየተምዘገዘገ የሚሄደውን ጀት ቤተሰብ ደውላችሁ ጠይቁ:: በተረፈ ህወሓት ተሁለድሬ እና ወረባቦ እየዋጀጀ ነው!
إظهار الكل...
#Ethiopia : እነሱ ይዋሹ ያውሩ ውሸት ተወልደው ያደጉበት ነው እኛ ጀግኖች ሰራዊቶቻችን ጎን ነን ድል ለሀገሬ ኢትዮጵያ! ኢትዮጵያ ታሸንፋለች‼️
إظهار الكل...
ሰበር ዜና‼️ #Ethiopia : ጀግናው የአየር ሀይላችን ዘረፊውን እና አሸባሪውን ቡድን ትላንት በከተመበት ተሁለደሬ ወረዳ ሠግለን ቀበሌ ሸበሬ አካባቢ በሰማይም በምድርም የሚገባውን ዋጋ እየሠጠው ነው ። ኢትዬጵያ ታሸንፍለች !!!
إظهار الكل...
የኢትዮጵያ መድን ድርጅት በተጠናቀቀው 2013 በጀት ዓመት ከታክስ በፊት 1.12 ቢሊዮን ብር ትርፍ አገኘ ! የኢትዮጲያ መድን ድርጅት በ2013 በጀት ዓመት 13.8 ቢሊዮን የዓረቦን ገቢ ሲያገኝ ካለፈው በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ24.7 በመቶ ብልጫ ማሳየቱን በዓመታዊ ጉባኤው ላይ ድርጅቱ አስታውቋል፡፡ በዓመቱ የተከፈለው የካሳ ክፍያ 1.3 ቢሊየን ሲሆን ይህም የእቅዱን 81 በመቶ መሆኑን እና ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀረ የ18 በመቶ ቅናሽ መኖሩን የኢትዮጵያ መድን ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ነፃነት ለሜሳ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።ይህም የሆነው የኮቪድ 19 ከአንድ ዓመት በላይ በፈጠረው ጫና ነው ብለዋል፡፡ ድርጅቱ በበጀት ዓመቱ 1.12 ቢሊየን ብር ትርፍ ከታክስ በፊት ያስመዘገበ ሲሆን የእቅዱን የ5.5 በመቶ ብልጫ አለው። የተገኘው ትርፍ ካለፈው በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ13.3 በመቶ ብልጫ አስመዝግቧል። አቶ ነፃነት በበጀት ዓመቱ ኮቪድ፣በኢትዮጲያ ያለው የኢኮኖሚያ አለመረጋጋት በተለይ በትግራይ ክልል የተፈጠረው ቀውስ፣ የምንዛሬ እጥረት የነበሩ ዋና ዋና ችግሮች መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ አስተማማኝ የመድን ሽፋን እየሰጠ እንደሆነ ያስታወቀው ድርጅቱ በበጀት ዓመቱ የ162 በላይ ውሎችን ሽያጭ እና እድሳት መከናወኑን አስታውቃል፡፡ [Bisrat FM]
إظهار الكل...
አባገዳዎች፣የአገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች ማንኛውም የዉጭ ጣልቃ ገብነትና አገር ለማፍረስ የሚደረገዉን ጥምረት እናወግዛለን አሉ። አባገዳዎቹ፣የአገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች ይህን ያሉት በወቅታዊ ጉዳይ ላይ በኦሮሞ ባህል ማዕከል ዉይይት እያደረጉ ባሉበት ነዉ። ዉይይቱ በአባገዳዎች፣የአገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች ተነሳሽነት ስለአገራችን ያገባናል በማለት የተደረገ መሆኑም ተነግሯል። የዉይይቱ ተሳታፊዎች ማንኛውም የዉጭ ጣልቃ ገብነትና አገር ለማፍረስ የሚደረገዉ ጥምረት እናወግዛለን ብለዋል። ተሳታፊዎቹ በመካከላችን ያለዉን ልዩነቶችን በማጥበብ ስለአገራችን ሉዓላዊነት መታገል አለብን ብለዋል። ከአሸባሪዉ ህወሃት ጋር ጥምረት የፈጠረዉ ሸኔም ኦሮሞን ነፃ ለማዉጣት ሳይሆን ህዝቡን ወደ ወጣበት የባርነት አረንቋ ልመልስ መሆኑን ተናግረዋ። ተሳታፊዎቹ ባለን አቅም ሁሉ ከመከላከያ ጎን በመቆም የአገራችን ሉዓላዊነት እናስከብራለን ብለዋል። በዉይይቱ ላይ የተገኙት በኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ ቤት የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ታዬ ደንደኣ አባገዳዎች፣የአገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች ብዙ ተከታዮች ስላላቸው ስለአገራቸው መምከር እንዳለባቸው ጠይቀዋል።
إظهار الكل...