376
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-17 أيام
-330 أيام
أرشيف المشاركات
Repost from Ethiopian New Curriculum( Kg _12)
Grade 12 model exam all subject for natural and social with their answer key
ለ12ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች በሙሉ
በቅድሚያ የከበረ ሰላምታችንን እያቀረብን ከዚህ በታች የቀረቡትን ሐሳቦች በአትኩሮት በመመልከት ለተግባራዊነታቸው የተለመደውን ትብብራችሁን እንድታደርጉ በጥብቅ እናሳስባለን።
1.የ12ኛ ክፍል የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና የመመዝገቢያ ፎርም የሚሞላው ከየካቲት 4/206-የካቲት 15/2016ዓ.ም ይካሄዳል
2.ለ12ኛ ክፍል ፈተና መሟላት የሚገባቸው
የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዋናው ማስረጃ እና ትራንስክርፕት ያላሟላችሁ በአስቸኳይ ለር/መ/ሩ እንድታስረክቡ
3.የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በእያንዳንዱ ትምህርት 100(አንድ መቶ ብር) በተጨማሪም 150(አንድ መቶ ሃምሳ ብር) ለመመዝገቢያ በድምሩ ከአንድ ተማሪ የሚጠበቀው አጠቃላይ ክፍያ 750.00(ሰባት መቶ ሃምሳ )መሆኑን አውቃችሁ ለምዝገባ ስጥመጡ ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን።
ት/ቤቱ
ለስኩል ኦፍ ሪደምሽን ቤተሰቦች በሙሉ፣
የ2016 ዓ/ም ማጠቃለያ ፈተና ፕሮግራም እንደሚከተለው ይሆናል።
፩) ከ 27/05--30/05/2016 ዓ/ም ፈተና ይሰጣል።
፪) አርብ በ 01/06/2016 ዓ/ም
የፈተና ማረሚያ ቀን ሲሆን ለተማሪዎች ት/ት ዝግ ይሆናል።
፫) ሰኞ በ 04/06/2016ዓ/ም የፈተና ውጤት ለተማሪዎች ይመለሳል።
፬) ከማክሰኞ 05/06/2016 ዓ/ም ጀምሮ ትምህርት ለተማሪዎች እረፍት ይሆናል።
፭) ሰኞ በ11/06/2016 የሁለተኛው መንፈቅ አመት ይጀመራል።
ት/ ቤቱ
ውድየ12ኛ ክፍል ወላጆች:- የ12ኛ ክፍል የቲቶሪያል ትምህርት ዘወትር ሰኞ ፣ረቡዕና አርብ ከ9:30_10:50 መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን።
በቅድሚያ ለክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለከተራ በዐል አደረሳችሁ እያልኩ ነገ
አርብ ማለትም 10/5/2016ዓ.ም በጥምቀት በዓል ምክንያት ተማሪዎች የትራንስፖርት ችግር እንዳይገጥማቸው ሙሉ ቀን ትምህርት የማይኖር መሆኑን እንገልፃለን ።
ት /ቤቱ
ውድ የ12ኛ ክፍል ወላጆች በሙሉ፣ ልጆቻችን ባለፈው ሳምንት የክፍለ ከተማ ሞዴል ፈተና እንደተፈተኑ ይታወቃል። ይህን ምክንያት በማድረግ አንዳንድ ልጆች ትምህርት ቤት የለም ብለው የቀሩ አሉ። ስለዚህ ትምህርት እያስተማርን በመሆኑ ልጆችን እንድትልኩ እናሳስባለን። እያንዳንዱን መረጃ እንድትከታተሉ ለማሳሰብ እንወዳለን።
ት/ ቤቱ
