ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 544 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 333 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 158 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 544 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 27 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 10، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -16، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 25.06‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.33‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 895 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 539 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 7.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 28 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 544
المشتركون
-1624 ساعات
-97 أيام
+1030 أيام
أرشيف المشاركات
photo content

የዕይታ ፍተሻ እና የግድብ ደህንነት መከታተያ መሳሪያዎችን በመጠቀም በግድቦች ላይ ክትትል እየተደረገ ነው ……...//……... የኃይል ማመንጫ ግድቦችን በክረምት ወራት ሊፈጠር ከሚችል የጎርፍ አደጋ ለመጠበቅ የዕይታ ፍተሻ እና የግድብ ደህንነት መከታተያ መሳሪያዎችን በመጠቀም ክትትል እየተደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ገለጸ፡፡ በዘርፉ የግድብ ክትትልና ቁጥጥር ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤልያስ ደላሽ እንደገለጹት ክትትሉ የሚከናወነው በክረምት ወራትሊፈጠር ከሚችል የጎርፍ አደጋና የአፈር መንሸራተት ግድቦችን በመጠበቅ የግድቦችን ደህንነት ለማረጋገጥ ነው፡፡ በክረምት ወራት ሊኖር የሚችለው ዝናብ ለኃይል ማመንጫ ግድቦች አስፈላጊ ቢሆንም ከመጠን ሲያልፍ ግን የግድቦችን ደህንነት ስጋት ላይ ሊጥል ስለሚችል በተቋሙ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን የአሠራር መመሪያ መሠረት በከፍተኛ ጥንቃቄ ያልተቋረጠ ክትትል ይደረግበታል ብለዋል፡፡ የግድቦቹን የውሃ ማስተንፈሻ /Spillways/ እና መቆጣጠሪያ በሮች በመጠገንና ለሥራ ብቁ እንዲሆኑ በማድረግ የግድብና ተያያዥ ክፍሎች ላይ ዘወትር የክትትል ሥራ እንደሚከናወን ገልጸዋል፡፡ የግድብ ክትትልና ቁጥጥር ሥራው በየጣቢያዎቹ ኃላፊዎችና ኦፕሬተሮች፣ በየጣቢያው ባሉ የግድብ ክትትልና ቁጥጥር ባለሙያዎች እና ከዋና መስሪያ ቤት በሚላኩ ባለሙያዎች እንደሚከናወን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡ እንደ አቶ ኤሊያስ ገለፃ የሚከናወነው የክትትልና ቁጥጥር ሥራ ከግድቡ በታች የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ከጎርፍ ከመከላከል ባለፈ የግድቦችን ደህንነት በመጠበቅ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎቹ የሚጠበቅባቸውን ኃይል በአግባቡ እንዲያመርቱ ለማድረግ ያግዛል፡፡ የግድብ ክትትልና ቁጥጥር ሥራ ከግድቦቹ ዲዛይን ጀምሮ በግንባታ ሂደት፣ ግድቡ ለመጀመሪያ ጊዜ ውሃ መያዝ ሲጀምር እና አገልግሎት እየሰጠ ባለበት ሰዓት ጭምር የሚከናወን ነው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 18 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ባለፉት አስራ አንድ ወራት ከቀረቡ ቅሬታዎች ለ71  መፍትሔ መሰጠቱ ተገለፀ ........///....... ባለፉት አሰራ አንድ ወራት በተቋሙ ሠራተኞችና ደንበኞች ከቀረቡ 135 የተለያዩ የአስተዳደራዊ ቅሬታዎችና ጥያቄዎች መካከል ለ71ዱ መፍትሔ መሠጠቱን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት አስታወቀ። በጽ/ቤቱ የአስተዳደራዊ ጉዳዮችና ዶክመንቴሽን ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንዳስታወቁት ባለፉት ዘጠኝ ወራት 81 በመቶ የሚሆነው ከውጭ ደንበኞች 19 በመቶው ደግሞ ከውስጥ ሠራተኞች የቀረቡ  ናቸው። ከቀረቡ ቅሬታዎች 45ቱ ከተቋሙ  መመሪያና ደንብ እንዲሁም ከተሰጠው ስልጣን ውጭ በመሆናቸው ውድቅ መደረጋቸውን እና  71 ጉዳዮች መፍትሔ እንደተሰጣቸው እንዲሁም 19ኙ በሂደት ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል። የአስተዳደራዊ ቅሬታዎችና ጥያቄዎች በካሳ ክፍያ፣ በጨረታና ግዥ፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት፣ በደረጃ ዕድገትና ዝውውር፣ በጥቅማ ጥቅም እና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ ያተኩሩ መሆናቸውንም ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። እንደ አቶ ዋለ ገለፃ ከሠራተኞች የሚቀርቡ ቅሬታዎች አመራሮችና ሠራተኞች የህብረት ስምምነቱን ድንጋጌዎች በአግባቡ ባለመረዳትና በራሳቸው ፍላጎት በመተርጎም  የሚመነጩ ናቸው። ለቅሬታዎች በወቅቱ መፍትሔ ለመስጠት ቅሬታው ከተነሳበት የሥራ ክፍል ጋር በመነጋገር  ከመስራት ባለፈ ጊዜያዊ ኮሚቴ በማዋቀር የሚሰራበት አግባብ እንዳለም አቶ ዋለ አንስተዋል። ቢሮው ከሠራተኞችና ቅሬታ ከቀረበበት የሥራ ክፍል አመራር ጋር ተቀራርቦ በመሥራቱ በተቋሙ  ላይ የሚቀርቡ አስተዳደራዊ ቅሬታዎች እየቀነሱ መምጣታቸውን አንስተዋል። አግባብ ያልሆኑ ቅሬታዎችን በማቅረብ ጊዜን ከማባከን ለመዳን እና የሠራተኛውንና የተቋሙን ጥቅም ለማስጠበቅ ሁሉም ተቋሙ የሚተዳደርባቸውን ደንቦችና መመሪያዎች ጠንቅቆ በማወቅ በአግባቡ ተግባራዊ ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል። ከካሳ ክፍያና ከኃይል ተደራሽነት ጋር በተያያዘ ከውጭ ደንበኞች የሚቀርቡ ቅሬታዎችን ለመፍታት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እየተሠራ እንደሆነም አቶ ዋለ ተናግረዋል። የካሳ ክፍያ ቅሬታዎች አብዛኞቹ ከኦሮሚያ ክልል እንደሚቀርቡ ያነሱት ሥራ አስኪያጁ ለተቋሙ የሚቀርቡ ቅሬታዎችን ለመቀነስ የቅሬታዎች አግባብነት በክልሉ የልማት ተነሽዎች ኤጄንሲ በኩል ተጣርቶ ወደ ተቋሙ የሚመጣበት አሰራር መዘርጋቱንም አስታውቀዋል። ሁሉም ቅሬታዎች ቀጥታ ለተቋሙ ይቀርቡ በነበረበት ጊዜ አግባብነት ያላቸው ቅሬታዎችን በወቅቱ ለመፍታት በሚከናወነው ሥራ ላይ ጫና ፈጥሮ መቆየቱን ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል። ማከፉፈያ ጣቢያዎች በሚገነቡበት አካባቢ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችን የኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር  የ40/60 ቀመር አሰራር ተዘርግቶ እየተሰራ ቢሆንም ተቋሙ ማከፉፈያ ጣቢያዎች ከሚገኙበት በምን ያህል ሬዲየስ ውስጥ በገንዘብ ማገዝ እንዳለበት የተቀመጠ ግልጽ አሰራር ባለመኖሩ የቅሬታ ምንጭ እየሆነ መጥቷል። ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኩል የአሰራር ሥርዓት ማኑዋል እየተዘጋጀ መሆኑንም አቶ ዋለ ጠቁመዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ሰኔ 17 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ተቋማቱ ባለፈውን አንድ ዓመት የነበረውን የትብብር ስራ ገመገሙ .....//..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር በመተባበር ለአንድ ዓመት የሠራቸውን የሬዲዮና የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች አፈጻጸም የሁለቱ ተቋማት ዋና ሥራ አስፈፃሚዎች በተገኙበት ገምግመዋል። የፕሮግራሞቹን አፈጻጸም ያቀረቡት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እና የኢቢሲ የክፍያ ፕሮግራሞች አስተባባሪ አቶ ኤሊያስ አማረ ናቸው። ከየካቲት 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተቋሙ እያከናወናቸው ያሉትን ተግባራትና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ለማስተዋወቅ ከኢቢሲ ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችል ውል  ተፈርሞ ሥራ መጀመሩን አቶ ሞገስ ገልፀዋል። በዚህም መሰረት በየሳምንቱ በአማርኛና አፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች በብሔራዊ ሬዲዬና ቴሌቪዥን ጣቢያ የ30 ደቂቃ ፍጆታ ያላቸው ፕሮግራሞች እየተዘጋጁ ሲተላለፉ መቆየቱን ተናግረዋል። በተላለፉት ፕሮግራሞች ላይ ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ እስከ ድህረ ፕሮዳክሽን የነበሩ ጠንካራና ደካማ ጎኖች ያቀረቡት አቶ ሞገስ በቀጣይ ግን የተሰሩ ፕሮግራሞች ያመጡት ለውጥ በጋራ ሊጠና እንደሚገባ ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እንደ ሀገር ብሔራዊ ኩራት እንዲሰማን የሚያደርጉ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን የሚገነባና ለሀገር ኢኮኖሚ ዋልታ የሆነ ተቋም ነው። በመሆኑም ከኢቢሲ ጋር የተጀመረው ሥራ የተቋሙን ዋንኛ ተግባራት ለማስተዋወቅ፣ ከስርቆት፣ ከካሳ ክፍያና ወሰን ማስከበር ጋር እያጋጠሙት ባሉት ችግሮች ዙሪያ ግልጽነት በመፍጠር ህብረተሰቡን ለማሳተፍ ያለመ እንደነበር አንስተዋል። እንደ አቶ አሸብር ገለጻ ተቋሙን ከማስተዋወቅ አንጻር ባለፈው አንድ ዓመት በተላለፉ ፕሮግራሞች የነበሩ ድክመቶች ታርመው በቀጣይ መርህን ባከበረ መልኩ የተሻሉ ፕሮግራሞችን አብሮ ለመስራት ውይይቱ ማስፈለጉን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጌትነት ታደሰ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሀገራዊ ተልዕኮውን በብቃት እንዲወጣ ኢቢሲ አብሮ የመስራትና የማገዝ ኃላፊነት አለበት ብለዋል፡፡ በውል ከምንገባቸው ፕሮግራሞች ባለፈ ተቀሙን በዜናና በሌሎች አማራጮች ሽፋን ለመስጠት አቅደው እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይም በእስከአሁን ሂደት የነበሩ ጥንካሬዎችን በማጎልበትና ክፍተቶችን በማረም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በተሻለ መንገድ በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ሰኔ 14 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

በአሶሳና አካባቢው የተቋረጠውን ኃይል መልሶ የማገናኘት ሥራ ተሰርቷል .........///......... የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ በመውደቁ ምክንያት በአሶሳና በዙሪያው በሚገኙ ወረዳዎች ለቀናት ተቋርጦ የቆየው ኃይል መልሶ መገናኘቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ እስማኤል ሙዘይን እንደገለፁት ዛሬ ከቀኑ 8፡50 ጀምሮ አካባቢው ዳግም ኃይል እንዲያገኝ ተደርጓል፡፡ አካባቢው ኃይል እንዲያገኝ የተደረገው በባለሙያዎች የቀረበውን ቴክኒካዊ የአማራጭ መፍትሔ በመተግበር መሆኑን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

በአሶሳና አካባቢው የተቋረጠውን ኃይል መልሶ ለማገናኘት የሚያስችሉ አማራጮች እየታዩ ነው .........///......... ከአሶሳ መንዲ በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ በመውደቁ በአሶሳና  በዙሪያው በሚገኙ ወረዳዎች ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ።    በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ እስማኤል ሙዘይን እንደገለፁት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶው የወደቀው  በምዕራብ ወለጋ ዞን መነሲቡ ወረዳ ቤንጉዋ ቀበሌ ነው። በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶው ላይ ስርቆት ባይፈፀምም በመፈታታቱ የተነሳ አገልግሎት መስጠት አቅቶት መውደቁን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። በዚህ የተነሳ በአሶሳ ከተማና በዙሪያው ባሉ ወረዳዎችና የገጠር ቀበሌዎች ከሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ኃይል መቋረጡን ገልፀዋል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ የወደቀውን የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ለመጠገን የቴክኒክ ቡድን በሥፍራው ቢደርስም ምሶሶውን በነበረበት ሁኔታ መልሶ ለማቆም ረዘም ያሉ ሳምንታት እንደሚወስድ ሪፓርት አቅርቧል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ለበርካታ ቀናት በጭለማ ውስጥ እንዳይቆይ የሚያደርግ ቴክኒካዊ አማራጭ መፍትሔ ቀርቦ ከሪጅኑ እና ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የድጋፍ ጥያቄ መቅረቡን ጠቁመዋል። በቀረበው ጊዜያዊ መፍትሔ ክልሉ በጥቂት ቀናት ውስጥ በተፋጠነ ሁኔታ ኤሌክትሪክ እንደሚያገኝ ዳይሬክተሩ እምነታቸውን ገልፀዋል። ህብረተሰቡ የደረሰው ጉዳት እስኪጠገን ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቅ አቶ እስማኤል ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ሰኔ 12 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

በሁመራ እና አካባቢው የተቋረጠውን ኃይል መልሶ ለማገናኘት የሚያስችል ሥራ ተጀምሯል .........///......... ከሽሬ- ሁመራ በተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ በደረሰ ተፈጥሯዊ አደጋ ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ውበት አቤ እንዳስታወቁት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶው የወደቀው  ከሁመራ ከተማ 30 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው እንድሪያስ ቀበሌ ነው። በዚህም የተነሳ ሁመራ ከተማን ጨምሮ በዳንሻ፣ ባዕከር፣ አዲረመጥ፣ ሶረቃ፣ ማይካድራ፣ አብደራፊ፣ አብርሃጅራ፣ አዲጎሹ እና አደባይ እንዲሁም በሁሉም የገጠር ቀበሌዎች ከሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጡን ተናግረዋል። የወደቀውን አንድ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ለመጠገን የቴክኒክ ቡድን በሥፍራው ደርሶ ጥገና መጀመሩን የገለፁት ዳይሬክተሩ ጥገናውን ለማጠናቀቅ እስከ አስር ቀናት ሊፈጅ እንደሚችልም ጠቁመዋል። ህብረተሰቡ የደረሰው ጉዳት እስኪጠገን ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቅም ነው አቶ ውበት ጥሪ ያቀረቡት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ሰኔ 12 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

የኤሌክትሮ ሜካኒካልና የሳፕ ትራቭል ማኔጅመንት ሞጁል ስልጠና እየተሰጠ ነው ….......//…....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኤሌክትሮ ሜካኒካልና የሁለተኛው ምዕራፍ ሳፕ ትራቭል ማኔጅመንት ሞጁል ስልጠና መሰጠት መጀመሩን በተቋሙ የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ቢሮ ገለጸ፡፡ የቢሮው ስራ አስኪያጅ ተወካይ አቶ ባትሪ ደረሰ እንደገለጹት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባሉ የተለያዩ ኃይል ማመንጫዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚመደቡ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ቴክኒሺያኖች ስልጠና መሰጠት ጀምሯል፡፡ ለአራት ወራት በሚቆየው ስልጠና ላይ 77 ሰልጣኞች ተካተው በሶስት የተለያዩ ቦታዎች ማለትም በኮተቤ ማሰልጠኛ፣ በአዳማ ንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ እና እና በአዳማ ማከፋፈያ ጣቢያ እየተሰጠ ይገኛል፡፡ ከሰልጣኞቹ መካከል 56 የሚሆኑት ከተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች የተመለመሉ አዲስ ሰልጣኞች ሲሆኑ ቀሪዎቹ 21 ሰልጣኞች ደግሞ ከድርጅቱ ሰራተኞች መካከል ትምህርታቸውን በማሻሻላቸው ለስልጠናው የተመለመሉ መሆናቸውን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ የኤሌክትሮ ሜካኒል ስልጠናው የድርጅቱን የሰው ኃይል ክፍተት በመሙላት ዓይነተኛ ሚና ሲወጣ መቆየቱን የገለፁት አቶ ባትሪ ከድርጅቱ ማሰልጠኛ ማዕከል በኤሌክትሮ ሜካኒካል ሰልጠነው ለከፍተኛ ኃላፊነት የበቁ የተቋሙ ሰራተኞች መኖራቸውን አስታውሰዋል፡፡ በዚህኛው ዙር ስልጠና ከአርብቶ አደር አካባቢ ለተመለመሉ ሰልጣኞች ልዩ ድጋፍ የሚያገኙበት አቅጣጫ ተቀምጦ በሥራ ላይ መዋሉንም ጠቁመዋል፡፡ እንደ አቶ ባትሪ ገለፃ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስልጠናውን ይዘትና የስልጠና አሰጣጡን ለማሻሻል የሚያስችሉ ጥረቶች ተጀምረዋል፡፡ አሁን በተጀመረው የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስልጠና ላይ ቀጣይነት ያለው የሰልጣኞች ምዘና ሥርዓትን (Continuous assessment) እንዲሁም ሰልጣኞች ከቴክኒካል ዕውቀት በተጨማሪ ባህሪያዊ እሴቶችን (Behavioral values) የሚጨብጡበት መርሃግብሮች ተካተው እንደሚሰጡ ገልፀዋል፡፡ በተያያዘ ዜና የሳፕ ምዕራፍ ሁለት ትግበራ ውስጥ ከተካተቱት ሞጁሎች ውስጥ የትራቭል ማኔጅመንት የተጠቃሚዎች ስልጠና በይፋ መጀመሩን አቶ ባትሪ ተናግረዋል፡፡ በሁለተኛው ምዕራፍ የሚተገበረው የትራቭል ማኔጅመንት ሞጁል በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ያለውን የአበል አከፋፈል ሥርዓት ለማዘመን ከማዕከል ሆኖ ቁጥጥር ለማድረግ ያስችላል ብለዋል፡፡ ስልጠናው በተግባርና በንድፈ ሀሳብ ታግዞ እንደሚሰጥ የገለጹት ኃላፊው በሥልጠናው ላይ ከሁሉም የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችና ሪጅኖች የተውጣጡ የፋይናንስ ባለሙያዎች እየተሳተፉ እንደሚገኙ ጠቁመዋል፡፡ ለሳፕ ምዕራፍ ሁለት የሞጁል ስልጠና 50 ኮምፒዩተሮች ያሉት የኮምፒውተር ስልጠና ማዕከል መቋቋሙን ገልፀዋል፡፡ የስልጠና ማዕከሉ የሚጠበቅበትን ተግባር በበለጠ እንዲወጣ የተለየ ክለላ(Zoning) ኖሮት ከተሽርካሪና ከእግረኛ ማቋረጫነት ተጠብቆ እንዲደራጅ የሚመለከተው አካል ሁሉ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጠይቀዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ሰኔ 12 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

አዲስ የተገነቡት የዕቃ መጋዘኖች ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓቶችን ለመዘርጋት ዕድል ፈጥረዋል ...///... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተገነቡት የዕቃ መጋዘኖች ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓቶችን ለመዘርጋት ዕድል መፍጠራቸውን በተቋሙ የንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ዘርፍ አስታወቀ፡፡ የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ስመኝ አያሌው እንዳስታወቁት ተቋሙ ለበርካታ ዓመታት ይጠቀምባቸው የነበሩትን ጠባብና አሮጌ የዕቃ መጋዘኖች የካይዘንና መሰል ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓቶችን ለመዘርጋት በሚያስችል ምቹ መጋዘኖች እየቀየረ ነው፡፡ አዲስ በተገነቡት መጋዘኖች ያለ አግባብ በየቦታው ተቀምጠው የነበሩ ዕቃዎችን በአንድ ላይ በመሰብሰብ ከፀሐይ፣ ከአቧራ እና ከዝናብ መከላከል መቻሉን ተናግረዋል። መጋዘኖቹ ብዛት ያላቸው የተለያዩ ዕቃዎች እንዲይዙ ተደርገው ከመገንባታቸውም በላይ የሙቀት መቆጣጠሪያ መሳሪያ የተገጠመላቸው መሆናቸውንም ነው የገለፁት። በተቋሙ የዕቃ ግምጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ፈለቀ ክፍሌ እንደተናገሩት የዕቃ መጋዘኖቹ መገንባት ለሠራተኞች ምቹ የቢሮና የሥራ አካባቢ ፈጥረዋል፡፡ የሳፕ የአሰራር ሥርዓትን ተግባራዊ በማድረግ ቀልጣፋና ዘመናዊ የቁጥጥርና የክትትል ሥራዎች እንዲከናወኑ ማስቻሉንም ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 11 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

እንኳን ለኢድ አል-አድሃ - አረፋ በዓል አደረሳችሁ! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በዓሉ የሠላም፣ የደስታ እና የመተሳሰብ እንዲሆንልዎ ከልብ ይመኛል! ኢድ ሙባረክ!