ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 543 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 332 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 157 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 543 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 27 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 10، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -16، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 25.06‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.33‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 895 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 539 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 7.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 28 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 543
المشتركون
-1624 ساعات
-97 أيام
+1030 أيام
أرشيف المشاركات
ለኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ግብዓት አቅርቦት የፊርማ ስምምነት ተከናወነ                           ……////……… ሥምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ  ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የኢትዮ-ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ ናቸው፡፡ ሥምምነቱ በዋናነት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሚገነባቸው የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ግብዓት የሚሆኑ ዕቃዎችን አምርቶ ለማቅረብ የሚያስችል እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢ/ር አሸብር ባልቻ በሁለቱ ተቋማት መካከል የተደረገው ሥምምነት ሃገራዊ ምርትን በመጠቀም የውጭ ምንዛሬን ለማዳንና ጊዜን ለመቆጠብ ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ገልፀዋል፡፡ እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ለተቋሙ  የሚያስፈልጉ የኤሌክትሪክ ግብዓቶችን ከሃገር ውስጥ ማሟላት ከተቋሙም አልፎ ለሃገራዊ ዕድገት ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል፡፡    የሁለቱን ተቋማት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጠው ይህ ስምምነት ተግባራዊ እንዲሆን የኢፌዴሪ የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ላደረገው ድጋፍ ሥራ አስፈፃሚው ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ሥራ አስፈፃሚው አክለውም የኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ተቋሙ በቅርቡ ለሚጀምራቸው የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት የሚያገለግሉ ግብዓቶችን ማምረት እንዲጀምር እምነታቸውን ገልፀዋል፡፡  የኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ በበኩላቸው ተቋማቸው የሚያመርታቸውን የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ግብዓት ለተቋሙ ትልቅ ጥቅም እንደሚሰጡ ተናግረዋል፡፡ ወደ ሃገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶችን በውጭ ምንዛሬ ማስገባት ተቋማዊ ዕደገትን የሚያቀጨጭ እና የሃገር ኢኮኖሚን የሚጎዳ በመሆኑ የራስን ምርት በጥራት አምርቶ መጠቀም ያስፈልጋል፡፡ የሃገር ውስጥ ምርቶች ጥራት የላቸውም የሚል አመለካከት መኖሩን የጠቀሱት አምባሳደሩ ይህን አመለካካት የሚያስቀይር ሀገሪቱ ጥራት ያላቸው ምርቶችን በማምረት ከራስ ፍጆታ አልፎ ለዓለም አቀፍ ገበያ እያቀረበች መሆኑን  አስረድተዋል። የራስን ምርት አክብሮ መጠቀም ትልቅ ኢኮኖሚያዊ ለውጥ እንደሚያመጣ ከሌሎች ሃገራት ብዙ ተሞክሮ ሊወሰድ ይገባል ብለዋል፡፡ ስለሆነም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሚገነባቸው የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ግብዓት የሚሆኑ ምርቶችን ተቋሙ በሚፈልገው ዓይነትና ጥራት አምርቶ ለማቅረብ ድርጅታቸው ቁርጠኛ ነው።  በሁለቱ ተቋማት መካከል የተፈረመው ሥምምነት ከምርት አቅርቦት በተጨማሪ የሠው ሃይል አቅምን ለማሳደግና የእውቀት ሽግግር እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን አምባሳደሩ ተናግረዋል፡፡ የኢፌዴሪ የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር የማኑፌክቸሪንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ገረመው ቀኖ  ሁለቱ ተቋማት ያደረጉት ሥምምነት የልማት ድርጅቶች ተባብረው በመሥራት በጋራ ተጠቃሚ መሆን እንደሚቻል ያሳየ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በቀጣይም በመሠረተ ልማት ግንባታ፣በኢንዱስትሪ እና በሌሎች ምርቶች የተሰማሩ የመንግስት የልማት ድርጅቶች በጋራ ሰርተው ለውጥ እንዲያመጡ ዘርፋቸው ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አቶ ገረመው ተናግረዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ግንቦት 08 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

የሴቶች ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ የሥርዓተ ፆታ ተወካዮች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ሊወጡ ይገባል ተባለ ………..////………… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚገኙ የሴት ሠራተኞች እና የአካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተቋሙ የሥራ ቦታዎች የሚገኙ የሥርዓተ ፆታ ተወካዮች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ መወጣት እንዳለባቸው በተቋሙ የሴቶች፣ህፃናትና ወጣቶች መምሪያ አሳሰበ። መምሪያው የሥርዓተ ፃታ ጉዳይን በተቋሙ የሥራ ቦታዎች ወጥነት ባለው መልኩ ለመተግበር የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በሪጅኖች፣ ማመንጫ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለሚገኙ የሥርዓተ ፆታ ጉዳይ ተወካዮች መስጠት ጀምሯል። የመምሪያው ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኤዲኤ እንደተናገሩት በተቋሙ የሥራ ቦታዎች የሥርዓተ ፆታ ጉዳይን ወጥነት ባለው መልኩ በመተግበር ላይ ክፍተቶች ይስተዋላሉ። ተወካዮቹ በሥርዓተ ፆታ ፅንሰ ሃሳብ እና በአሰራር መመሪያው ላይ የግንዛቤ ክፍተቶች ስላሉባቸው የሥርዓተ ፆታ ጉዳዮችን ወጥነት ባለው መልኩ መተግበር እንዳልተቻለ ዳይሬክተሯ አንስተዋል። እንደ ወ/ሮ ሌንሴ ገለፃ ስልጠናው በስርዓተ ፆታ ፅንሰ ሃሳብ ላይ ግንዛቤ በመያዝ የሴቶችን ተጠቃሚነት በእውቀት ላይ ተመስረተው እንዲሰሩ ለማድረግ እና የአሰራር መመሪያውን በአግባቡ ለመተግበር ያግዛል። የሥርዓተ ፃታ ጉዳይን በተቋሙ የሥራ በታዎች ወጥነት ባለው መልኩ ለመተግበር እና ተወካዮቹ ሥራቸውን በትብብር እንዲሰሩ ለማስቻል ስልጠናው ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረውም አመላክተዋል። በተቋሙ የሚከናወኑ ሥራዎች የሥርዓተ ፆታ ጉዳይን ባካተተ መልኩ እንዲፈፀሙ ተወካዮች በሥራ ቦታቸው ባሉ የተለያዩ ኮሚቴዎች ላይ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለባቸው ያነሱት ዳይሬክተሯ ለዚህም በየሥራ ቦታዎቹ የሚገኙ ኃላፊዎች የሥርዓተ ፆታ ተወካዮችን በኮሚቴ አባልነት ማካተት ይኖርባቸዋል ብለዋል። ከሥርዓተ ፃታ አካታችነት ጎን ለጎን የአካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሥራ ቦታዎች ላይ ምቹ የሥራ ከባቢ እንዲፈጠር ተወካዮቹ የበኩላቸውን ሚና መወጣት እንዳለባቸውም ጠቁመዋል ። ከግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው በተጨማሪ ተወካዮች እያጋጠሟቸው ባሉ ችግሮች ላይ ውይይት በማድረግ በቀጣይ ድጋፍ የሚደረግበት አሰራር እንደሚዘረጋ ዳይሬክተሯ አረጋግጠዋል። ተሳታፊዎቹ ስልጠናውን በአግባቡ በመከታተል ወደ ሥራ ቦታቸው ሲመለሱ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል። ከግንቦት 8 እስከ 9 ቀን 2016 ዓም እየተሰጠ ባለው ስልጠና ላይ 24 የሥርዓተ ፆታ ጉዳይ ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 08 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

የማህበረሰባዊ እሴቶችን በመጠቀም የመሠረተ ልማት ስርቆትን መከላከል ተችሏል ………..////………… የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ስርቆትን ከመደበኛው ህግ በተጨማሪ የማህበረሰቡን እሴት መጠቀም ውጤት እያመጣ መሆኑን በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ዘርፍ የሰሜን ምስራቅ ሪጅን 2 መምሪያ ገለፀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ሀሰን መሃመድ እንደገለፁት በ2016 በጀት ዓመት 10 ወራት ውስጥ ሪጅኑ በሚያስተዳድራቸው የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ ምንም ዓይነት ስርቆት አልተፈፀመም፡፡ በ2015 በጀት ዓመት 2 የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ ስርቆት መፈፀሙን ያስታወሱት አቶ ሀሰን በዳጉ የመረጃ መቀባበያ ስልት ክትትል ተደርጎ በአጥፊዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ገልፀዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ የክልሉ የፀጥታ ቢሮ እና ሪጅኑ በመተባበር ለእያንዳንዱ ወረዳ እንዲሁም የአካባቢው የጎሳ መሪዎች ስለ መሰረተ ልማት ጥበቃ የማስገንዘብ ሥራ ተሰርቷል፡፡ አካባቢው ሙቀት በመሆኑ ኤሌክትሪክ ለማህበረሰቡ ትልቅ ትርጉም እንዳለው ያነሱት ዳይሬክተሩ ማህበረሰቡም ለመሠረተ ልማቱ የሚሰጡት ትኩረት ከፍ ያለ ነው ብለዋል፡፡ በተጨማሪም ስርቆት የማህበረሰቡ መልካም እሴት ባለመሆኑ በሪጅኑ ውስጥ የሚስተዋሉ የስርቆትና መሰል ተግባራትን የአፋር ህዝብ እሴት በሆነው የዳጉ መረጃ መቀባበያ ሥርዓት ክትትል ተደርጎ እንደሚያዙም ነው የተገለፀው፡፡ የሰሜን ምሥራቅ ሪጅን 1 በሥሩ 3 የማከፋፈያ ጣቢያና 450 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመሮችን አሉት፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ግንቦት 07 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ጉብኝቱ የኢንደስትሪ ምርቶችን ለማሳወቅ እና የሀገር ውስጥ ምርቶችን ለመጠቀም ለተቋማት ዕድል የሚፈጥር ነው በሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሄደ ያለው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በሀገር ውስጥ እየተከናወኑ ያሉ የኢንደስትሪ ምርቶችን ለማሳወቅ እና የሀገር ውስጥ ምርቶችን ለመጠቀም ዕድል የሚፈጥር መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ተናግረዋል። የተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ከግንቦት 1 እስከ 5 ቀን 2016 ዓ.ም እየተካሄደ ያለውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በዛሬው ዕለት ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት በተቋሙ የኢንጅነሪንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ውድነህ የማነ እንደገለፁት ጉብኝቱ ሀገሪቱ እየሄደችበት ያለውን የኢንዱስትሪ ጉዞ ለማወቅና ተቋማት ከሃገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች ምን ዓይነት ምርቶችን ማግኘትና መጠቀም እንዳለባቸው ለመለየት ያስችላል። በሀገር ውስጥ ይመረታሉ ተብለው የማይታሰቡ እና ለተቋሙ ግብዓት የሚሆኑ የተለያዩ ምርቶችን በጉብኝቱ ላይ መመልከታቸውንም አንስተዋል። መንግስት የውጭ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ተቋሙ የሀገር የሀገር ውስጥ ምርቶችን ለመጠቀም ዝግጅት እያደረገ እንደሆነም ሥራ አስፈፃሚው አመላክተዋል። ተቋሙ ከዚህ በፊት ከኢትዮ ኢንጅነሪንግ ግሩፕ ጋር ስምምነት በማድረግ ወደ ሥራ መግባቱን ያወሱት አቶ ውድነህ በቀጣይ በኤክስፖው ላይ ከተሳተፉ አምራች ድርጅቶች ጋር ስምምነት በማድረግ የሀገር ውስጥ ምርቶችን ለመጠቀም በቁርጠኝት እየሰራበት እንደሆነም ተናገረዋል። ይህም ለተቋሙ የውጭ ምንዛሬን በማስቀረት በኩል ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል። በዐውደርዕዩ ላይ የቀረቡ ምርቶች በሀገሪቱ ኢንደስትሪዎች እየተስፋፉ መምጣታቸውን የሚያሳዩ ናቸው ያሉት አቶ ውድነህ ይህም ተቋሙ የኢንደስትሪዎችን ዕድገት ታሳቢ ያደረገ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ በትኩረት መሠራት እንዳለበት ያመላከተ ነው፡፡ በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት የአስተዳደራዊ ጉዳዮች እና ዶክመንቴሽን ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ በበኩላቸው ጉብኝቱ ከተቋሙ የሥራ ባህሪ ጋር የሚገናኙ የተለያዩ ምርቶችን በመውሰድ ጥቅም ላይ ለማዋል ዕድል ይፈጥራል። እንደ ኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ያሉ ምርቶች በአውደ ርዕዩ ላይ መቅረባቸውን ያነሱት ስራ አስኪያጁ ይህም በሀገር ውስጥ ምርት ሀገራዊ ተቋም ለመገንባት እየተሰራ ካለው ስራ በተጨማሪ ለተሸከርካሪዎቹ ከሚቀርበው የኤሌክትሪክ ኃይል ገቢ ለማግኘት ያስችላል፡፡ በጉብኝቱ ላይ ከተሳተፉት የተቋሙ ሠራተኞች መካከል አቶ ደረሰ ዳንኤል እና አቶ ዳንኤል ተስፋዬ እንደተናገሩት የተቋሙ ሠራተኞች አውደርዕዩን እንዲጎበኙ መደረጉ ሀገሪቱ በኢንደስትሪው ዘርፍ የምታከናውናቸውን ሥራዎች እንዲያውቁ ዕድል ይፈጥራል። ጉብኝቱ ሠራተኛው የኢንደስትሪ ቴክኖሎጅዎችን እንዲያውቅ ከማድረጉ በተጨማሪ በሀገሪቱ ላይ ያለውን የተዛባ አመለካከት እንደሚቀይር ተናግረዋል፡፡ በቀጣይ በሀገሪቱ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችን ለማስገንዘብ ይህን መሰል ጉብኝት መደረግ እንዳለበትም አሳስበዋል። ከግንቦት 1 ቀን እስከ 05 ቀን 2016 ዓ.ም በኢንደስትሪ ሚኒስቴር አዘጋጅነት እየተካሄደ ያለው ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ የዘንድሮው ለ3ኛ ጊዜ የተዘጋጀ ነው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 05 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

photo content
+9

photo content
+7

ተቋማዊ ሥጋቶችን በመለየት ዘላቂ መፍትሄ ማስቀመጥ ያስፈልጋል ........///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚያከናውናቸውን የኃይል መሠረተ ልማቶች ግንባታና የኦፕሬሽን ሥራዎች ሊጎዱ የሚችሉ ስጋቶችን በመለየት ዘላቂ መፍትሄ ማስቀመጥ እንደሚገባ ተጠቆመ ። የኢፌዲሪ የመንግሥት የልማት ድርጀቶች ይዞታና አስተዳደር የተቋሙን 9 ወራት ክንውን ገምግሟል። የተቋሙን የዘጠኝ ወራት አፈፃፀም ሪፖርት ያቀረቡት የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ ተቋሙ በፕሮጀክት ግንባታ፣ በኦፕሬሽን፣ በለውጥ ሥራዎች፣ በፋይናንስ እንዲሁም በሠው ኃይል አስተዳደርና አቅም ግንባታ የነበረውን አፈፃፀም አቅርበዋል። በግንባታ ላይ ያሉ የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች የፊዚካል አፈጻጸም  ከ70 በመቶ በላይ እና የፋይናንስ ደግሞ ከ66 በመቶ በላይ እንደሆነ በሪፖርቱ አመልክተዋል። እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ በጸጥታ ችግር ግንባታቸው ከተስተጓጎሉ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ውጪ ያሉ ፕሮጀክቶች አማካይ አፈጻጸም ከ85 በመቶ በላይ ደርሷል። ተቋሙ በኦፕሬሽን ዘርፍ ከ15 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል በማምረት የዕቅዱን 94 በመቶ ማሳካቱን የገለፁት አቶ አንዱዓለም ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ14 በመቶ ዕድገት አሳይቷል ብለዋል። ተቋሙ ከሃገር ውስጥ የኃይል ሽያጭ   13 ነጥብ 8 ቢሊዮን ለመሠብሰብ አቅዶ 14 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በመሠብሰብ ከዕቅድ በላይ ማሳካት ቢችልም ከኃይል ኤክስፓርት የተገኘው ገቢ ግን ከዕቅዱ ያነሰ መሆኑን ጠቅሰዋል። በሠው ኃይል አስተዳደር ስምሪትና አቅም ግንባታ፣ በለውጥ ሥራዎች እንዲሁም ሀብትን በማስተዳደር የታዩ አፈጻጸሞች አበረታች መሆናቸውን ገልፀዋል። በመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ የኢነርጂ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሀገሬ ውሂብ በበኩላቸው የኃይል ምርት ዕድገትና የአቅርቦት መሻሻሎች፣ ተቋሙን ለማዘመን እየተሠሩ ያሉ የለውጥ ሥራዎች፣ ወቅታዊ የሂሳብ መግለጫ ዝግጅት እንዲሁም ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም የማከናወን ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልፀዋል። ውዝፍ የውጭ ሀገር የኃይል ሽያጭ ገቢን በመሠብሰብ፣ የታሪፍ ጥናትን አስፀድቆ ተግባራዊ በማድረግ እና የብድር ክፍያ አፈጻጸምን በማሻሻል የተቋሙን የፋይናንስ ቁመና ማሻሻል ያስፈልጋል ብለዋል። ተቋሙ የለያቸውን የፀጥታ ስጋቶች፣ የኃይል መሠረተ ልማት ሥርቆት፣ የካሳ ክፍያና ወሠን ማስከበር እንዲሁም የታሪፍ ተመጣጣኝ አለመሆን እና የውጭ ምንዛሬ ለውጥ ስጋቶችን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን  ዘላቂ መፍትሄ ማስቀመጥ እንደሚኖርበትም ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በግምገማው ማጠቃለያ ላይ እንደገለፁት የተቋሙን ወጭ የሚቀንሱ አሠራሮችን በመዘርጋት እና የገቢ ማስገኛ አማራጮችን በማስፋት የተቋሙን የፋይናንስ አቅም ለማሳደግ በትኩረት ይሠራል። ተቋሙ የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝና ተደራሽ በማድረግ ደንበኞቹን ለማርካት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል። ዘርፉን የሚጎዱ የሥጋት አካባቢዎችን በመለየት ዘላቂ መፍትሔ የሚያመጡ አማራጮች ተግባራዊ እንደሚደረጉ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አረጋግጠዋል። ከፀጥታና ከመሠረተ ልማት ስርቆት ጋር የሚስተዋሉ ችግሮችን ከሚመለከታቸው የክልል መስተዳድሮች ጋር በመመካከር ለመፍታት አቅጣጫ መቀመጡን ጠቁመዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ግንቦት 04 ቀን 2016 ዓ.ም

ዘርፉ የተጣለበትን ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጣ በትብብር መስራት ይገባል በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጅነሪንግ ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ባለፉት አምስት ዓመታት በተገኙ መልካም ተሞክሮዎች እና ተግዳሮቶች እንዲሁም በ2016 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ላይ ወይይት አካሄዱ። የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ውድነህ የማነ እንደገለፁት ባለፉት አምስት ዓመታት እንደዘርፍ በርካታ ውጤቶችና መልካም ተሞክሮዎች ተገኝተዋል። ከዚሁ ጎን ለጎን ለአፈፃፀም ክፍተት የሆኑ ተግዳሮቶች ማጋጠማቸውንም ጠቁመዋል። የውይይይ መድረኩ ዘርፉ በቀጣይ ለሚያከናውናቸው ሥራዎች ከሠራተኞች በቂ ግብዓት ለመሠብሰብና በተደጋጋሚ ለሚያጋጠሙ ተግዳሮቶች ዘላቂ የጋራ መፍትሔ ለማስቀመጥ እንደተዘጋጀ የተናገሩት ሥራ አስፈፃሚው ውይይቱ ሠራተኛው በእኔነት ስሜት እንዲሰራና የተቋሙን ስትራቴጅክ ዕቅድ ውጤታማ በሆነ የአሰራር ስርዓት ለመተግበር ያስችላል። እንደ አቶ ውድነህ ገለፃ ባለፉት አምስት ዓመታት የዘርፉ የማማከር አቅም እያደገ የመጣ ቢሆንም ከባለድርሻ አካላትና የፕሮጀክት ባለቤቶች ጋር የነበረው ግንኙነት የተጠናከረ አለመሆን፣ በፕሮጀክት ሥራ ላይ የባለቤትነት ክፍተቶች መኖርና በዘርፉ ውስጥ ያሉ የሥራ ክፍሎች እንደ አንድ አማካሪ ድርጅት ተቀናጅተው አለመስራት የታዩ ክፍተቶች ናቸው። በውይይቱ ላይ ከሥራ ክፍሎች አደረጃጀት፤ ከደመወዝና ጥቅማ ጥቅም፣ ከደረጃ ዕድገትና ዝውውር፤ ለሥራ ከሚያስፈልጉ ሶፍትዌሮች፣ አዳዲስ ቴክኖሎጅዎች፣ የሥራ ላይ ደህንነት መጠበቂያ መሳሪያዎች እና ከሌሎች ግብዓቶች ቅርቦት ጋር በተያያዘ ከሠራተኞች ጥያቄዎች ተነስተዋል። በተጨማሪም ከስልጠና ተደራሽነት፣ ከሥራ መዘርዝርና የሠራተኞችን ደህንነት ከማረጋገጥ አኳያ እየተከናወነ ስላለው ሥራ በተመለከተ ከሠራተኞች ለተነሱ አስተያየቶችና ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል። በውይይቱ ላይ ተገኝተው ከሠራተኞች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የሰው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ አቶ አታላይ አበበ የሠራተኛውን የደመወዝና ጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በፊት ጥናት መደረጉን አስታውሰው ጥናቱ ላይ ማሻሻያ በማድረግ አሁን ካለው የኑሮ ሁኔታ ጋር የሚጣጣም ለማድረግ እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል። ከደመወዝ ጋር በተያያዘ በአንዳንድ የሥራ ክፍሎች የሠራተኛ ፍልሰቱ እየጨመረ እንደሆነ እና ፍልሰቱን ለመቀነስ የተቋሙን የፋይናንስ አቅም ባገናዘበ መልኩ መፍትሔ ለመስጠት እየተሰራ ነው። የደረጃ እድገትና ዝውውሩ በህብረት ስምምነቱ ድንጋጌዎች መሠረት እየተፈፀመ እንደሆነ ያነሱት አቶ አታላይ የሠራተኛውን አቅም ለማሳደግ ከሚሰጠው ስልጠና ባለፈ የዕርስ በዕርስ መማሪያ መድረኮችን ማጠናከር እንደሚገባም አፅንዖት ሠጥተዋል። በተቋሙ የፋይናንስ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ በበኩላቸው ተቋሙ ከኃይል ሽያጭ በተጨማሪ በኢንጅነሪንግ ዘርፍ ከሚከናወኑ ሥራዎች ገቢ ለማግኘት አቅዶ እየተሰራ እንደሆነ ገልፀው ዘርፉ የገቢ ማስገኛ ሥራዎችን በማስፉት ለተቋሙ ስትራቴጅክ ዕቅድ ስኬት ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለበትም አሳስበዋል። የሠራተኛውን የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ለመመለስ ተቋሙ ገቢ የሚያገኝበትን መንገድ ማሳደግና ወጪዎችን መቀነስ እንደሚገባም አቶ ደመረ አስገንዝበዋል። የተቋሙ መሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ በበኩላቸው ዘርፉን ተወዳዳሪ ለማድረግ በሠራተኞች የሚነሱ ጥያቄዎች መመለስ እንዳለባቸው አንስተው ለዚህም ማህበሩ ከሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች ጋር በመሆን እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ውድነህ የማነ በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ እንደተናገሩት ለዘርፉ ሥራ የሚያስፈልጉ የተለያዩ ግብዓቶችን ለማሟላት ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ይገኛል። የሠራተኛውን አቅም ለማሳደግ የሚሰጡ የሀገር ውስጥና የውጭ ስልጠናዎችን በአግባቡ መከታተል እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ለተቋሙ ስኬት ዘርፉ የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ ለማከናወን በትኩረት እንደሚሰራ የተናገሩት አቶ ውድነህ ለዚህም ሁሉም በትብብርና በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል። በቀጣይም ለዘርፉ ስኬታማነት ይህን መሠል የውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት ከሠራተኛው ሃሳቦችን የመቀበልና በግብዓትነት የመጠቀም እንዲሁም ለጋራ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት ከየዘርፉ ሥራ አስፈፃሚዎች ጋር በትብብር የመስራቱ ልምድ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

የኮይሻ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ለሠራተኞቹ ማዕድ አጋራ .........///.......... የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ፕሮጀክት የትንሣዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለፕሮጀክቱ የድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች ማዕድ ማጋራቱን የፕሮጀክቱ የሳይት አስተዳደርና አገልግሎት ቢሮ ገለፀ። የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ክብሮም ገ/መድህን እንደገለፁት በፕሮጀክቱ ላይ የሚገኙ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች ከሌሎች የፕሮጀክቱ ባለሙያዎች ጋር በዓሉን በጋራ እንዲያከብሩ ተደርጓል። በማዕድ ማጋራት ፕሮግራሙ ላይ 94 ሾፌሮች፣ የፅዳት፣ የጥበቃ፣ የአትክልት እና የጉልበት ሠራተኞች መሳተፋቸውን ተናግረዋል። ሠራተኞቹ በዓሉን በጋራ ማክበራቸው በመካከላቸው ያለውን የአብሮነት እና የመረዳዳት መንፈስ እንደሚያጠናክር አቶ ክብሮም ገልፀዋል። ፕሮጀክት ጽ/ቤቱ ለሠራተኞች ያለውን አጋርነት ለማሳየት በሌሎች በዓላትም ተመሳሳይ መርሃግብሮችን ሲያከናውን እንደነበርም ሥራ አስኪያጁ አስታውሰዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 28 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

photo content

ለትንሳዔ በዓል ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት በ25 በመቶ እድገት ያሳየ የኃይል አቅርቦት ዝግጁ ተደርጓል ..........///............ ለትንሳኤ በዓል የኃይል አቅርቦት ችግር እንዳያጋጥም ዝግጅት መደረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ። በማዕከሉ የሪል ታይም ኦፕሬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ጉልላት እንግዳ እንዳስታወቁት በዋዜማውና በበዓሉ ዕለት በመላው ሀገሪቱ የሚኖረው የኃይል ፍላጎት 3 ሺህ 497 ሜጋ ዋት ሊደርስ እንደሚችል ተተንብይዋል፡፡ በመሆነም ይህን ታሳቢ ያደረግ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መሰራታቸውን እና ሊመጣ የሚችል ተጨማሪ የኃይል ፍላጎትን ለማስተናገድ 300 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለመጠባበቂያነት ዝግጁ መደረጉን አስታውቀዋል፡፡ እንደ አቶ ጉልላት ገለፃ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ሁሉም ዩኒቶች ላይ የፍተሻ ሥራ በማከናወን ዩኒቶች ዝግጁ ተደርገዋል፡፡ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለኃይል መቋረጥ ምክንያት እንዳይሆኑ የቅድመ መከላከልና የፍተሻ ሥራዎች መከናወናቸውንም ጠቁመዋል፡፡ አምና በተመሳሳይ ወቅት የኃይል ፍላጎቱ 2 ሺህ 850 ሜጋ ዋት ሊደርስ እንደሚችል ተተንብዮ ለዚያ የሚሆን ኃይል ዝግጁ መደረጉን እንዲሁም ተጨማሪ 350 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለመጠባበቂያነት መያዙን አስታውሰዋል፡፡ ለዘንድሮ የትንሳዔ በዓል ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት በ25 በመቶ ዕድገት ያለው የኃይል አቅርቦት ዝግጁ መደረጉን አስታውቀዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ በበዓሉ ወቅት የኃይል መቆራረጥ እንዳይከሰት ለማድረግ ከተቋሙ በቀጥታ ኃይል የሚያገኙ የዳታ ማይኒንግ ኩባንያዎች እና ከፍተኛ ቮልቴጅ ተጠቃሚዎች ኃይልአጠቃቀማቸውን እንዲቀንሱ ተደርጓል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል ካሉ ደንበኞች መካከልም ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎችና ዳታ ማይኒንግ ኩባንያዎች ኃይል አጠቃቀማቸውን እንዲቀንሱ ከስምምነት ተደርሷል፡፡ ከበዓሉ ጋርተያይዞ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን ለመፍታት እና በሚሰራው ሥራ ላይ ውሳኔ ለሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች መፍትሔ ለመስጠት በየደረጃው የሚገኙ የዘርፍ ኃላፊዎችና የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል የሥራ ኃላፊዎች በኦፕሬሽን ሥራው ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 26 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ሠራተኞች ማዕድ አጋሩ ...///… በመጪው የሚከበረውን የትንሳዔ በዓል ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የክርስትና እምነት ተከታይ ለሆኑ 130 የተቋሙ ሴት የፅዳት እና ጥበቃ ሠራተኞች ማዕድ አጋርተዋል። ማዕድ በማጋራት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በመገኘት ለሠራተኞቹ የተዘጋጀውን ስጦታ ያበረከቱት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ናቸው፡፡ በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት የአስተዳደራዊ ጉዳዮችና ዶክዩመንቴሽን ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደተናገሩት ሠራተኛው ያደረገውን ድጋፍ አመስግነው በቀጣይ መሰል ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። የገንዘብ አሰባሳቢ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ አብደላ ሻንቆ በበኩላቸው የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ሴት ሠራተኞች ማዕድ ለማጋራት ከተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ገንዘብ የማሰባሰብ  ሥራ ሲከናወን መቆየቱን ተናግረዋል። እንደ አቶ አብደላ ገለፃ የኢድ-አልፈጥር እና ትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ ከተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ከ213 ሺህ ብር በላይ  በበጎ ፈቃደኝነት ተሰብስቧል። ከተሰበሰበው ገንዘብ ውስጥ 159 ሺህ 120 ብር የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ ዝግተኛ ገቢ ላላቸው ሴት ሠራተኞች ስጦታ ተሰጥቷል። በዛሬው ዕለት የክርስትና እምነት ተከታይ ለሆኑ የተቋሙ 126 የፅዳት እና 4 የጥበቃ ሴት ሠራተኞች ለእያንዳንዳቸው የ1220 ብር የዓይነትና የጥሬ ገንዘብ  ድጋፍ ተደርጓል። በተቋሙ ሠራተኞችና አመራሮች የተጀመረው ማዕድ የማጋራት ሥራ አስተባባሪ ከተገኘ ሠራተኛው በተለያዩ ማህበራዊ ችግሮች ላይ ተሳትፎውን በማጎልበት ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ያሳየበት ነው ተብሏል። ድጋፍ የተደረገላቸው ሠራተኞች በበኩላቸው የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች በአሁኑ ወቅት ያለውን የኑሮ ሁኔታ ተረድተው ላደረጉት ድጋፍ አመስግነዋል። የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ባሳለፍነው የኢድ-አልፈጥር በዓል ላይም ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የእስልምና እምነት ተከታይ ለሆኑ 36 የተቋሙ ሴት የፅዳት ሠራተኞች የ54 ሺህ ብር የአይነትና የጥሬ ገንዘብ ማዕድ ማጋራታቸው ይታወሳል።     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9