ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 540 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 340 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 161 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 540 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 28 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 1، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -4، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 24.98‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.34‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 882 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 539 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 8.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 29 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 540
المشتركون
-424 ساعات
-147 أيام
+130 أيام
أرشيف المشاركات
ኢትዮጵያ በቀጣናው የጀመረችውን የኃይል ትስስር አጠናክራ ትቀጥላለች ………///…….. ኢትዮጵያ በቀጣናው የጀመረችውን የኃይል ትስስር አጠናክራ እንደምትቀጥል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ ለጎረቤት አገራት እያቀረበች ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል የበለጠ ለማስፋፋት እየሰራች ነው። ኢትዮጵያ ለሱዳን፣ ለጅቡቲና ለኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል እያቀረበች መሆኑን ገልጸው ለውጭ ገበያ የሚቀርበውን የኤሌክትሪክ ኃይል እስከ ደቡብ አፍሪካ የማድረስ ዕቅድ መያዙን ተናግረዋል። በቅርቡም ለታንዛኒያ ኃይል ለማቅረብ መግባባት ላይ መደረሱን ጠቁመው ደቡብ ሱዳን፣ ኡጋንዳና ሩዋንዳ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለመውሰድ ፍላጎት ማሳየታቸውን ጠቁመዋል። ይህንንም ተከትሎ ኢትዮጵያ ከሀገራቱ ጋር ንግግር መጀመሯን ገልጸው በቀጣይም በቀጣናው የጀመረችውን የኃይል ትስስር አጠናክራ እንደምትቀጥል ነው ያረጋገጡት። እንደ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ሥርቆት እየተበራከተ መሆኑን ጠቁመው ይህን ለመከላከል የኅብረተሰቡ እና በየደረጃው የሚገኙ የመንግስት መዋቅሮች ተሳትፎና ቁርጠኝነት ያስፈልጋል። የመሰረተ ልማቶች ስርቆት በኤሌክትሪክ የተለያዩ አገልግሎቶች የሚሰጡ ተቋማት ላይ ከፍተኛ መስተጓጎል እንደሚፈጥር ጠቅሰው ይህም በሀገር ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንደሚያደርስ ተናግረዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 20 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

የኤሌክትሪክ ኃይል ታሪፍ ወጪን ታሳቢ ያደረገ አለመሆኑን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ ….......//…....... የኤሌክትሪክ ኃይል ታሪፍ ለማምረት የሚወጣውን ወጪ ያማከለ አለመሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ። ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የእንግሊዝ ኤምባሲ ባዘጋጀው የዩኬ-ኢትዮጵያ አረንጓዴ ቴክኖሎጂ ፎረም ላይ እንደተናገሩት በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚሸጥበት ታሪፍ ወጪን ያላማከለ ነው። ከዚህም ባለፈ በኢነርጂ ዘርፉ መዋዕለ ንዋያቸውን ለማፍሰስ የሚፈልጉ ባለሃብቶችን የማያበረታታና በቂ ክፍያ የማያስገኝ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በኢነርጂ ዘርፉ ላይ ለተቋሙ አስቸጋሪው ጉዳይ ታሪፍ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈጻሚው  ተናግረዋል፡፡ እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ በዓለም ባንክ አጋዥነት የውጭ አማካሪ በመቅጠር የታሪፍ፣ የማምረቻ ዋጋ እና የኦፕሬሽን ወጪ  ልዩነት ችግሮችን የተመለከተ ጥናት ተደርጓል፡፡ በአማካሪ ድርጅቱ የተዘጋጀውን ጥናት ለኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን እና በየደረጃው ለሚገኙ አካላት በማቅረብ እንደሚገመገም ኢንጂነር አሸብር ጠቅሰዋል፡፡ በዩኬ-ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ቴክኖሎጂ ፎረም ላይ በኢነርጂ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ በርካታ የእንግሊዝ የግል ድርጅቶች፣ አማካሪዎችና ሌሎች የመንግሥት ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     መጋቢት 20 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

ኢትዮ - ኤሌክትሪክ አሸናፊነቱን አጠናክሮ ቀጥሏል .........///......... በሐዋሳ ስቴዲየም በተከናወነ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ወልድያ ከተማን ሶስት ለሁለት በማሸነፍ ወሳኝ ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል። ሁለቱም ቡድኖች ለማሸነፍ ብርቱ ፉክክር ባሳዩበት በዚህ ጨዋታ  የኢትዮ-ኤሌክትሪክን የማሸነፊያ ሁለት ጎሎች መሳይ ሰለሞን አንድ ጎል ደግሞ አቤል ሀብታሙ አስቆጥረዋል። በጨዋታው ሁለት ጎሎችን ያስቆጠረው መሳይ ሰለሞን የጨዋታው ኮከብ በመሆን የማሊያ ሽልማት ተበርክቶለታል። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ39 ነጥብ ሊጉን ሲመራ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀረው ኦሮሚያ ፖሊስ ክለብ በ11 ነጥብ ልዩነት ይከተላል። 18ኛው ሳምንት የከፍተኛ ሊግ መርሐግብር በመጪው ማክሰኞ መጋቢት 24 ቀን 2016 ዓ.ም የሚከናወን ሲሆን ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ጋር ይጫወታል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 20 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

የተቋረጠው ኃይል ሙሉ በሙሉ ተገናኝቷል .......///...... ለተወሰኑ ሰዓታት ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉ ተገናኝቷል። ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ዳግም ኃይል እንዲያገኙ
የተቋረጠው ኃይል ሙሉ በሙሉ  ተገናኝቷል .......///...... ለተወሰኑ ሰዓታት ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉ  ተገናኝቷል። ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ዳግም ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ የተደረገው ርብርብ ተሳክቶ በአሁኑ ወቅት ሁሉም አካባቢዎች ኃይል አግኝተዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     መጋቢት 19 ቀን 2016 ዓ.ም

በመላ ሀገሪቱ የተቋረጠው ኃይል መልሶ መገናኘት ጀምሯል .......///...... ዛሬ ከቀኑ 09:46 ጀምሮ ከባህርዳርና አካባቢው በስተቀር በመላው ኢትዮጵያ ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል መልሶ መገናኘት ጀምሯል። በዚህም መሰረት አብዛኛው የአዲስ አበባ ክፍል እና የተቀሩት የሀገሪቱ ክፍሎች መልሰው ኃይል ማግኘት ችለዋል። የተቀሩትን አካባቢዎች መልሶ ለማገናኘት ጥረቱ ቀጥሏል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 19 ቀን 2016 ዓ.ም

በመላ ሀገሪቱ ኃይል ተቋርጧል .......///...... ዛሬ ከቀኑ 09:46 ጀምሮ ከባህርዳርና አካባቢው በስተቀር በመላው ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉ ተቋርጧል። በሲስተማችን ላይ በገጠመ
በመላ ሀገሪቱ ኃይል ተቋርጧል .......///...... ዛሬ ከቀኑ 09:46 ጀምሮ ከባህርዳርና አካባቢው በስተቀር በመላው ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉ ተቋርጧል። በሲስተማችን ላይ በገጠመ ችግር ኃይል የተቋረጠ ሲሆን ለጊዜው የችግሩን ምክንያት ለማወቅ ጥረት እየተደረገ ነው። የተቋረጠውን ኤሌክትሪክ መልሶ የማገናኘት ሥራ የተጀመረ ሲሆን ችግሩን በመቅረፍ ዳግም ሲስተሙን መልሰን እስከምናገናኝ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን። የሚኖሩንን አዳዲስ መረጃዎችም በየጊዜው የምናሳውቃችሁ ይሆናል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 19 ቀን 2016 ዓ.ም

”ፕሮጀክቱ ብዙ ችግሮችን እንደሚፈታልን ተስፋ እናደርጋለ” የቃሊ ቀበሌ ነዋሪዎች ………..///………. በሀረሪ ክልል ሶፊ ወረዳ ሊገነባ የታሰበው ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ብዙ ችግሮችን እንደሚፈታ እምነት እንዳላቸው በሶፊ ወረዳ የቃሊ ቀበሌ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ የምሥራቃዊ ኤሌክትሪክ ግሪድ ማጠናከሪያ ፕሮጀክት አካል የሆነው ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ግንባታ ለማስጀመር የሚያስችሉ ውይይቶች ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ተደርጓል፡፡ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተውጣጡ የተወከሉ ባለሙያዎች ስለሚገነባው ፕሮጀክት ፋይዳ፣ ስለ ካሳ አከፋፈል ሁኔታ እና ፕሮጀክቱ ሲጀመር ለአካባቢው ማህበረሰብ ስለሚፈጥረው የሥራ ዕድል ለአካባቢው ነዋሪዎች አስረድተዋል፡፡ የሶፊ ወረዳ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊና የቃሊ ቀበሌ የልማት ተጠሪ አቶ አብዲ አወል እንደገለፁት የአካባቢው ነዋሪዎች የኤሌክትሪክ እና ሌሎች መሰረተ ልማቶች ጥያቄ ሲያነሱ ቆይተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ችግር ፈች የሆነ ትልቅ ፕሮጀክት ሊገነባ ማቀዱ ለአካባቢው ማህበረሰብና ለወረዳው ትልቅ ዕድል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቱ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ከተቋሙ ጋር በቅርበት ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል፡፡ የአካባቢው አርሶ አደር የሆኑት አቶ ቃሲም አብዱከሪም በበኩላቸው በአካባቢያቸው የሚገነባው ፕሮጀክት የንፁህ መጠጥ ውሃ እና የመብራት ችግሮችን እንደሚፈታላቸው ተስፋ ማድረጋቸውን ገልፀዋል፡፡ ሌላዋ የአካባቢው አርሶ አደር ወ/ሮ ሳሮ አሊይ በቀበሌዋ ምንም ዓይነት ውሃ ባለመኖሩ እስከ ስምንት ኪሎ ሜትር ተጉዞ ውኃ መቅዳት አሰልቺ የሴቶች የዘወትር ተግባር መሆኑን አንስተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ፕሮጀክቱን ሲገነባ ከኃይል አቅርቦት ጎን ለጎን ሌሎች ማህበራዊ ችግሮችን የሚፈታ በመሆኑ ግንባታው ሲጀመር እርሳቸውና ሌሎች የአካባቢው ነዋሪዎች ለፕሮጀክቱ መሳለጥ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል፡፡ ከሀረር ከተማ በ15 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሊገነባ የታቀደው ይህ ፕሮጀክት ከኤሌክትሪክ አቅርቦት ባሻገር ለአካባቢው ወጣቶች ቋሚና ጊዚያዊ የስራ ዕድል ይፈጥራል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 19 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

ፕሮጀክቱን ለማስጀመር የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው ……….///……… የሀረር ቁጥር 4 ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክትን ለማስጀመር የሚያስችሉ የዝግጅት ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን የምስራቅ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ግሪድ ማጠናከሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ የሳይት ተወካይ አቶ መኮንን ዓለሙ እንዳስታወቁት ፕሮጀክቱ በሚያርፍበት ቦታ ይዞታ ላላቸው አርሶ አደሮች ተገቢውን ካሳ ለመክፈል የእርሻ መሬት ልኬትና የተክል ቆጠራ ቀደም ብሎ ተከናውኗል፡፡ ይዞታቸው ለፕሮጀክቱ የሚፈለግ 40 የአካባቢው ነዋሪዎች በልኬቱና በቆጠራው መሠረት አስፈላጊውን ካሳ ከፍሎ ለግንባታ ዝግጁ ለማድረግ ከሚመለከታቸው የክልል፣ የወረዳና የአካባቢው መስተዳደሮች ጋር ሰፊ ውይይቶች መደረጋቸውን ተወካዩ አንስተዋል፡፡ ተቋሙ የቀረበለትን የካሳ ክፍያ መጠን አዋጁን መሠረት አድርጎ ለመክፈል ከተቋሙ የተውጣጡ የህግና የአካባቢ ጥናት ባለሞያዎች በስፍራው በመገኘት ክትትል ማድርጋቸውን ገልፀዋል፡፡ እንደ ተወካዩ ገለጻ ክልሉና ወረዳው ያዋቀሯቸው ኮሚቴዎች የካሳ ክፍያ ግምቱን አጠናቀው ለተቋሙ በአስቸኳይ እንዲያቀርቡ እና ወደ ሥራ እንዲገባ ከክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቱ በሚያርፍበት ቦታ ላይ ከፕላን ጋር ተያይዘው የተነሱ ጥያቄዎች መኖራቸውን ያነሱት ሥራ አስኪያጁ ጉዳዩ በክልሉ ምክር ቤት ታይቶ ውሳኔ እንዲሰጥ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ በሀረሪ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ የከተማ ማደስና መልሶ ማልማት ቡድን መሪ አቶ ፈቲ ሁሴን በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በከተማዋና በዙሪያው ለሚገነቡ ኢንዱስትሪዎች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ፕሮጀክቱ ከመጀመሩ በፊት ለአርሶ አደሮቹ ተገቢውን ካሳ ለመክፈል ከክልሉና ከወረዳ መስተዳድር የተውጣጡ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ኮሚቴዎች ሲከታተሉ መቆየታቸውን አቶ ፈቲ አስታውሰዋል፡፡ የካሳ ክፍያ መመሪያው በሚያዘው መሠረት በየሁለት ዓመቱ የሚሻሻል መመሪያ መኖሩን የጠቆሙት አቶ ፈቲ በዚህ ምክንያት ግምቱ እንደዘገየ አስረድተዋል፡፡ አሁን ግን የካሳ ክፍያውን የመጨረሻ ግምት አፅድቆ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ለአርሶ አደሮቹ ክፍያ የሚፈፀምበት የባንክ ደብተር፣ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ እና ተያያዥ ጉዳዮችን እየተጠናቀቁ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ የሀረር ቁጥር 4 ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ከሀረር ከተማ በ15 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ቃሊ ቀበሌ ሊገነባ የታሰበ ፕሮጀክት ነው፡፡ ፕሮጀክቱ በአፍሪካ ልማት ባንክ ፋይናንስ የሚገነባ ሲሆን የምስራቅ ኢትዮጵያን የኤሌክትሪክ ግሪድ ለማጠናከር ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 18 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

photo content

ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ተቋማችን በአዲስ ዘመን ጋዜጣ መጋቢት 11 ቀን 2016 ዓ.ም በተለያዩ የስራ መደቦች ባለው ክፍት ቦታ በቋሚነት አመልካቾችን ለመቅጠር ማስታወቂያ አውጥቷል፡፡ በመሆኑም መስፈትሩን የምታሟሉ አመልካቾች ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ ተጠቅማችሁ እንድትመዘገቡ ተጋብዛችኋል፡፡ መልካም ዕድል! https://docs.google.com/forms/d/1bgjGG7oebOHtdsQA9g34_WTjVmN7KhUQzYGEOGAV1yA/edit https://forms.gle/d5wiSik2DY1eJP5X6 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም

ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው ሁለተኛ ሆና አጠናቀቀች ........///....... በጋና አክራ በተካሄደው የመላው አፍሪካ አትሌቲክስ ውድድር ኢትዮጵያ ሁለተኛ ሆና አጠናቃለች። በውድድሩ ኢትዮጵያ ካገኘቻቸው 18 ሜዳሊያዎች መካከል የኢትዮ ኤሌክትሪክ አትሌቶች አምስት ሜዳሊያዎችን ለሀገራቸው አስገኝተዋል። በሻምፒዮናው ከተሳተፉት አስራ አራት የኢትዮ-ኤሌክትሪክ አትሌቶች መካከል ሶስቱ ወርቅ ሲያገኙ ሁለቱ የብር ሜዳሊያ አግኝተዋል። ሀጎስ ገ/ህይወት በ5 ሺህ ሜትር፣ ሳሙኤል ፍሬው በ3 ሺህ መሠናክል እንዲሁም ሂሩት መሸሻ በአንድ ሺህ 500 ሜትር ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳልያ ያስገኙ የኢትዮ - ኤሌክትሪክ አትሌቶች ናቸው። በተጨማሪም ብርቱካን ሞላ በሴቶች 5 ሺህ ሜትር እንዲሁም ገመቹ ዲዳ በወንዶች 10 ሺህ ሜትር የብር ሜዳሊያ ለሀገራቸው አስገኝተዋል። በዚህ አህጉራዊ ውድድር ኢትዮጵያ ሰባት ወርቅ፣ ሰባት ብር እና አራት ነሐስ በድምሩ አስራ ስምንት ሜዳሊያ በመሠብሰብ ናይጄሪያን  ተከትላ ከአፍሪካ ሁለተኛ ሆና አጠናቃለች። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 14 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በሀዋሳ ድል አስመዝግቧል ........///........ በ15ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ውድድር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን ጅማ አባጅፋርን በመርታት ሶስት ነጥብ አግኝቷል። በሐዋሳ ስቴዲየም በተከናወነው ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ አቤል ሀብታሙ እና ቢኒያም ካሳሁን ባስቆጠሯቸው ጎሎች ሁለት ለአንድ ማሽነፍ ችሏል። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከተከታዩ ንብ እግር ኳስ ክለብ በ10 ነጥብ ርቆ ሊጉን በ36 ነጥብ በመምራት ላይ ይገኛል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ኳስ መስርቶ በመጫወት እና ቶሎ ቶሎ ተቃራኒ የግብ ክልል በመድረስ በእጅጉ የተሻለ ሲሆን በአንፃሩ ጅማ አባጅፋር በመከላከልና አልፎ አልፎ በመልሶ ማጥቃት ለመጫወት ተገዶ ነበር። በዕለቱ ጨዋታ ግሩም እንቅስቃሴ ሲያደርግ የነበረው አቤል ሀብታሙ ኮከብ ተጫዋች በመሆን የማሊያ ሽልማት ተበርክቶለታል። በ16ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ መርሐግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመጪው ሀሙስ መጋቢት 19 ቀን 2016 ዓ.ም ከወልዲያ ከነማ ጋር ጨዋታውን የሚያከናውን ይሆናል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 14 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

ወጥና በቴክኒኖሎጂ የታገዘ አሰራር በመዘርጋት የኤሌክትሪክ መቆራረጥን ለማስቀረት እየተሰራ ነው ……//…… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ወጥና በቴክኖሎጅ የታገዙ አሰራሮችን በመዘርጋት የኃይል መቆራረጥን ለማስቀረት እየሰራ መሆኑን በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፊያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የቴክኒካል ድጋፍ መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ አበባው ያለው እንደገለጹት በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚሰሩ የፍተሻና የጥገና ሥራዎችን በሁሉም ሪጅኖች ወጥነት ባለው መልኩ ማከናወን የሚያስችል አሰራር ተተግብሯል፡፡ የተበላሹ ዕቃዎችን፣ ማሻሻያ የሚፈልጉ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በማጥናትና በመጠገን ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፊያ ጣቢያዎች ያለብልሽት በሙሉ አቅማቸው እንዲሰሩ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እና የስርጭት መስመሮች ሲቆረጡ የተቆራረጡ መስመሮችን እና ያደረሱትን ጉዳት እንዲሁም ያልተሸጠ ኃይል የሚመዘግብ ኢኢፒ ሳውዝ ክላውድ የሚባል ሶፍትዌር በክፍሉ ሠራተኞች በልፅጎ ሥራ ላይ መዋሉንም ተናግረዋል፡፡ አር ቲ ኢ ኢንተርናሽናል ከሚባል የፈረንሳይ የትራንስሚሽን ካምፓኒ ጋር “ግሪድ ሞደርናይዜሽን” የሚባል ፕሮጀክት ተቀርጾ እየተሰራ ነው ያሉት አቶ አበባው ካምፓኒው እንዴት እየሰራ ነው የሚለውም ፈረንሳይ ድረስ በመሄድ የልምድ ልውውጥ ተደርጓል። ካምፓኒው ፕላንት ሜንቴናንስ ለሚባለው የሳፕ ሞጁል የሚባል እስከ ሴሪያል ቁጥር ድረስ የወረደ የድርጅቱን ንብረት የሚመዘግብ አሰራር ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን የተናገሩት ኃላፊው ለዚህም ዳታ የማሰባሰብና የማደራጀት ሥራ ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው። በተመሳሳይ ከኬኒያው አሞቴክ አፍሪካ ኩባንያ ጋር የትራንስፎርመርና ሌሎች ፍተሻዎችን ለማካሄድ ለመሃንዲሶች ስልጠና በመስጠት በጋራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ይህም የቴክኖሎጂና የዕውቀት ሽግግር እንዲኖር እድል በመስጠትና ሥራዎችን በማዘምን በኩል ሚናው የጎላ ነው ብለዋል። መምሪያው ዳታ ቤዝ በማዘጋጀት በካምፓኒው ውስጥ ያሉ ዕቃዎችን እየመዘገበ እንደሚገኝ አስታውሰዋል። አቶ አበባው እንዳሉት ሪጅኖች ያሉባቸውን የመለዋወጫ እጥረት በማጥናት ዋናው ፓወር ትራንስፎርመር አደጋ እንዳይደርስበት የሚከላከሉ 40 እርዚንግ ትራንስፎርመር እና 46 ሺ ሜትር የፓወር ኬብል ገመድ ግዥ ለመፈጸም ፕሮሰስ ተጀምሯል።                                                                                በዘርፉ ሥር የሚከናወኑ ሁሉንም ተግባራት የጥራት አስተዳደር ሥርዓት (QMS)ን የተከተለና የተቋሙን የ-ISO 9001 ዓለም ዓቀፍ ስታንዳርድ መርሆዎች የተከተለ እንዲሆን ሥርዓቶችን፣ ፕሮሲጀሮችን፣ ፖሊሲዎችን፣ ማኑዋሎችንም እያዘጋጀ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ ላሉት ለ13ቱ ሪጅኖች የሚሆኑ የሥራ ላይ ደህንነት ጨምሮ 7 ፕሮሲጀሮችንም አስጸድቆ ወደ ተግባር መግባቱን ገልጸዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 13 ቀን 2016 ዓ.ም