ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 560 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 357 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 160 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 560 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 25 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 32، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -5، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 26.03‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.88‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 052 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 472 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 8.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 26 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 560
المشتركون
-524 ساعات
+167 أيام
+3230 أيام
أرشيف المشاركات
የተቋረጠውን መስመር ማገናኘት ተችሏል ……….///…….. በስርቆት ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የበደሌ - መቱ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ኃይል መስጠት ጀምሯል፡፡ ከትና
የተቋረጠውን መስመር ማገናኘት ተችሏል ……….///…….. በስርቆት ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የበደሌ - መቱ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ኃይል መስጠት ጀምሯል፡፡ ከትናንት ከሰዓት በኋላ አንስቶ በኢሉ አባቦር ዞን ፣ በሸካ ዞን፣ በቄለም ወለጋ ዞን እና በጋምቤላ ክልል ተቋርጦ ያደረው የኤሌክትሪክ ኃይል ተመልሷል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 16 ቀን 2017 ዓ.ም

የኢትዮ-ኤሌክትሪክ እንስቶች በአቋም መለኪያ ጨዋታ አሸንፈዋል ........///........ የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን በአቋም መለኪያ ጨዋታ ቦሌ ክፍለ ከተማን ሁለት ለባዶ አሸንፏል። ጎፋ በሚገኘው የኤሌክትሪክ ሜዳ በተከናወነው የአቋም መለኪያ ጨዋታ ሁለቱንም የማሸነፊያ ጎሎች ሳባ ኃ/ሚካኤል ከመረብ አሳርፋለች። ኢትዮ ኤሌክትሪኮች ኳስ ይዞ በመጫዎት እና ቶሎ ቶሎ ወደ ተቃራኒ ጎል በመድረስ ተጋጣሚያቸው ላይ ተፅእኖ ማሳረፍ ችለዋል። በአንፃሩ ቦሌዎች መከላከል ላይ የተመሠረተ አጨዋወት የተከተሉ ሲሆን አልፎ አልፎ በመልሶ ማጥቃት ጎል ለማግኘት ሙከራ አድርገዋል። የ2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ጥቅምት 24 የሚጀመር ሲሆን ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የመጀመሪያ ጨዋታውን ከቂርቆስ ክፍለ ከተማ ጋር የሚያካሂድ ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 16 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

በስርቆት ምክንያት ኃይል ተቁርጣል ……….///…….. በበደሌ - መቱ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ በተፈፀመ ስርቆት ኃይል ተቋርጧል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ምዕራብ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንደገለፁት በስርቆት ምክንያት ታወሩ የወደቀው ከበደሌ ከተማ በ 69 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ነው፡፡ በዚህ የተነሳ በኢሉ አባቦር ዞን ፣ በሸካ ዞን፣ በቄለም ወለጋ ዞን እና በጋምቤላ ክልል የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጡን አስታውቀዋል፡፡ በስርቆት ምክንያት የወደቀው የብረት ምሰሶ መልሶ ለመተካት እንቅስቃሴ መጀመሩን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ ችግሩ አስኪስተካከል ድረስ ደንበኞች በትግስት እንዲጠባበቁ ጠይቀዋል፡፡ የኃይል መሰረተ ልማቶች ስርቆት በተለያዩ አካባቢዎች ለኃይል መቋረጥ ምክንያት እየሆነ በመምጣቱ ህብረተሰቡና የሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት ድርጊቱን ለማስቆም እንዲረባረቡ አቶ ጌታሁን አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 15 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ማመንጫ ጣቢያው ከዕቅድ በላይ ኃይል አምርቷል፤ ........//......... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግልገል ጊቤ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2017 የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከዕቅድ በላይ ኃይል ማምረቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ሹመት በላቸው እንደገለጹት ጣቢያው በሩብ ዓመቱ 565 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማመንጨት አቅዶ 631 ነጥብ 53 ጌጋ ዋት ሰዓት በማምረት የዕቅዱን 111 ነጥብ 68 በመቶ ማሳካት ችሏል። ጣቢያው በየወሩ በአማካይ እስከ 360 ነጥብ 59 ሜጋ ዋት ኃይል ሲያመርት እንደነበረም ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል። የጣቢያው አራቱም ተርባይኖች ውሃን ለመቆጣጠር የሚያገለግለው ሹል ጫፍ ያለው የብረት አካል ወይም ኖዝል በመበላቱ ምክንያት የአንድ ተርባይን የማመንጨት አቅም ከ105 ሜጋ ዋት ወደ 25 ሜጋ ዋት ድረስ ቀንሶ እንደነበር አቶ ሹመት አስታውሰዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ጉዳት የደረሰባቸውን የኖዝል አካላት በራስ አቅም በመጠገን አራቱም ዩኒቶች ወደ ሥራ መግባታቸው ለአፈጻጸሙ ከፍ ማለት በምክንያትነት ጠቅሰዋል። ከኖዝል በተጨማሪ የጣቢያውን ኃይል የማምረት አቅም አስተማማኝነት የሚያረጋግጡ የጥገና ሥራዎች ቀድመው መሰራታቸውም ለአፈጻጸሙ ከፍ ማለት ሚናቸው የጎላ መሆኑንም ጠቁመዋል። ጣቢያው በበጀት ዓመቱ 1 ሺ 859 ነጥብ 13 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማምረት አቅድ እየሰራ ነው ያሉት አቶ ሹመት በመጀመሪያው ሩብ ዓመት የተመዘገበውን የተሻለ ውጤት አስጠብቆ በመቀጠል ዓመታዊ ዕቅዱን ለማሳካት የቅድመ መከላከል፤ የትንበያ እና የሁኔታ አመላካች ጥገና ሥራዎች በዕቅድ ተይዘው እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። በ2002 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረው የጊቤ 2 የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በአራት ተርባይኖች 420 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም አለው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 15 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአድምኒስትሬሽን ኦፊሰር 1ኛ እና ፋይናንስ ኦፊሰር 1ኛ የስራ መደብ ለመቀጠር ታህሳስ 12 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የውጭ ማስታወቂ
+7
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአድምኒስትሬሽን ኦፊሰር 1ኛ እና ፋይናንስ ኦፊሰር 1ኛ የስራ መደብ ለመቀጠር ታህሳስ 12 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የውጭ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል ፡፡ ስለሆነም ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 6፡30 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ ማሳሰቢያ፡-በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ለፈተና ከተጠራችሁበት ሰዓት ቀድማችሁ እንድትገኙ በጥብቅ አሳስቧል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 14 ቀን 2017 ዓ.ም

የታወር ስርቆትን ለመከላከል መገናኛ ብዙኃን ህብረተሰቡን በማንቃት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ ……...//……... የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈጸሙ ስርቆቶችን በዘላቂነት ለመከላከል የመገናኛ ብዙኃን ህብረተሰቡን በማንቃት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጥሪ አቀረበ፡፡ የተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደገለጹት ተቋሙ የኃይል መሰረተ ልማቶችን በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ለማስፋፋት በሚያከናውነው ሥራ ላይ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ስርቆት ዋነኛ ፈተና ሆኖበታል፡፡ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት በየደረጃው ከሚገኙ የክልል የመስተዳድርና የጸጥታ አካላት እንዲሁም ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር የውይይትና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን በመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ ሞገስ ገለፃ ችግሩ በሚጎላባቸው አካባቢዎች ከሚካሄዱት የምክክር መድረኮች በተጨማሪ ተቋሙ በአማርኛና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንዲሁም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ እና በሌሎችም የኮሙዩኒኬሽን አማራጮች ግንዛቤ ለመፍጠር እየሰራ ነው ብለዋል፡፡ ይሁንና ከችግሩ ስፋት አንጻር እስከ አሁን በተቋሙ በተከናወኑ ሥራዎች የሚፈለገውን ውጤት ማምጣት አለመቻሉን ነው ዳይሬክተሩ የተናገሩት፡፡ ስለሆነም መገናኛ ብዙኃን በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ በሚፈጸሙ ስርቆቶች እየደረሰ ያለውን ዘርፈ ብዙ ጉዳት የሚያሳዩ፣ የእኔነት ስሜትን የሚያሳድጉ እና የኃይል መሰረተ ልማቶችን ለመጠበቅ በወጡ ህጎችና አተገባበራቸው ላይ ለኅብረተሰቡ ግንዛቤ የሚፈጥሩ ዜናዎችንና ፕሮግራሞችን በዕቅድ ይዘው ሊሰሩ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ስርቆቱ በኅብረተሰቡ ላይ እያሳደረ ያለውን ተፅዕኖ ለመቀነስና ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ተቋሙ ከመገናኛ ብዙኃን ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ሞገስ በኃይል መሠረተ ልማቱ ላይ የሚፈፀሙ ስርቆቶችን ለመከላከል ሚዲያዎች የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎች ላይ ትኩረት ሠጥተው እንዲሰሩም ጥሪ አቅርበዋል። ተቋሙ በ2016 በጀት ዓመት ብቻ በስርቆት ምክንያት ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት ሲደርስበት የደረሰውን ጉዳት ለመጠገን ደግሞ 200 ሚሊዮን ብር ለማውጣት መገደዱን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

ሪጅኑ ለዳታ ማይኒንግ ማዕከላት ኃይል እያቀረበ ነው ……....///……….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የደቡብ አንድ ሪጅን የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ለሦስት የዳታ ማይኒንግ ኩባንያዎች ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ የመምሪያው ዳይሬክተር አስታወቁ። ዳይሬክተሩ አቶ ምትኩ ንጉሴ እንደገለፁት ሪጅኑ በአሁኑ ወቅት ሁዋን ዩ፣ አሲክ እና ፊንጋቺ ለተባሉ ሦስት የዳታ የምናባዊ ግብይት ማቀላጠፊያ ማዕከላት ከ145 በላይ ሜጋ ዋት ኃይል እያቀረበ ይገኛል። ሁለቱ ኩባንያዎች ከሀዋሳ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ 105 ሜጋ ዋት እንዲሁም አንዱ ኩባንያ ደግሞ ከይርጋለም ቁጥር ማከፋፈያ ጣቢያ 40 ሜጋ ዋት ኃይል እያገኙ መሆኑን ነው የጠቀሱት። የዳታ ማይኒንግ ማዕከላቱ የጀመሯቸውን ሥራዎች ሙሉ በሙሉ ሲያጠናቀቁ ከ270 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል የመጠቀም ፍላጎት እንዳላቸው ነው ዳይሬክተሩ የገለፁት። በሪጅኑ የሚገኙ አስራ ሁለቱ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች 1 ሺህ 910 ሜጋ ዋት ኃይል የመጫን አቅም ያላቸው መሆኑን ተናግረው በአሁኑ ሰዓት 1 ሺህ 710 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል እያቀረቡ እንደሚገኙ ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባሳለፍነው በጀት ዓመት ለዳታ ማይኒንግ ማዕከላት ካቀረበው ኃይል ከ25 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቱን መዘገባችን አይዘነጋም። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 13 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

ኢትዮ - ኤሌክትሪክ በሊጉ የመጀመሪያውን ድል አስመዘገበ ……….////……… በድሬዳዋ ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው 4ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ባህር ዳር ከተማን 1 ለባዶ በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ ኢትዮ - ኤሌክትሪክ በ16ኛው ደቂቃ ላይ አቤል ሀብታሙ ባስቆጠራት ጎል የመጀመሪያውን አጋማሽ መምራት ችሏል፡፡ ለማሸነፍ ከፍተኛ ግምት የተሰጠው ባህርዳር ከተማ ቢሆንም ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ያገኘውን ዕድል ወደግብ በመቀየር 3 ነጥብ ይዞ ወጥቷል፡፡ ኢትዮ - ኤሌክትሪክ በውድድር ዘመኑ 4 ጨዋታዎችን አድርጎ በሁለቱ አቻ ሲወጣ፣ በአንዱ ተሸንፎ የዛሬውን ጨዋታ አሸንፏል፡፡ ሁለቱ ክለቦች ከዚህ በፊት በተገናኙባቸው ሁለት ጨዋታዎች ባህርዳር ከተማ ማሸነፉ አይዘነጋም፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

photo content

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቁጥር ኢ.ኤ.ኃ/8.4/23/16 ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም. በሾፌር - 3ኛ እና በሾፌር-4ኛ የሥራ መደብ ለውጭ አመልካቾች ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም. በሾፌር - 3ኛ እና ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. በሾፌር - 4ኛ የሥራ መደቦች ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ መንጃ ፈቃድ በመያዝ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው የተቋሙ ዋና መ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና ስለሚሰጥ በፈተናው ቦታ ላይ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ ማሳሰቢያ፦ በፈተና ሰዓት የእጅ ስልክ (ሞባይል) ይዞ መግባት ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ዛሬ ወሳኝ ጨዋታውን ያደርጋል ……….////……… በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 4ኛ ሳምንት ጨዋታ ዛሬ 10፡00 ሰዓት ላይ ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ከባህር ዳር ከተማ ጋር ይጫወታል፡፡ ባህር ዳር ከተማ በስድስት ነጥብ በሊጉ በአራተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ሲሆን ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ደግሞ በሁለት ነጥብ በሊጉ 16 ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡ ኢትዮ - ኤሌክትሪክ በውድድር ዘመኑ 3 ጨዋታዎችን አድርጎ በሁለቱ ሲሸንፍ በአንዱ አቻ ወጥቷል፤ የዛሬ ተጋጣሚው ባህር ዳር ከተማም በተመሳሳይ 3 ጨዋታዎችን አድርጎ በሁለቱ ሲያሸንፍ በአንዱ ተሸንፏል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ተቋሙ ከ1 ሺህ 3 መቶ ለሚበልጡ ሠራተኞች የህክምና አገልግሎት ሰጥቷል ……….///……….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መካከለኛ ክሊኒክ በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሦስት ወራት ከ1 ሺህ 3 መቶ ለሚልቁ የተቋሙ ሠራተኞች የህክምና አገልግሎት መስጠቱን የጤና አገልግሎት ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ተወካይ ሥራ አስኪያጅ አቶ አድማሱ ተኽልቁ እንደገለጹት የተቋሙን ሠራተኞች ጤንነት ለመጠበቅ ቢሮው ከበሽታ መከላከልና ህክምና አገልግሎት ጋር የተያያዙ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው ሩብ ዓመት 23 የድንገተኛ ህክምና አገልግሎትን ጨምሮ 600 ሴት እና 727 ወንድ ሠራተኞች በተቋሙ መካከለኛ ክሊኒክ የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡ ተወካይ ሥራ አስኪያጁ አክለውም ከክሊኒኩ አቅም በላይ የሆኑ ህክምናዎች ሲያጋጥሙ ሠራተኞቹ የተሻለ ህክምና እንዲያገኙ ለማድረግ ተቋሙ 20 ከሚሆኑ የጤና ተቋማት ጋር ስምምነት ማድረጉን ገልፀዋል፡፡ በዚህም ባለፉት ሦስት ወራት ስምምነት በተፈፀመባቸው የጤና ተቋማት ላይ 1 ሺ 586 ሠራተኞች የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ መደረጉን አስረድተዋል፡፡ የታካሚዎች አሃዝ በድግግሞሽ የህክምና አገልግሎት ያገኙ ሠራተኞችን ቁጥር ታሳቢ ያደረገ እንደሆነ የጠቀሱት አቶ አድማሱ የተቋሙ ሠራተኞች በሩብ ዓመቱ ላገኙት የህክምና አገልግሎት የመድኃኒት ወጪን ጨምሮ ተቋሙ ከ7 ነጥብ 47 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማድረጉንም አስታውቀዋል፡፡ እንደ አቶ አድማሱ ገለፃ በዋናው መስሪያ ቤት ባለው መካከለኛ ክሊኒክ ከሚሰጡ የህክምና አገልግሎቶች በተጨማሪ በማመንጫ ጣቢያዎች ላይ ለሚገኙ 12 ክሊኒኮች የተለያዩ ድጋፎች ተደርገዋል፡፡ ክሊኒክ የሌላቸው የኃይል ማመንጫ ፕሮጀቶችና የጣቢያ ሠራተኞች በአካባቢያቸው የሚገኙ ሪጅኖቹ ውል በፈፀሙባቸው የጤና ተቋማት እና በሌሎች የማመንጫ ጣቢያ ክሊኒኮች የህክምና አገልክሎት እንዲያገኙ መደረጉንም ተናግረዋል፡፡ የየካ ክፍለ ከተማ የምግብ፣ መድኃኒትና ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን በ2016 በጀት ዓመት በስሩ በሚገኙ የግልና የመንግስት ጤና ተቋማት ላይ ባካሄደው ምዘና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መካከለኛ ክሊኒክ 97 ነጥብ 27 በመቶ በማስመዝገብ ቀዳሚ በመሆን እውቅና አግኝቷል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም