ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 533 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 338 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 162 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 533 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 29 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 6، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 25.10‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.85‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 901 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 619 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 8.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 30 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 533
المشتركون
-124 ساعات
-167 أيام
+630 أيام
أرشيف المشاركات
photo content
+5

በጣቢያው ስዊች ያርድ ላይ የተከናወነው የጥገና ሥራ ኃይል ተቋርጦ የሚቆይበትን ጊዜ አሳጥሯል ……..///…… በመልከ ዋከና የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ስዊች ያርድ ላይ በቅርቡ የተከናወነው የጥገና ሥራ የኦፕሬሽን ሥራውን እያቀላጠፈ እንደሆነ የጣቢያው ኃላፊ ገለፁ፡፡ ኃላፊው አቶ ቴዎድሮስ በቀለ እንደገለጹት ማመንጫ ጣቢያው ከተገነባ ረጅም ጊዜ በማስቆጠሩና የመልሶ ግንባታ ሥራ ያልተከናወነለት በመሆኑ በስዊች ያርድ መቀጣጠሪያዎች ላይ ችግሮች ያጋጥሙ ነበር፡፡ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ ተደጋጋሚ ችግሮች ሲከሰቱ መቆየታቸውን ያነሱት አቶ ቴዎድሮስ በሲዊች ያርዱ ውስጥ የሚገኙ ሃያ ሰባቱንም መቆጣጠሪያዎች ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጅ በመቀየር ችግሩን መፍታት ተችሏል ብለዋል፡፡ ከዚህ በፊት የነበረው መቆጣጠሪያው በአየር የሚሰራ (Air blast) እንደነበር እና በቅርቡ በሲዊች ያርዱ ላይ በተደረገው የጥገና ሥራ ብሬከሩን "SF 6 Gas circuit breaker" በሚባል የመቆጣጠሪያ ዓይነት መቀየሩን አስታውቀዋል፡፡ በአየር የሚሰራው ብሬከር በነበረበት ጊዜ፤ ኃይል በተለያዩ ምክንያቶች ሲቋረጥ ሲስተሙን መልሶ ለማገናኘት ከ2 ሰዓት እስከ አንድ ቀን ይወስድ እንደነበር የጣቢያው ኃላፊ አስታውሰዋል፡፡ እንደ አቶ ቴዎድሮስ ገለጻ ጣቢያው ከሲስተም ሲወጣ መልሶ ለማገናኘት ተርባይኖችና ሌሎች ማሽኖች ዝግጁ ቢሆኑም ብሬከሩ አየር እስኪሞላ ድረስ መጠበቅ ያስገድድ ነበር፡፡ ብሬከሩን አየር ለመሙላት እስከ ሦስት ሠዓት እንዲሁም በብሬከሩ ላይ የአየር ስርገት ሲያጋጥም የተቋረጠውን ሲስተም መልሶ ለማገናኘት ከግማሽ ቀን በላይ ይወስድ እንደነበርም ተናግረዋል፡፡ በተርባይኖቹ ምክንያት ብሬከሩ ሲከፍት የተቋረጠውን ኃይል መልሶ ለማገናኘት እስከ አንድ ቀን ስለሚወስድ የጥገና ሥራው አድካሚና ኃይል ተቋርጦ የሚቆይበትን ጊዜ ይራዘም እንደነበር ገልፀዋል፡፡ የተቀየረው መቆጣጠሪያ ኃይል ሲቋረጥ ከ5 እስከ 15 ባሉት ደቂቃዎች ውስጥ መልሶ ለማገናኘት እንደሚያስችል ገልጸው የመቆጣጠሪያው መቀየር ሲስተሙ በተለያዩ ምክንያቶች ሲቋረጥ መልሶ ለማገናኘት ይወስድ የነበረውን እና ኃይል ተቋርጦ የሚቆይበትን ጊዜ ማሳጠር እንዳስቻለ አስታውቀዋል፡፡ የጣቢያውን ስዊች ያርድ የጥገና ሥራ ሲያን ኤሌክትሪክ የተባለ የቻይና ኩባንያ ያከናወነው ሲሆን ለሥራው ከ714 ሺህ የአሜሪካን ዶላር በላይ እና 532 ሺህ ብር ወጪ ተደርጓል፡፡ የመልካ ዋከና የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ከ1980 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን እያንዳንዳቸው 38 ነጥብ 25 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው አራት ተርባይኖች አሉት፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 11 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሊጉን እየመራ ነው ........///......... በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ እየተሳተፈ የሚገኘው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን በስድስት ነጥብ እና አራት ንፁህ ጎል ምድቡን እየመራ ይገኛል። ትናንት በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም ከቀኑ 8 ሰዓት በተካሄደው ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ነቀምቴ ከተማን 3 ለ 0 በማሸነፍ በሊጉ አናት ላይ ተቀምጧል። በፈጣን የማጥቃት እንቅስቃሴ ጨዋታውን የጀመረው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በቢኒያም ካሳሁን አማካኝነት በ10ኛው ደቂቃ የመጀመሪያውን ጎል ማስቆጠር ችሏል። የመጀመሪያው አጋማሽ ሊጠናቀቅ ሁለት ደቂቃዎች ሲቀሩት ያሬድ የማነ በግሩም ሁኔታ ሁለተኛውን ጎል ለክለቡ ሲያስቆጥር የአጥቂ ስፍራ ተጫዋቹ እሱባለው ሶስተኛዋን ጎል አስቆጥሯል። ከሙሉ የጨዋታ ብልጫ ጋር ያሸነፈው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሶስተኛ የጨዋታ መርሀግብሩን በመጪው ማክሰኞ ከጅማ አባጅፋር ጋር ከቀኑ 10:00 ሰዓት በአበበ ቢቄላ ስቴዲየም የሚያከናውን ይሆናል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 08 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

በኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ እየተፈጸመ ያለው ስርቆት በፕሮጀክቶች የግንባታ አፈፃፀም ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ ነው .........///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል በሚገነባቸው የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ እየተፈጸመ ያለው ስርቆት በፕሮጀክቶች የግንባታ አፈፃፀም ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ መሆኑን በተቋሙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የፕሮጀክት አፈጻፀም ክትትል እና ቁጥጥር ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ አንቺነሽ መንግስቱ እንደተናገሩት ተቋሙ የግሪድ መሰረተ ልማቱን ለማሳደግ በርካታ የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችንና የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችን እየገነባ ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ በአንዳንድ ፕሮጀክቶች ላይ የሚፈጸመው ስርቆት በፕሮጀክቶቹ ግንባታ ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ ይገኛል ብለዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጇ ገለጻ የቡታጅራ - ወራቤ፣ ባህርዳር - ወልዲያ- ኮምቦልቻ፣ አዘዞ - ጭልጋ እንዲሁም ለአዋሽ- ወልዲያ-ሃራ ገበያ የባቡር መስመር ኃይል ለማቅረብ እየተገነቡ ያሉ ማስተላለፊያ መስመሮች ተደጋጋሚ ስርቆት እየተፈተመባቸው ካሉ ፕሮጀክቶች መካከል ተጠቃሶች ናቸው፡፡ የቡታጅራ -ወራቤ ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ ከተጀመረ ጀምሮ በተለያየ ጊዜ እና አካባቢ በተፈጸመ ስርቆት ከ555 በላይ የታወር አካላት እና 390 ሜትር የሚሆን ኮንዳክተር በአዲስ መተካቱን ወ/ሮ አንቺነሽ አንስተዋል፡፡ በሩብ ዓመቱ በአዘዞ - ጭልጋ ፕሮጀክት በተፈጸመ ስርቆት የወደቁ ሦስት የኃይል ተሸካሚ ምሶሶዎች እንደገና መገንባታቸውንና በባህር ዳር-ወልዲያ- ኮምቦልቻ ፕሮጀክት ላይ በተፈጸመ ስርቆት ደግሞ ሰባት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች መውደቃቸውን ተናግረዋል፡፡ ወ/ሮ አንቺነሽ እንዳሉት እየተፈጸመ ያለው ስርቆት የፕሮጀክቶቹን የግንባታ ሥራ በተያዘላቸው ጊዜ እንዳይጠናቀቅ ከማድረጉም በላይ ተቋሙን ለተጨማሪ ወጪ እየዳረገው ይገኛል፡፡ በአራቱ ፕሮጀክቶች ላይ በተፈጸመ ስርቆት ብቻ ተቋሙ 10 ነጥብ 6 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ተጨማሪ ወጪ ለማውጣት እንደተገደደ ሥራ አስኪያጇ አስታውቀዋል፡፡ በተያያዘ ዜና በአንዳንድ አካባቢዎች እየተስተዋሉ ያሉት የጸጥታ እና የወሰን ማስከበር ችግሮች በፕሮጀክቶች የግንባታ ሥራ ላይ ተፅዕኖ እያሳደሩ መሆናቸውን ወ/ሮ አንቺነሽ ገልፀዋል። ከብረት ምሰሶዎች አካላት ስርቆት እና ከወሰን ማስከበር ጋር የተያያዙ ችግሮችን ለመፍታት በየደረጃው ከሚገኙ የክልል የመስተዳደር አካላት ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች መደረጋቸውን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጇ ችግሮቹን በዘላቂነት በዘላቂነት ለመፍታት ከአስተዳደር አካላት ጋር በትብብር የመስራቱ ሁኔታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች 20 የሚሆኑ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች የግንባታ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 07 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

በሪጅኑ በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙት የስርቆት ወንጀሎች እየቀነሱ መጥተዋል ……..///……. በሰሜን ምስራቅ ሪጅን አንድ በሚገኙ የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ ሲፈጸሙ የነበሩ ስርቆቶች እየቀነሱ መምጣታቸውን የሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ እንዳስታወቁት ሪጅኑ በሚያስተዳድራቸው የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሶሶዎች ላይ ከዚህ በፊት ተደጋጋሚ ስርቆቶች ሲፈጸሙ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ስርቆት በተደጋጋሚ በሚፈፀምባቸው አካባቢዎች ሪጅኑ በየደረጃው ከሚገኙ የጸጥታና የአስተዳደር አካላት እንዲሁም ከማኅበረሰቡ ጋር በቅንጅት በመስራቱ የስርቆት ተግባራት እየቀነሱ መጥተዋል፡፡ አቶ በድሩ እንዳሉት ህብረተሰቡ የኃይል መሰረተ ልማቶችን በኃላፊነት እንዲጠብቅ ለማድረግ ሪጅኑ በየደረጃው ከሚገኙ የአስተዳደር እና የጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ለህብረተሰቡ የግንዛቤ ማስጨበጫ በመስጠቱ በአጣየ፣ ሰንበቴ፣ ሀይቅ እና ሸዋሮቢት ከተሞችና አካባቢያቸው የስርቆት ወንጀሉ እየቀነሰ መምጣቱን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ በእነዚህ አካባቢዎች ህብረተሰቡ በአካባቢው የሚገኙ የኃይል ተሸካሚ ምሶሶዎችን በባለቤትነት ስሜት በመጠበቁ በመሰረተ ልማቶች ላይ ሲፈጸሙ የነበሩ ስርቆቶች እየቀነሱ መሆናቸውንና ተሞክሮውን ወደሌሎች አካባቢዎች ለማስፋፋት እየተሰራ እንደሆነ አመልክተዋል፡፡ በአቀስታ፣ ሰኞ ገበያ፣ ኮምቦልቻ፣ ሚዳ እና ወረኢሉ አካባቢዎች ካለው የጸጥታ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ህብረተሰቡን ያሳተፈ ሥራ መስራት ባለመቻሉ አሁንም በአካባቢዎቹ ስርቆትን ማስቀረት እንዳልተቻለ ገልፀዋል፡፡ በአካባቢዎቹ ያለው የጸጥታ ሁኔታ ወደነበረበት ሲመለስ ከህብረተሰቡና በየደረጃው ከሚገኙ የአስተዳደር አካላት ጋር ተቀራርቦ ለመስራት መታቀዱም ጠቁመዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ ህብረተሰቡን በማሳተፍ እየተሰራ ካለው ሥራ በተጨማሪ ስርቆት በስፋት በሚስተዋልባቸው አካባቢዎች ተደጋጋሚ የፍተሻ ሥራ በማከናወን መሰረተ ልማቱን ከመውደቅ መታደግ ተችሏል፡፡ በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ እየደረሰ ያለውን ስርቆት ተቋሙ በሚያደርገው ክትትል ብቻ መከላከል ስለማይቻል ህብረተሰቡ ንብረቶቹን በባለቤትነት ስሜት እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ለሪጅኑ የጥገና ባለሙያዎች የደህንነት እና የተቋሙ አርማ ያለበት የደንብ ልብስ ተደራሽ በመደረጉ ህብረተሰቡ የተቋሙ ሠራተኞችን በቀላሉ ለመለየትና ስርቆትን ለመከላከል የተጀመረውን ሥራ እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሪጅኑ የተለያየ የኪሎ ቮልት መጠን ያላቸው 971 ነጥብ 23 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመሮችን እና ስምንት የማከፋፈያ ጣቢያዎችን እያስተዳደረ ይገኛል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 05 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

በሪጅኑ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ ድግግሞሽ ቀንሷል ………..////………. በሪጅኑ ሲያጋጥም የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ ድግግሞሽ መቀነሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ሪጅን 1 የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ገበየሁ በላይ እንደገለጹት ሪጅኑ በሚያስተዳድራቸው አካባቢዎች አዳዲስ የማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታና በቆዩ ጣቢያዎች ላይ ደግሞ የማስፋፊያና አቅም የማሳደግ ሥራዎች ተሠርተዋል። በመሆኑም በሪጅኑ ከሚገኙ 12 የማከፋፈያ ጣቢያዎች አብዛኞቹ ኃይል የመሸከም አቅማቸው አስተማማኝ በመሆኑ ቀደም ሲል ያጋጥም የነበረው የኃይል መቆራረጥ ድግግሞሽ በከፍተኛ ደረጃ መቀነሱን ተወካዩ ገልጸዋል። በሪጅኑ በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመከላከል የቅድመ ክትትልና ጥገና ሥራዎች መሰራታቸው እንዲሁም ድንገተኛና መደበኛ የጥገና ሥራዎች ሲኖሩ ከክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በመነጋገር በፍጥነት ማጠናቀቅ መቻሉ ኃይል ጠፍቶ የሚቆይበትን ጊዜ እንዲቀንስ አድርጎታል ብለዋል፡፡ በግንባታ፣ ጥገናና ኦፕሬሽን ዘርፍ የተቋሙ የሰው ኃይል አቅም እያደገ መምጣቱ የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳበረከተ የጠቆሙት ተወካዩ በሪጅኑ ለሚያጋጥሙ ችግሮች ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚችሉ ልምድ ያላቸው ባለሙያዎች መኖራቸውንም አክለዋል፡፡ ሪጅኑ በአሁኑ ወቅት አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይልን ለደንበኞቹ እያቀረበ ቢሆንም በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ላይ የሚያጋጥሙ ሥርቆቶች እየጨመሩ በመምጣታቸው ችግሩን ወደ ነበረበት ሊመልሰው ይችላል ሲሉ ተወካዩ ስጋታቸውን ገልጸዋል። እንደተወካዩ ገለጻ በከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ የሚፈፀም ስርቆት ዘርፉን ወደ ኋላ የሚጎትትና ተቋሙንም ለከፍተኛ ኪሳራ የሚዳርግ ከመሆኑም በላይ በህብረተሰቡ ኑሮ ላይ ትልቅ ጫና ያሳድራል፡፡ ይህ እንዳይሆን ህብረተሰቡ፣ መገናኛ ብዙኃን፣ የየአካባቢው መሥተዳደሮችና የጸጥታ አካላት ከተቋሙ ጋር በቅንጅት መሥራት እንዲሰሩ ተወካዩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 05 ቀን 2016 ዓ.ም

ኢትዮ - ኤሌክትሪክ የውድድር ዓመቱን የመጀመሪያ ድል አስመዘገበ ……..///……… በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ እየተሳተፈ የሚገኘው ኢትዮ - ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ክለብ የውድድር ዓመቱን በድል
ኢትዮ - ኤሌክትሪክ የውድድር ዓመቱን የመጀመሪያ ድል አስመዘገበ ……..///……… በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ እየተሳተፈ የሚገኘው ኢትዮ - ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ክለብ የውድድር ዓመቱን በድል ጀምሯል፡፡ ክለቡ በትናንትናው ዕለት በአበበ ቢቄላ ስቴዲየም ከቀኑ 10፡00 ሠዓት ከሀላባ ከተማ ጋር ባደረገው ግጥሚያ አንድ ለባዶ በማሸነፍ ሦስት ነጥብ ይዞ መውጣት ችሏል፡፡ በውድድር ዓመቱ ወደ ፕሪሚየር ሊግ ለመመለስ እየሰራ ላለው ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ብቸኛዋን የማሸነፊያ ጎል ከርቀት አክርሮ በመምታት ያስቆጠረው ሚኪያስ ካሳሁን ነው፡፡ በጨዋታው ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ኳስን መስርቶ በመጫወት ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል በተደጋጋሚ በመድረስ የተሻለ እንቅስቃሴ ማድረግ ችሏል፡፡ ሀላባ ከነማ በበኩሉ በመልሶ ማጥቃት ጎል ለማስቆጠር ጥረት ቢያደርግም ሳይሳካለት ቀርቷል፡፡ ኢትዮ - ኤሌክትሪክ በኢትዮጵያ የጥሎ ማለፍ ዋንጫ አዲስ አበባ ከተማን በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፉ የሚታወስ ሲሆን በመጪው አርብ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ውድድር ከቀኑ 8፡00 ሠዓት በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም ከነቀምቴ ከተማ ጋር ይጫወታል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 04 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

በገፈርሳ -ሙገር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ስርቆት ተፈጽሟል ……..///…….. ከገፈርሳ ሙገር በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተፈጸመ ስርቆት አንድ የመስመሩ ተሸካሚ ምሰሶ መውደቁን የማዕከላዊ ሪጂን አንድ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የማስተላለፊያ መስመርና ኦፕቲካል ፋይበር ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ በፍቃዱ በቀለ እንደተናገሩት ስርቆቱ ህዳር 1 ቀን 2016 ዓ.ም. የተፈፀመው መስመሩ በሚያልፍበት ወልመራ ወረዳ በከና ቆሮዶ በሚባል ቀበሌ ነው፡፡ በዚህ የተነሳ በዕለቱ ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ ከመስመሩ ኃይል ሲያገኙ የነበሩት የሐበሻ፣ ደርባ እና ሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካዎች እንዲሁም በሙገር ከተማና አካባቢው ኃይል ተቋርጦ እንደነበር አንስተዋል፡፡ ይሁን እንጂ ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች እና የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ከህዳር 2 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 7፡00 ጀምሮ በጊዜያዊነት ከሌላ መስመር በከፊል ኃይል እንዲያገኙ መደረጉን ነው ሥራ አስኪያጁ የተናገሩት፡፡ አቶ በፍቃዱ እንዳሉት በማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶው ላይ የደረሰው ጉዳት እስኪስተካከል ድረስ ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ዳንጎቴ ሲሚንቶ ፋብሪካ ኃይል ከሚያገኝበት መስመር ላይ ኤሌክትሪክ እያገኙ የሚቆዩ ይሆናል፡፡ የወደቀውን ምሶሶ ወደ ነበረበት ለመመለስ በአሁኑ ወቅት ለጥገና ሥራው የሚያስፈልጉ ዕቃዎችን ወደ ቦታ የማጓጓዝ ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ የጥገና ሥራው እንደተጠናቀቀም አካባቢዎች ቀድሞ ኃይል ሲያገኙበት ወደነበረው መስመር እንዲመለሱ ይደረጋል ብለዋል፡፡ የወደቀውን የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ ለመጠገን፤ የታወር ዋጋውን ጨምሮ እስከ 2 ሚሊዮን የሚጠጋ ብር ያስፈልጋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 04 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ተቋሙ ለሀገር ዕድገት አስተዋጽዖ ያላቸው ፕሮጀክቶች ግንባታ ላይ በትኩረት እየሠራ ነው …….....///……….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሀገር ዕድገት አስተዋጽዖ ያላቸው የኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይና የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ አስታወቁ። አቶ አንዱዓለም እንደገለፁት ተቋሙ የሦስት ዓመት ስትራቴጂ ዕቅድ ቀርፆ ለሀገር ዕድገት አስተዋጽኦ ያላቸው የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ ነው። በሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት ውስጥ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የ35 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ለማስጀመርና የተጀመሩትን ለማጠናቀቅ እንቅስቃሴ መጀመሩንም ተናግረዋል። የምስራቃዊ ግሪድ የኃይል አቅርቦትን ለማጠናከር በሁርሶ፣ ሐረር እና ፋፈን ላይ አዳዲስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ለመገንባት እና የአቅም ማሻሻያ ሥራዎችን ለማከናወን መታቀዱንም ነው የጠቆሙት። እንደ አቶ አንዱዓለም ገለፃ በደቡባዊ ግሪድ ላይም ከወላይታ ሶዶ - አርባምንጭ - ሽግዳን አዲስ የኃይል የማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታና የአቅም ማሳደግ ሥራዎች ይከናወናሉ። የኢትዮ- ጅቡቲ ሁለተኛ ሰርኪዩት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታም በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት ከሚከናወኑት መካከል እንደሚገኝ ነው የዋና ሥራ አስፈፃሚው ተወካይ የገለፁት። የባህርዳር- ወልዲያ- ኮምቦልቻ፣ ለግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም ለአዋሽ-ወልዲያ-ሐራ ገቢያ የባቡር መስመር ኃይል ለማቅረብ የተጀመሩ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ ተናግረዋል። ተቋሙ በአሁኑ ሰዓት የህብረተሰቡን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የጠቆሙት አቶ አንዱዓለም የተጀመሩት የኃይል መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች አማካይ አፈፃፀማቸው ከ75 በመቶ በላይ መድረሱን አመልክተዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 03 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

ተቋሙ በኤሌክትሮ ሜካኒካል ዘርፍ ያሰለጠናቸውን 40 ቴክኒሺያኖች አስመረቀ ...........///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለአራት ወራት ያህል በኤሌክትሮ ሜካኒካል የትምህርት ዘርፍ ያሰለጠናቸውን 40 ቴክኒሺያኖች ዛሬ አስመርቋል።    በምርቃት ሥነ- ስርዓቱ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደተናገሩት ተቋሙ ሀገራዊ የኃይል ፍላጎትን ከማሟላት ባሻገር አፍሪካን በኃይል መሠረተ ልማት ለማስተሳሰር እየሰራ ይገኛል። ተቋሙ የተጣለበትን ተልዕኮ ለመወጣት በክህሎትና በአመለካከት የዳበረ፣ ብቃት ያለውና ተወዳዳሪ የሰው ኃይል እንደሚያስፈልግ ያነሱት አቶ ሙላት ለዚህም የማሰልጠኛ ማዕከሉን በአሰራር፣ በግብዓት እና በአደረጃጀት ማዘመን ያስፈልጋል ብለዋል።   ተመራቂዎች በሚመደቡበት የሥራ ቦታ ዘርፉ የሚጠይቀውን የሙያ ሥነ- ምግባር በመላበስ፣ የደህንነት ህጎችን በማክበር እና ለሚያጋጥሟቸው ውስጣዊና ውጫዊ ችግሮች መፍትሄ አመንጪ በመሆን ተቋማዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።                    በተቋሙ የሰው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ እና የሠው ሀይል አስተዳደር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ተማም አፍደል በበኩላቸው ተቋሙ የነደፈውን የሦስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ለማሳካት የዛሬ ተመራቂዎችም የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል። በስልጠና ሂደቱ ላይ በርካታ ፈተናዎች አጋጥመው እንደነበር ያነሱት የተቋሙ የሰው ሀብት ልማት መምሪያ ዳይሬክተር ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር) ችግሮችን በመቋቋምና የመፍትሄ እርምጃ በመውሰድ ሠልጣኞችን ለውጤት ማብቃት መቻሉን አንስተዋል። በማሰልጠኛ ማዕከሉ በሚሰጡ የስልጠና ርዕሶች እና በመርሃ ግብሩ ላይ ክለሳ በማድረግ የስልጠና ሂደቱን ለማሻሻል መታቀዱንም አስታውቀዋል። በተቋሙ የስልጠናና ልማት ማዕከል ሥራ አስኪያጅ አቶ ደምስ ሰይፉ በበኩላቸው ተቋሙ እንደ አዲስ ከተቋቋመበት ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ ከ660 በላይ የሚሆኑ ሠልጣኞችን በዘርፍ በማሰልጠን በኦፕሬሽን የሥራ ዘርፎች ላይ እንዲሳተፉ መደረጉንና በተያዘው በጀት ዓመት በተሰጠው የስምንተኛ ዙር ስልጠና 17 ወንድ እና 23 ሴት ሠልጣኞችን መመረቃቸውን አንስተዋል። በማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የቴክኒካል ሰፖርት መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አበባው ያለው በበኩላቸው ተመራቂዎች ወደ ሥራ ሲሰማሩ ዘርፉ የሚጠይቀውን አሰራር ተከትለው ሥራዎችን ማከናወን እንደሚኖርባቸው አሳስበዋል። የተቋሙ መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር ጸሐፊ አቶ ኃይሉ ወልዴ በሥነ ስርዓቱ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ተመራቂዎች  ለሠራተኛው እና ለተቋሙ የጋራ ተጠቃሚነት ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።                  ከሠልጣኝ ተመራቂዎች መካከል ትዕግስት አምዴ እና ደሳለኝ ፈንታሁን እንደተናገሩት ከስልጠናው ወደፊት የሚሰጣቸውን ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ የሚያስችል እውቀትና ክህሎት እንዳገኙ ተናግረዋል። ተቋሙ በሚመድባቸው የሥራ ቦታዎች ሁሉ በመሠማራት የሚሰጣቸውን ኃላፊነት በትጋትና በብቃት ለመወጣት ዝግጁ  መሆናቸውንም አረጋግጠዋል።                    በዕለቱም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂዎች እና መምህራን የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 01 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

አስተዳደሩ የተቋሙን የሦስት ወራት አፈፃፀም ገመገመ ………///……… የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሦስት ወራት አፈፃፀም በፈተና ውስጥ ውጤት የተመዘገበበት ነው ሲል ገለፀ፡፡ ለአስተዳደሩ በቀረበው የበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የአፈፃፀም ሪፖርት እንደተገለፀው በሩብ ዓመቱ 5 ሺህ 526 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ለማምረት ታቅዶ 4 ሺህ 760 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የዕቅዱን 86 ነጥብ 1 በመቶ ኃይል ማምረት ተችሏል፡፡ ከተመረተው ኃይል ውስጥ ከውሃ የመነጨው 4 ሺህ 639 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም 97 ነጥብ 5 በመቶ፣ ከንፋስ 106 ነጥብ 3 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም 2 ነጥብ 2 በመቶ እና ከተርማል 14 ነጥብ 3 ወይም 0 ነጥብ 3 በመቶ ድርሻ እንደነበራቸው ተነስቷል፡፡ የኃይል ሽያጭ ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ጭማሪ ቢታይበትም ከዕቅድ አንፃር ግን መጠነኛ ልዩነት መታየቱን ሪፖርቱ አመልክቶ ለጎረቤት ሀገራት 21 ነጥብ 4 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ሽያጭ መከናወኑ ተገልጿል። በራስ አቅም የሚሰሩ ፕሮጀክቶች በመልካም አፈፃፀም ላይ ስለመሆናቸው የተነሳ ሲሆን 7 ፕሮጀክቶች በአማካይ 83 በመቶ አፈፃፀም እንዳላቸው በሪፖርቱ ተጠቅሷል፡፡ ለመሠረተ ልማት ግንባታ የሚወጣውን ወጪ ለመመለስ የሚያስችል ታሪፍ እንደሌለ፣ እያደገ የሄደው የውጭ ምንዛሬ ለውጥ በተቋሙ የፋይናንስ አቋም ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ መሆኑ፣ የመሰረተ ልማት ስርቆት፣ የካሳ ክፍያና የጸጥታ ችግር የተቋሙ ዋንኛ የስጋት ምንጮች መሆናቸውና ስጋቱን ለመቀነስ የሚያስችል ሥራ እየተሰራ መሆኑም በሪፖርቱ ተመላክቷል፡፡ ተቋሙ የቀጣዮቹን ሶስት ዓመታት ስትራቴጂክ ዕቅድ ማዘጋጀቱ፣ ከቢሮ ኪራይ ወጥቶ በራሱ ህንፃ ውስጥ መግባቱ፣ ዕዳና ወጪን ተመጣጣኝ ለማድረግ እየሰራ መሆኑ፣ የብሔራዊ የኃይል ቋት ማዕከል ግንባታ መጀመሩ፣ የተተኪ አመራሮች ዕቅድ መኖሩ፣ የግብ ቋት ለመፍጠር ከተቋም እስከ ግለሰብ ፈፃሚ ድረስ እየተሰራ መሆኑ በሪፖርቱ ተነስቷል፡፡ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር በበኩሉ በዋና ዋና መመዘኛዎች ተቋሙ ያለበትን ደረጃ የተመለከተ ዝርዝር ሪፖርት አቅርቧል፡፡ የአስተዳደሩ የግምገማ ሪፖርት የኢነርጂ ምርት በ11 በመቶ ማደጉንና የሩብ ዓመቱ አፈፃፀም 86 በመቶ መሆኑ፤ የኃይል ሽያጩ የዕቅዱን 81 በመቶ ቢከናወንም የውጭ ኃይል ሽያጭ ማነሱን፣ ተቋማዊ ስጋቶች ተለይተው የድርጊት መርሃግብር መዘጋጀቱን በዝርዝር ተመልክቷል፡፡ የተጠቃሚን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ኃይል ማምረት መቻሉ፣ ለአሰላ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የተገዛው ዕቃ ወደሀገር ውስጥ እየገባ መሆኑ፤ አሰራርን ለማዘመን የተዘረጋው ሳፕ የተባለው መተግበሪያ በመርሀ ግብሩ መሰረት መከናወኑ፣ በራስ አቅም ፕሮጀክቶች መገንባታቸው፣ የሶስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ መዘጋጀቱ በጥንካሬ ተነስቷል፡፡ የውጭ ሀገር ሽያጭ መቀነሱ፣ የገቢ አሰባሰብ ከዕቅዱ አንፃር ሲታይ ማነሱ፣ ፕሮጀክቶች በጊዜና በወጪ ልዩነት የታየባቸው መሆኑ፣ የሩብ ዓመቱ ፋይናንስ መግለጫ አለመዘጋጀቱ፣ በተያዘው ዕቅድ መሰረት የብድር ክፍያ አለመፈፀሙ በክፍተትነት ተነስቷል፡፡ በሪፖርቱ ላይ ጥያቄዎች ቀርበው በሚመለከታቸው ኃላፊዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ በግምገማው ማጠቃለያ ላይ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ኃ/ሚካኤል እንደተናገሩት ተቋሙ ስጋቶቹን በመለየት መፍትሔ ለመስጠት የጀመረው ሥራ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል፡፡ ገቢውን እና የውስጥ አቅሙን ለማጠናከር ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ ያሳሰቡት ዋና ዳይሬክተሩ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡ እንደ አቶ ሀብታሙ አስተያየት ተቋሙ በፈተና ውስጥም ሆኖ ውጤት ማስመዝገብ ችሏል፤ ለዚህም የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ሊመሰገን ይገባል ብለዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 01 ቀን 2016 ዓ.ም