ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 533 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 332 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 177 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 533 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 05 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 18، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -4، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 27.66‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.09‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 297 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 344 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 06 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 533
المشتركون
-424 ساعات
-77 أيام
+1830 أيام
أرشيف المشاركات
ምስል - በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የማህበራዊ ትስስር ገፅ
+1
ምስል - በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የማህበራዊ ትስስር ገፅ

የህዳሴ- ደዴሳ የማስተላለፊያ መስመርን ለአገልግሎት ዝግጁ የማድረግ ስራ እየተሰራ ነው ………..///………… በተጠናቀቀው የህዳሴ- ደዴሳ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተለያየ ምክንያት የተሰበሩትን ኢንሱሌተሮችን በአዲስ የመተካት ስራ ተጀመረል። የምዕራብ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ቢሮ ዳይሬክተር አቶ ቶማስ መለሰ እንደገለፁት ኢንሱሌተሮቹን የመተካት ሥራው የተጀመረው በቅርቡ የቅድመ ኃይል ማመንጨት ሥራ ለሚጀምረው የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መስመሩን ዝግጁ ለማድረግ ነው፡፡ ኢንሱሌተር የመቀየር ሥራው ከህዳሴ- ደዴሳ - ሆለታ ድረስ ከተዘረጋው መስመር መካከል እስከ ደደሳ ማከፋፈያ ጣቢያ ድረስ ባለው በሁለቱም የማስተላለፊያ መስመሮች ( ሎት1 እና ሎት2 ) በተተከሉ ምሶሶዎች ላይ የሚከናወን መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡ በመስመሩ ላይ በተካሄደለት የፍተሻ ስራ መሠረት በሁለቱም መስመሮች ላይ ከተተከሉት 1 ሺህ 535 ምሶሶዎች መካከል በ3 መቶ 12 ምሶሶዎች ላይ የሚገኙ ኢንሱሌተሮችን በሌላ የመቀየር ስራ እንደሚከናወን ኃላፊው ጠቁመዋል። በቀጣይ ከደደሳ ማከፋፈያ ጣቢያ እስከ ሆለታ ማከፋፈያ ጣቢያ በተዘረጋው ባለ 500 ኪሎ ቮልት ማስተላለፊያ መስመር ላይ የተሰበሩ ኢንሱሌተሮችን በተመሳሳይ የመቀየር ሥራ እንደሚከናወን ተጠቁማል። የደደሳ ማከፋፈያ ጣቢያ ስምንት ባለ 33 እና ሁለት ባለ 132 እንዲሁም አንድ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ያሉት ሲሆን ከዚህ ውስጥ በአሁኑ ሠዓት ሁለት ባለ 33 እና አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ለነቀምቴ ከተማ እና አካባቢው ኃይል በማቅረብ ላይ ይገኛል። የህዳሴ ደደሳ ሆለታ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ቻይና ኤሌክትሪክ ቴክኖሎጅ በተሰኘ ኩባንያ መገንባቱ ይታወሳል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 04 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content
+1

photo content

photo content

photo content

ግንባታውን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ………..///………… በኮምቦልቻ ከተማ እየተገነባ የሚገኘውን ባለ 400/230/33 ኪ ቮ. የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ቀሪ የሲቪል እና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራዎች ግንባታ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አስታወቀ፡፡ የጣቢያው ሳይት ተቆጣጣሪ መሃዲስ አቶ ኃይለየሱስ ስንታየሁ እንደተናገሩት እስከአሁን የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎችን የመገጣጠምና ወሳኝ የብረታ ብረት ስራዎች ተጠናቀዋል፡፡ የኤሌክትሮ መካኒካልና የብረታ ብረት ተከላና ለኤሌክትሪክ ገመዶች ቀበራ የሚውል ግንባታ ፣ እና ሁለት ባለ 150 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመር ተከላ ሥራዎች እና ሁለት ባለ 500 ሜጋ ቮልት አምፒር መትከያ የመሰረት ግንባታም ተከናውኗል፡፡ የመቆጣጠሪያ ቤት፣ የሰራተኞች መኖሪያ ቤት፣ የጥበቃ ቤት፣የስዊች ጊር ቤት እና የፍሳሽ ማስወገጃ ግንባታዎች የማጠናቀቂያ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ በቀጣይም የጠጠር ንጣፍ፣ የውስጥ አጥር፣ የስዊችያርድ ግንባታ እና የኬብል ዝርጋታ ሥራዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው እንደሚከናወኑ መሃንዲሱ ጠቁመዋል፡፡ እንደ አቶ ኃይለየሱስ ገለጻ ማከፋፈያ ጣቢያው 1000 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ሁለት ባለ 500 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመር እና 300 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለቸው ሁለት 150 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመር ይገጠሙለታል ፡፡ የፕሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ የትናየት ይመር እንደተናገሩት የማከፋፈያ ጣቢያውን ስራ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት 952 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር ተመድቦለታል፡፡ ግንባታውን ሻንጋይ ኤሌክትሮ ግሩፕ የተባለው የቻይና ኩባኒያ ሲያከናውን የአማካሪነት ስራውን ደግሞ የኢትዮጵያ ኤሌከትሪክ ኃይል እያከናወነው ይገኛል፡፡ ከአዲስ አበባ በ350 ኪ.ሜ. ርቀት ላይበአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በኮምቦልቻ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው የኮምቦልቻ ባለ 400 /230/33 ኪ.ቮ. የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ የተለያዩ የሲቪል እና የኤሌክትሮ መካኒካል ስራዎችን በማከናወን አማካይ አፈጻጸሙ ከ48 በመቶ በላይ ደርሷል፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅ ሃያ ባለ 33 ኪ.ቮ. ወጪ መስመር ያሉት ይህ ማከፋፈያ ጠቢያ የኮምቦልቻ ኢንዲሰትሪ ፓርክ፣ የኮምቦልቻ -ወልዲያ ባበር ፕሮጀክት እና የኮምቦልቻ ከተማ እና በአካባቢው የኃይል ፍላጎት አቅርቦት ጥያቄ ከመመሉሱ ባሻገር አስተማማኝ ተጨማሪ ኃይል እንዲኖር ያደርጋል ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 04 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content
+3

የቡኢ ባለ 132/33/15 የማከፋፈያ ጣቢያ ተመረቀ ……..////………. በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት በጉራጌ ዞን የተገነባው የቡኢ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ዛሬ በይፋ ተመረቀ፡፡ በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እርስቱ ርዳው፣ የፊደሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈጉባኤ ወ/ሮ እፀገነት መንግስቴ፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና ሌሎች የፌደራል፣ የክልሉና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። የክልሉ ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው ማከፋፈያው ለተጀመሩም ሆነ አዲስ ለሚጀመሩ ኢንቨስትመንቶች አስተማማኝ የኃይል ለማቅረብ ያስችላል ብለዋል፡፡ እንደዚህ ያሉ ፕሮጀክቶች የክልሉን ልማት የሚያፋጥኑ በመሆናቸው ክልሉ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ጀማል በበኩላቸው የማከፋፈያው መገንባት ቀደም ሲል በከተማዋ የተለያዩ የልማት ስራ ለመስራት እቅድ ያላቸውን የአካባቢው ተወላጆች እንደሚያበረታታ ተናግረዋል፡፡ የቡኢ ከተማ ከንቲባ አቶ ዘማች እንዳለ ደግሞ ከተማዋ ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ የምትገኝ ከተማ እንደመሆኗ የማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት አዳዲስ ባለሃብቶችን በመሳብ ረገድ የላቀ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው አለው ብለዋል፡፡ በምርቃት ስነሥርዓቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ የማከፋፈያ ጣቢያው ከአፍሪካ ልማት ባንክ በተገኘ 7 ነጥብ አንድ ሚሊየን ዶላር ብድርና ከመንግስት በተገኘ 39 ሚሊየን 320 ሺህ 425 ብር በጀት መገንባቱን ተናግረዋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው አራት ባለ 33 ኪሎ ቮልት እና አራት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ያሉት ሲሆን ቡኢ ከተማን ጨምሮ 22 ከተሞችንና የገጠር ቀበሌዎችን የኤሌክትሪክ ተደራሽ ያደርጋል። የማከፋፈያ ጣቢያውን ገንብቶ ለአገልግሎት ዝግጁ ያደረገው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኮንስትራክሽን የራስ አቅም(Own force ) ቢሮ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 03 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content
+1

የቡኢ ባለ 132/33/15 ኪ.ቮ. እና የነጆ ባለ 132/33 ኪ.ቮ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በቅርቡ በይፋ ተመርቀው ሥራ ይጀምራሉ ………///…………. በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት በጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ እና በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በምዕራብ ወለጋ ዞን ነጆ ከተማ የተገነቡት የማከፋፈያ ጣቢያዎች በይፋ ተመርቀው ሥራ ሊጀምሩ ነው፡፡ የቡኢ ባለ 132/33/15 ማከፋፋያ ጣቢያ አራት ባለ 15 ኪ.ቮ እና አራት ባለ 33 ኪ.ቮ ወጪ መስመሮች እንዲሁም 50 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው ትራንስፎርመር አለው፡፡ ለማከፋፈያ ጣቢያው ከቡታጅራ ነባር የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተነስቶ ቡኢ ማከፋፈያ ጣቢያ ድረስ 30 ኪ.ሜ የሚረዝምና 78 የኃይል ተሸካሚ ማማዎች የተተከሉለት ባለ 132 ኪ.ቮ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ ተከናውኗል፡፡ በተያያዘ ዜና እና በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በምዕራብ ወለጋ ዞን ነጆ ከተማ የተገነባው ባለ 132/33 የማከፋፈያ ጣቢያ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆኗል፡፡ ከአዲስ አበባ በ500 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ ተገንብቶ ለምርቃት ዝግጁ የሆነው የነጆ ማከፋፈያ ጣቢያ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመር እና አራት ባለ 33 ኪ.ቮ. ወጪ መስመሮች አሉት፡፡ ለማከፋፈያ ጣቢያው ከጊንቢ - መንዲ ከተዘረጋ ባለ 132 ኪ ቮ. መስመር ላይ ተቆረጦ የሁለት ኪ.ሜ ርዝመት ያለው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተዘርግቷል፡፡ ሁለቱ የማከፋፈያ ጣቢያዎች በቡኢ እና በነጆ ከተሞችና በዙሪያቸው ላሉ አካባቢዎች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ያስችላሉ ተብሎ ይታመናል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያዎቹን ገንብቶ ለአገልግሎት ዝግጁ ያደረገው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኮንስትራክሽን የራስ አቅም(Own force ) ቢሮ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 01 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content
+2

ለሠራተኞች የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች የሚሰጠው በሚኖራቸው አፈፃፀም መሠረት ይሆናል ተባለ ……….///………….. የውጤት ተኮር የአፈፃፀም ስርዓት መዘርጋት ውጤታማ ስራ ለመስራት እንደሚያግዝ የፐርፎርማንስ ማኔጅመንት እና ሪዋርድ ቢሮ ገለፀ። ቢሮው በውጤት ተኮር የአፈፃፀም ስርዓት ( performance Management) ዙሪያ በትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ስራ አስፈፃሚ ስር ለሚገኙ የመምሪያ ኃላፊዎች እና ስራ አስኪያጆች የ3 ቀን ስልጠና ሰጥቷል። የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ አእምሮ እንደገለፁት ስልጠናው በተቋሙ የተዘረጋውን የውጤት ተኮር የምዘና ስርዓት ሁሉም የስራ መሪና ሠራተኛ ከተቋሙ ስትራቴጂ፣ ራዕይ፣ ተልዕኮ እና እሴቶች ጋር በማያያዝ እንዲፈጽም ለማድረግ ያግዛል። እንደ ኃላፊው ገለፃ የምዘና ሥርዓቱ ስርዓቱ ሠራተኞች በአፈፃፀማቸው ልክ የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞችን እንዲያገኙ የሚያስችል አሰራር ለመዘርጋትና ወጥነት ያለው የሥራ አፈፃፀም ምዘና ለማካሄድ ያገለግላል። የውጤት ተኮር የአፈፃፀም ስርዓት መመሪያ በ2011ዓ.ም ወጥቶ የነበረ ሲሆን በአተገባበር ግን ልዩነቶች እንደታዩበት ነው ሥራ አስኪያጁ ያስታወቁት። በአሁኑ ሰዓት ግን የሠራተኞችን ጥቅማ ጥቅም በመመሪያው መሠረት እንዲፈፀም ለማድረግ እየተሰራ በመሆኑ ሠራተኛው ይህን ተገንዝቦ አፈፃፀሙን እንዲያሻሽል፣ ቅሬታ የቀነሰ ወይም የማይኖርበት ስርዓት ለመዘርጋትና የተቋሙን ግብ ለማሳካት የተለያዩ ሥራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ። ከስልጠናው ጎን ለጎን በውጤት ተኮር የአፈፃፀም ስርዓት ዙሪያ ተሳታፊዎች በየክፍላቸው የነበሩ ችግሮችን አቅርበው ውይይት የተካሄደ ሲሆን ይህም በቀጣይ የተሻለ ሥራ ለመስራት እንደሚያግዝ ነው የተገለፀው። የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች የውጤት ተኮር የአፈፃፀም ስርዓት መመሪያውን ቢተገብሩ ሥራቸውን በአግባቡ ማከናወን እንደሚችሉ እና ባከናወኑት ተግባር ልክ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ በማመን ለተግባራዊነቱ በትብብር መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል። የሠው ሃብት ልማት መምሪያ ዳይሬክተር ዶ/ር ወንድወሰን ካሳ በበኩላቸው ስልጠናው የእርስ በርስ የልምድ ልውውጥ የሚገኝበትና የተነሱ ሃሳቦችን በመያዝ በቀጣይ የተሻለ ሥራ ለመስራት የሚያግዝ መሆኑን ገልፀዋል። ከስልጠናው የተገኙ ሃሳቦችን በመያዝ በቀጣይ የተሻለ ሥራ ለመስራት መዘጋጀት እና ለመመሪያው መተግበር ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ እስከ አሁን ሪጅኖች የሠራተኞችን የሥራ አፈፃፀም መረጃዎችን በመላክ በኩል የተለያዩ ክፍተቶች እንደነበሩባቸውም ኃላፊው አስታውሰው በቀጣይ ለሠራተኞች የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች የሚሰጠው ከሥራ ክፍላቸው በሚላከው አፈፃፀም መሠረት በመሆኑ ሪጅኖች የሠራተኞቻቸውን የአፈፃፀም መረጃ በወቅቱ መላክ እንዳለባቸው አሳስበዋል። ሠራተኞችም መረጃቸው በወቅቱ መላኩን ክትትል ማድረግ ይኖርባቸዋል ነው የተባለው። የትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሃብታሙ ውቤ በበኩላቸው ስልጠናው የተቋሙን ግብ ለማሳካትና ሠራተኛው ተቋሙ በሚተገብራቸው አሠራሮች ላይ ንቁ ተሳትፎ እንድኖረው ለማድረግ ፉይዳው የጎላ ነው ብለዋል። የውጤት ተኮር አፈፃፀም ስርዓትን በተቋሙ ወጥ በሆነ መልኩ ለመተግበር የሥራ መሪዎች የሠራተኞችን አፈፃፀም ሲሞሉ የአፈፃፀም መለኪያዎችን መሠረት በማድረግ እና ፍትሃዊነትን በተላበሰ መልኩ ለማከናወን ትኩረት ሰጥተው መስራት እንዳለባቸው ሥራ አስፈፃሚው አሳስበዋል። በስልጠናው ላይ 40 የሚሆኑ በትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ ስር የሚገኙ የመምሪያ ዳይሬክተሮችና ሥራ አስኪያጆች የተሳተፉ ሲሆን በቀጣይ ለሌሎች የስራ ክፍሎች ተመሳሳይ ስልጠና ለመስጠት እቅድ ተይዞ እየተሠራ መሆኑን ከፐርፎርማንስና ሪዋርድ ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 01 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content
+2

በወልዲያ ከተማ የተጀመረው የከፍተኛ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ 48 በመቶ ደረሰ ………..////……… በሰሜን ወሎ ዞን ወልድያ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው የወልዲያ ባለ 400 /230/33/15 ኪ.ቮ. የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት አማካይ አፈጻጸም 48 በመቶ መድረሱን የባህርዳር-ኮምቦልቻ -ወልዲያ ከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የሳይት ተቆጣጣሪ መሐንዲስ አቶ ሐብታሙ ተሾመ አስታወቁ፡፡ አቶ ሃብታሙ እንደገለፁት እስከ አሁን የኤሌክትሮ መካኒካልና የብረታ ብረት ተከላና ለኤሌክትሪክ ገመዶች ቀበራ የሚውል ግንባታ ፣ እንዲሁም ሁለት የባለ 63 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመር ተከላና ሁለት የባለ 250 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመር መትከያ የመሰረት ግንባታ ተጠናቋል፡፡ የመቆጣጠሪያ ቤት፣ የሠራተኞች መኖሪያ ቤት፣ የጥበቃ ቤት፣ የስዊች ጊር ቤት ግንባታ፣ የፍሳሽ ማስወገጃ ግንባታ የማጠናቀቂያ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ በቀጣይም የጠጠር ንጣፍ፣ የውስጥ አጥር፣ የሲዊች ያርድ ግንባታ እና የኬብል ዝርጋታ ሥራዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው እንደሚከናወኑ መሐንዲሱ ጠቁመዋል፡፡ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎችን የመገጣጠምና የብረታ ብረት ስራዎች የተጠናቀቁ ሲሆን በቀጣይ የስዊች ጊር ስራዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው የሚሰሩ መሆናቸውን የሳይት መሐንዲሱ ተናግረዋል፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው 500 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ሁለት ባለ 250 ትራንስፎርመሮች እና 126 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለቸው ሁለት ባለ 63 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች ይኖሩታል፡፡ ለማከፋፈያው ጣቢያው የሚያስፈልጉት የተለያዩ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ከ 40 በመቶ በላይ ወደ ግንባታ ሥፍራው ተጓጉዘው የደረሱ ሲሆን ቀሪዎቹም ተፈብርከው በቅርቡ ወደ ሀገር ቤት ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ የትናየት ይመር እንደተናገሩት የማከፋፈያ ጣቢያውን ስራ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ከ913 ሚሊዮን ብር በላይ ፋይናንስ ተበጅቶለታል፡፡ ግንባታውን ሻንጋይ ኤሌክትሮ ግሩፕ የተባለ የቻይና ኩባኒያ ሲያከናውን የአማካሪነት ስራውን ደግሞ የኢትዮጵያ ኤሌከትሪክ ኃይል እያከናወነ ይገኛል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው ስምንት ባለ 33 ኪሎ ቮልት እና ስምንት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች የሚኖሩት ሲሆን አማካይ አፈጻጸሙ ከ ከ48 በመቶ በላይ ደርሷል፡፡ ማከፋፋያ ጣቢያው ሲጠናቀቅ የወልዲያ ኢንደስትሪ ፓርከ፣ የባቡር ፕሮጀክቱ እና የወልዲያ ከተማና የአካባቢው ን የኃይል ፍላጎት አቅርቦትን ጥያቄ ከመመለሱም ባሻገር አስተማማኝ ኃይል እንዲኖር በማድረግ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 25 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content
+6

የተቋረጠውን የዋግ ኽምራ ዞን ኤሌክትሪክ ለማገናኘት እየተሰራ ነው ........///........ በዋግ ኽምራ ዞን በሚገኙ አብዛኛዎቹ አካባቢዎች የተቋረጠውን የኤሌክትሪክ አገልግሎትመልሶ ለማገናኘት ጥረት እየተደረገ መሆኑን የሰሜን ምስራቅ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ዳይሬክተር አቶ ታገል ደገፉ እንደገለፁት በአካባቢው ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ ኤሌክትሪክ የተቋረጠው በሶስት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ ስርቆት በመፈፀሙና በመውደቃቸው ነው። ወደስፍራው ለጥገና የተንቀሳቀሰው ቡድን የወደቁትን ምሰሶዎች መልሶ ለመትከል ከእሁድ ጀምሮ እንቅስቃሴ መጀመሩን ተናግረዋል። ከአንድ ወር በፊት ከአላማጣ እስከ ሰቆጣ በሚገኙት 269 ምሰሶዎች ላይ የፍተሻ ስራ መከናወን መጀመሩን የጠቀሱት ዳይሬክተሩ በስምንት የብረት ምሰሶዎች ላይ የስርቆት ሙከራ መፈፀሙን በማረጋገጥ ምሰሶዎቹ ከመውደቃቸውና ኤሌክትሪክ ከመቋረጡ በፊት መስተካከሉን ገልፀዋል። በአሁኑ የተፈፀመው ስርቆት በመስመሩ ውስጥ በሚገኙትና የፍተሻ ስራ ባልተካሄደባቸው 47 ምሰሶዎች ውስጥ በሶስቱ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። የደረሰውን ችግር በተመለከተም ለዞኑ አስተዳደር የማሳወቅ ስራ መሰራቱንም ተናግረዋል። በምሰሶዎቹ መውደቅ የዞኑ ዋና ከተማ ሰቆጣን ጨምሮ በአምደወርቅ፣ በዳህና፣በአበርገለ፣ በሰሀላ፣በዝቋላና በአካባቢያቸው ኤሌክትሪክ ተቋርጧል። የዋግ ኽምራ ዞነ አብዛኛዎቹ አካባቢዎች ኃይል የሚያገኙት ከአላማጣ ባለ 66 ኪሎቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ከሚወጣ መስመር ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 24 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content

photo content

ሠራተኞች በአፈፃፀማቸው ልክ ተጠቃሚ የሚሆኑበት አሰራር ተግባራዊ ይደረጋል - የሠው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ ………///…………. በውድድር ጊዜ የትምህርት ዓይነት፣ የትምህርት ደረጃና የስራ ልምድ አያያዝ አግባብነት ባለውና ወጥ በሆነ መልኩ በሁሉም የሥራ ክፍሎች ሊተገበር እንደሚገባ የኢትየጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ አሳሰቡ፡፡ ተቋሙ በቀጣይ ዓላማውን ያማከለና ሠራተኞች ባከናወኑት ተግባር ልክ ተጠቃሚ የሚሆኑበት የውጤት ተኮር ስርዓት ተግባራዊ እንደሚያደርግም ገልፀዋል፡፡ የሠው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ተማም አፍደል በበኩላቸው ከማስታወቂያ ጀምሮ የፈተና አወጣጥ፣ የፈተና እርማት እና የውጤት ማሳወቂያ ሂደቶች በተያዘላቸው ስታንዳርድ መሠረት በማጠናቀቅ ከቅሬታ ነፃ የሆነ አገልግሎት ለመስጠት እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ ደግሞ በሁሉም የሥራ ክፍሎች ወጥ የሆነ የማወዳደሪያ መስፈርቶችን ከመተግበር አኳያ ክፍተቶች በመኖራቸው ሊስተካከሉ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡ በደረጃ ዕድገት፣ በዝውውርና ቅጥር ላይ የሚቀርቡ የሰራተኛ ቅሬታዎች በዘለቄታው ለመፍታት ይረዳ ዘንድ በሠው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ የሚወጡ ደንቦችና መመሪያዎች ሳይሸራረፉ በሁሉም የሥራ ክፍሎች ሊተገበሩ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ የውይይቱ ተሳታፊዎች እንደገለፁት ለውድድር የሚወጡ ጥያቄዎችን ሚስጥራዊነት እንዲጠበቅ ለማድረግ ራሱን የቻለ የፈተና ቋት መፍጠር ያስፈልጋል፡፡ የሰው ኃይል ሁለንተናዊ አሰራርን የሚያዘምኑ በርካታ ሃሳቦች በተወያዮች የቀረቡ ሲሆን ከመሰል ተቋማት ልምድ በመውሰድ፣ የሚሻሻሉ መመሪያዎችንና ደንቦች በመለየት የተሻለ አሠራርን ተግባራዊ ለማድረግ በርካታ ሥራዎች ማከናወን እንደሚገባም አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡ የሰው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ እና የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር አመራሮች የተሳተፉበት ውይይት ላይ በተቋሙ የሚከናወኑ የደረጃ ዕድገት፣ ዝውውር እና የቅጥር ተግባራት ወጥ በሆነና የአሰራር ስርዓትን ባገናዘበ መልኩ እንዲከናወኑ ማድረግ በሚቻልበት መንገድ ላይ ትኩረት አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአሁኑ ጊዜ ከ8 ሺህ በላይ ቋሚና ጊዜያዊ ሠራተኞች አሉት፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 24 ቀን 2013 ዓ.ም