ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 537 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 368 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 174 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 537 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 30 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 10، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -6، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 24.86‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.87‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 862 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 620 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 9.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 01 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 537
المشتركون
-624 ساعات
-207 أيام
+1030 أيام
أرشيف المشاركات
በተቋሙ የስትራቴጂክ ዕቅድ ዝግጅት ላይ ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀረበ ....///.... በተቋሙ የሦስት ዓመት የስትራቴጂክ ዕቅድ ዝግጅት ላይ ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች የጀመሩትን የነቃ ተሳትፎ አጠናክረው እንዲቀጥሉ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ጥሪ አቀረበ። በዘርፉ የኃይል ማመንጫዎች ስትራቴጂና ኢንቨስትመንት ሥራ አስኪያጅ አቶ ማርዓለም አምደብርሃን እንደገለፁት የተቋሙን የሦስት ዓመታት የስትራቴጂክ ዕቅድ ለማዘጋጀት ሁሉም የሥራ ዘርፎች የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ ይገባል። የተቋሙን የሦስት ዓመታት የዕቅድ ዝግጅት ላይ ግብዓት ለመሰብሰብ የስትራቴጂ ሳምንት በሚል መሪ ሀሳብ በየሥራ ዘርፎቹ ውይይት መጀመሩን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል። እንደ አቶ ማርዓለም ገለፃ ውይይቱ ለሁሉም የተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች የስትራቴጂክ ዕቅዱ እየተዘጋጀ ያለበትን ሂደት ለማሳወቅ እና ግብዓት ለመሰብሰብ ያለመ ነው። በስትራቴጂክ ሳምንቱ የተቋሙን ጥንካሬዎች፣ ድክመቶች፣ መልካም አጋጣሚዎች እና ስጋቶች እንዲሁም ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ በሁሉም የሥራ ዘርፎች የግንዛቤ መፍጠር ሥራ ይሰራል። ተቋሙ በቀጣይ ተግባራዊ ለማድረግ ላቀዳቸው ቁልፍ የትኩረት መስኮችና አቅጣጫዎች ተጨማሪ ግብዓት ለመሰብሰብ ውይይቶቹ አጋዥ እንደሚሆኑም ነው ሥራ አስኪያጁ የተናገሩት። ሁሉም የሥራ ዘርፎች ባለፉት ሦስት ዓመታት የሥራ አፈፃፀማቸው ላይ የታዩ ጠንካራና ደካማ ጎኖች እንዲሁም ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ ጉዳዮችን በመለየት በሚዘጋጀው የስትራቴጂከ ዕቅድ ለማካተት እንደሚሰራም ነው አቶ ማርዓለም የጠቀሱት። የተቋሙ ሠራተኞች በየሥራ አካባቢያቸው የሚያጋጥሟቸው የተለያዩ ችግሮችና ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች በውይይታቸው ላይ ማንሳት እንደሚጠበቅባቸውም ገልፀዋል። የሦስት ዓመታት የስትራቴጂክ ዕቅድ ዝግጅቱን አስመልክቶ የተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ የሥራ ዘርፍ ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች የጀመሩትን ውይይት የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ መርተውታል። በቀጣይም ሁሉም የሥራ ዘርፎች በዕቅዱ ላይ ውይይት ያካሂዳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ማርዓለም ተናግረዋል። ተቋሙ በቀጣይ ሦስት ዓመታት የሚተገብረውን የስትራቴጂክ ዕቅድ አካታችና አሳታፊ ለማድረግ ከተቋሙ መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር አመራሮች ጋር ውይይት ማካሄዱ ይታወሳል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም.

photo content
+6

ሪጅኑ የሥራ ኃላፊዎችና እና ሠራተኞችን አፈጻጸም ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን ገለፀ ……..////……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ ሪጅን 1 የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬሽን መምሪያ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞችን አፈፃፀም ለማሻሻል የሚያግዝ ሥልጠና መስጠቱን አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ እንደተናገሩት በሪጅኑ ሥር ለሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ቴክኒሺያኖች በኃይል ማከፋፈያ ጥገና እና የፍተሻ (inspection) ቅደም ተከተሎች ላይ ያተኮረ ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ የንድፈ ሀሳብ ሥልጠናው በኤሌክትሪክ ኃይል አጋዥ ሲስተም (AuxiliarySystem) እና በባትሪ ሲስተም ላይ ያተኮረ ነው፡፡ ዳይሬክተሩ እንደገለፁት ስልጠናው በማከፋፋያ ጣቢያ የሚገኙ የኦፕሬሽንና የጥገና ሠራተኞች በእውቀት እና ክህሎት ላይ የተመሠረተ ስራ እንዲያከናውኑ ከማገዙም ባሻገር ከብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል (LDC) ጋር ያለውን የስራ ግንኙነት ለማዘመን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል፡፡ በተመሳሳይ በሪጅኑ ሥር ለሚገኙ የማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊዎች እና ለዘርፍ ሥራ አስኪያጆች በሪፖሪቲንግ ሲስተም እንዲሁም በመሠረታዊ የኮምፒውተር ክህሎት ዙሪያ በተግባር የተደገፈ ሥልጠና መሰጠቱን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡ በሪጅኑ የሰው ሀብት አስተዳዳር፣ ንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ አለማየሁ ተገኝ በበኩላቸው የሪጅኑን የሥራ አፈፃፀም ይበልጥ ለማጎልበት ያለመ የተግባር እና የንድፈ ሃሳብ ሥልጠናዎች በ2016 በጀት ዓመት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አስታውቀዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 09 ቀን 2015 ዓ.ም.

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር 4ኛ የሥራ መደብ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ሚያዚያ 25 ቀን 2015 ዓ.ም. ባወጣው የውጪ ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመል
+1
ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር 4ኛ የሥራ መደብ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ሚያዚያ 25 ቀን 2015 ዓ.ም. ባወጣው የውጪ ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመልካቾች በሙሉ ሰኔ 14 ቀን 2015 ዓ.ም. ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ሜክሲኮ ኬ ኬር በሚገኘው በዋናው መ/ቤት 20ኛ ፎቅ የጽሑፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ
የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ

photo content
+1

ተቋሙ በቀጣይ ሶስት ዓመታት የሚተገብረውን ዕቅድ አካታችና አሳታፊ ለማድረግ እየሰራ ነው .........///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቀጣይ ሦስት አመታት የሚተገብረውን ስትራቴጂክ ዕቅድ አካታችና አሳታፊ ለማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን የኮርፖሬት ፕላኒንግ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ። ተቋሙ በሚያዘጋጀው የሦስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ ግብዐት ለመሰብሰብ ከተቋሙ መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር አመራሮች ጋር ዛሬ በሂልተን ሆቴል በተካሄደው ውይይት ላይ በሥራ ላይ ያለው ስትራቴጂክ ዕቅድ ግምገማ እና የቀጣዩ ዕቅድ የትኩረት መስኮች ላይ ያተኮረ ሪፖርት ቀርቧል። በውይይቱ ላይ ሥራ አስፈፃሚው አቶ አንዱዓለም ሲኣ እንደገለፁት ውይይቱ ያለፉት ሦስት ዓመታት የተቋሙ አፈጻጸም ላይ የታዩ ጠንካራና ደካማ ጎኖች እንዲሁም ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ ጉዳዮችን በመለየት በሚዘጋጀው ስትራቴጂከ ዕቅድ ለማካተት ግብዐት ለመሰብሰብ ነው። ተቋሙ በቀጣይ ተግባራዊ ለማድረግ ያቀዳቸውን ቁልፍ የትኩረት መስኮችና አቅጣጫዎች ላይ ተጨማሪ ግብዐት ለመሰብሰብ የተቋሙ የውስጥ ባለድርሻ ከሆነው መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር ጋር መወያየት ማስፈለጉን አቶ አንዱአለም ተናግረዋል። በቀጣይም በየደረጃው ከሠራተኞችና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ተመሳሳይ ውይይት ለማካሄድ መታቀዱን አስታውቀዋል። በውይይቱም በሥራ ላይ የቆየው ስትራቴጂክ ዕቅድ አሳታፊ እንዳልነበረ፣ የሠራተኞች፣ የደንበኞችና የባለድርሻ አካላት የእርካታ መጠን በዕቅድ ቢቀመጥም በተግባራዊ አለመመመዘኑ፤ የንፋስ፣ የውሃና የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የአዋጭነት ጥናት ቢካሄድም ወደተግባር አለመገባቱ ተቋሙ ዕቅዱን እንዳያሳካ ማድረጉ ተነስቷል፡፡ በተጨማሪም የተቋሙ ዓመታዊ ዕቅድ ሲታቀድ ስትራቴጃዊ ግቦች ተገምግመው ባለቤት እንዲኖራቸው አለመደረጉ፣ የአፈጻጸም ክትትልና ግምገማ ባህል አነስተኛ መሆን፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር ተግባራዊ አለመደረግና የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ዝቅተኛ መሆን አፈጻጸሙን ዝቅ እንዳደረገው ተገልጿል፡፡ ተቋሙ የተለዩትን ክፍተቶችን በማረም በቀጣይ ዕቅዱ በሰው ሀብት ልማት፣ በልህቀት፣ በፋይናንስ ሥርዓት፣ በኃይል መሰረተ ልማት ግንባታ፣ በኮንስትራክሽን ንግድ እንዲሁም በፈጠራና ቴክኖሎጂ ትራንስፎርሜሽን ትልቅ ውጤት ለማምጣት በትኩረት መታቀዱን አቶ አንዱዓለም ገልጸዋል፡፡ የሰው ኃይል ልማትን አቅም በመገንባት የጋራ ተጠቃሚ ለመሆን የሠራተኛውን ልምድና ተሳትፎ ማሳደግ ተገቢ ነው ያሉት አቶ አንዱዓለም አቅማቸውን ተጠቅመው ለሚሠሩ ሠራተኞች የማበረታቻ ሥርዓት መዘርጋት የሚያስችል ዕቅድ መዘጋጀቱን በውይይቱ አንስተዋል፡፡ ወጪ ቆጣቢ አሰራሮችን በመዘርጋትና የተለያዩ የገቢ አማራጮችን በማስፋት ገቢን ለማሳደግ፤ የኃይል ሽያጭን ጨምሮ ለኃይል ፈላጊ ኢንዱስትሪዎች እና በነዳጅ ለሚሰሩ ተሸከርካሪዎች በቀጥታ ኃይል በማቅረብ የተረጋጋና ቀጣይነት ያለው የፋይናንስ ሥርዓትን ለመፍጠር በትኩረት እንደሚሰራ ተገልጿል፡፡ የመሰረታዊ ሠራተኛ ማህበር አመራሮች በበኩላቸው በዕቅድ ዝግጅቱ ላይ አሳታፊ በሆነ መንገድ ግብዐት ለመሰብሰብ የታየውን ጅማሬ አድንቀዋል። ለቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት እንዲያገለግል በሚዘጋጀው ስትራቴጂክ ዕቅድ የመሠረተ ልማት ሥርቆት፣ ለሠራተኞች ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠር፣ የተቋሙን ፋይናንስ ያገናዘበ የጥቅማ ጥቅም ስርዓት መዘርጋት፣ ተቋማዊ የሥራ ባህልን ማሳደግ እና የገቢ ምንጮችን ማስፋት በዕቅዱ እንዲካተቱ አስተያየት ሰጥተውባቸዋል። በውይይቱ የተገኙ ግብዓቶችን በመውሰድ የተሻለና ሁሉን ያካተተ እንዲሁም የተቋሙን፣ የደንበኞችንና የሠራተኛውን የጋራ ተጠቃሚነት ያማከለ ስትራቴጅክ ዕቅድ እንደሚዘጋጅ እና ከትግበራ በፊት ዝርዝር ውይይት እንደሚደረግበት አቶ አንዱዓለም አረጋግጠዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ     ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric    ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication    ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia    ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower    ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et    ሰኔ 07 ቀን 2015 ዓ.ም.

photo content
+9

ፋብሪካዎች ተሠርቀው የሚመጡ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ብረቶችን ባለመግዛት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ ..........///........... በኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ የሚፈፀመውን ስርቆት ለመከላከል ባለ ድርሻ አካላት የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ ጥሪ አቀረቡ። ሥራ አስፈፃሚው አቶ ሀብታሙ ውቤ እንደተናገሩት በአሁኑ ወቅት በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ እየደረሰ ያለው ስርቆት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። በመስመሮቹ ላይ እየተፈፀመ ያለው ስርቆት ለህብረተሰቡ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እየተሰራ ላለው ሥራ ተግዳሮት ከመሆኑም ባለፈ ተቋሙን ለከፍተኛ ኪሳራ እየዳረገው ይገኛል ብለዋል። በስርቆቱ የተሳተፉ አካላትን ተጠያቂ ለማድረግ እና ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ለማድረግ መሰረተልማቶቹ የተተከሉባቸው አካባቢዎች ነዋሪዎች ለፖሊስ እና ለመስተዳድር አካላት መረጃ በመስጠትና እርምጃ እንዲወሰድ በማድረግ በኩል የበኩላቸውን እንዲወጡ አቶ ሀብታሙ ጠይቀዋል። በማዕከላዊ ሪጅን 2 የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጎሳዬ ደምሴ በበኩላቸው  ስርቆት የሚፈፀምባቸውን ምሰሶዎች በመከታተል ጥገና ቢከናወንም ተደጋጋሚ ስርቆት ስለሚፈፀምባቸው ውጤት ማምጣት አለመቻሉን ተናግረዋል። ከዚህ በፊት ከብረታ ብረት ፋብሪካዎችና ከባለድርሻ አካላት ጋር ተገናኝቶ ችግሩን መከላከል በሚቻልበት መንገድ ላይ ውይይት በማድረግ በኩል ውስንነቶች እንደነበሩ አንስተው በቀጣይ ግን ከድርጅቶችና ችግሩ በስፋት በሚስተዋልበት አካባቢ ከሚገኙ ነዋሪዎች ጋር  ውይይቱ እንደሚደረግ አቶ ጎሳዬ ጠቁመዋል። የአፖሎ ስቲል የምርት ሱፐርቫይዘር አቶ ጌቱ ሞገስ እና የአቢሲኒያ ኢንቲግሬትድ ስቲል ፋብሪካ ኤሌክትሪካል ኢንጅነር ሔኖክ ደምሰው በሰጡት አስተያየት የተሰረቁ የኤሌክትሪክ፣ የቴሌና የባቡር መሠረተ ልማቶች ወደ ማቅለጫ ፋብሪካ እንዳይገቡ እንደሚደረግ ተናግረዋል። ብረቶችን ለሽያጭ ወደ ፋብሪካ ይዘው የሚመጡ አካላትን ለሚመለከታቸው የህግ አካላት አሳልፈው እንደሚሰጡ የተናገሩት አስተያየት ሰጪዎቹ፣ ድርጅቶች ተሠርቀው የሚመጡ ብረቶችን ባለመግዛት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል። ችግሩን በዘላቂነት ለመከላከል የብረት ፋብሪካዎች፣ የሚመለከታቸው ተቋማት እና የአካባቢው ማህበረሰብ በቅንጅት መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 07 ቀን 2015 ዓ.ም.

photo content
+3

የጣቢያውን ኦፕሬሽን ለማቀላጠፍ የሚያግዝ የካይዘን ፍልስፍና ተግባራዊ እየተደረገ ነው ………..///………. በጊቤ 1 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራውን ለማቀላጠፍ የሚያግዝ የካይዘን ፍልስፍና ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑ ተገለፀ። የጣቢያው የኦፕሬሽንና ጥገና ባለሙያ የሆኑት አቶ የጠራወርቅ በላይ እንደገለፁት በጣቢያው የካይዘን አሰራርን ለመተግበር በኢትዮጵያ ካይዘን ኢንስቲትዩት ለጣቢያው ባለሙያዎች ስልጠና ተሠጥቷል። ሥልጠናውን ተከትሎ የጣቢያውን ንብረት የመለየትና የማደራጀት ሥራ መሰራቱን ባለሙያው ተናግረዋል። እንደ ባለሙያው ገለጻ ለጣቢያው አስፈላጊ የሆኑ የመለዋወጫ ዕቃዎች ተለይተው በመደራጀታቸው አስቸኳይ ጥገና ሲያስፈልግ መለዋወጫ ለመፈለግ የሚወስደውን ጊዜ ያሳጥራል። የጣቢያው የጥገና ቡድን አባልና የግዢ ባለሙያ አቶ ሀብታሙ ጌቴ በበኩላቸው ጣቢያው የማይፈልጋቸው ዕቃዎች በቀይ ካርድ ለይቶ ተቋሙ በሚያስቀምጠው አቅጣጫ መሰረት እንደሚወገዱ ገልፀዋል። በጣቢያው ውስጥ ያሉ ንብረቶች በሙሉ ከአምስት ወር ባልበለጠ ጊዜ ይደራጃሉ ያሉት ባለሙያው የተደራጁት ንብረቶችም መለያ ተሰጥቷቸውና በዳታ ቤዝ ተመዝግበው ኮምፒውተር ላይ እንደሚቀመጡ ገልጸዋል። ካይዘን ሚዛናዊ የሥራ እና ማህበራዊ አከባቢን በማሳመር ለዕይታ ማራኪ የሥራ ቦታ እንዲኖር የሚያስችል ወጪ፤ ጊዜና ጉልበትን የሚቆጥብ ከጃፓን የተቀዳ የአሰራር ፍልስፍና ነው። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 06 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+6

በከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የሚፈፀመውን ስርቆት በጋራ መከላከል ይገባል .........///........ በከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የሚፈፀመውን ስርቆት በጋራ መከላከል እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አሳሰቡ። ሥራ አስፈፃሚው አቶ ሀብታሙ ውቤ በማስተላለፊያ መስመሮችና የኃይል ተሸካሚ ብረቶች ላይ የሚፈፀመውን ስርቆት ለመከላከል ከብረታብረት ማቅለጫ ፋብሪካዎችና ባለድርሻ አካላት ጋር በተደረገ የውይይት መድረክ ላይ እንደገለፁት እንደሀገር ኤሌክትሪክ ለማስፋፋት ጥረት እየተደረገ ቢሆንም ስርቆቱ ግን ከፍተኛ ስጋት ሆኗል። የሚፈፀመው ስርቆት በተቋሙ ላይ ብቻ ሳይሆን በከፍተኛ፣ መካከለኛና አነስተኛ ኃይል ተጠቃሚዎች ላይ ጭምር ከፍተኛ ጫና እያሳደረ እንደሚገኝ አብራርተዋል። በርካታ የብረት ማቅለጫ ፋብሪካዎች ባሉበት እንደ ዱከም፣ ቢሾፍቱና ሞጆ ባሉት አካባቢዎች በማወቅም ይሁን ባለማወቅ በሚፈፀመው ስርቆት የተነሳ የሚፈጠረውን ችግር ለመከላከል የአካባቢው የመስተዳድር አካላት፣ የፀጥታ አካላት፣ ብረታ ብረት ማቅለጫ ፋብሪካዎችና ህብረተሰቡ ርብርብ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። የማዕከላዊ ሪጅን 2 የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ዘበርጋ በበኩላቸው በመጠናቀቅ ላይ ባለው በጀት ዓመት በአደአ ወረዳ 1ሺህ 405 የታወር ብረቶች ተፈታተው መሰረቃቸውን እና በቢሾፍቱ ከተማ፣ በድሬ ወረዳ ቃጂማ ቀበሌ፣ በዱከም እና በዲባዩ ቀበሌ ተደጋጋሚ ስርቆቶች እያጋጠሙ መሆናቸውን ገልፀዋል። በስርቆቱ የተነሳ የሚባክነው ኃይል እና የተሰረቀውን ለመተካት የሚወጣው ወጪ ከፍተኛ ከመሆኑ ባሻገር የኢንደስትሪዎች የማምረት ሂደት እንደሚስተጓጎልና ህብረተሰቡንም ኤሌክትሪክ እንደሚያሳጣው ተናግረዋል። በስርቆቱ የተጎዱትን የብረት ምሰሶዎች በእንጨት ምሰሶ በመተካት አገልግሎት እንዲሰጡ እየተደረገ ቢሆንም የአገልግሎት ዕድሜያቸው አጭር ስለሆነ ከፍተኛ ጥንቃቄ ይፈልጋል ብለዋል። የብረታብረት አቅላጭ ፋብሪካዎች በበኩላቸው ቁርጥራጭ ብረታብረቶችን ሲቀበሉ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ብረቶች፣ ጨረራ አመንጪ ቁሶችና ተቀጣጣይ ነገሮች አለመኖራቸውን አረጋግጠው እንደሚቀበሉ ገልፀዋል። እንዲህም ሆኖ በሚፈፀመው ስርቆት ለቀናት ኃይል ስለሚቋረጥ ምርት ማምረት እንደተቸገሩና ሰራተኞቻቸው ሳይሰሩ ለመክፈል እንደተገደዱ በመግለፅ ስርቆትን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። የዱከም ክፍለከተማና የአድአ ወረዳ ተወካዮችም ማህበረሰቡን በማወያየት መሰረተልማቱን እንደራሱ ንብረት እንዲጠብቅ እንሰራለን ብለዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 05 ቀን 2015 ዓ.ም.

photo content
+6

በማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የሚፈፀሙ ስርቆቶች ለኦፕሬሽን ሥራ ፈተና እየሆኑ ነው .........///........ በኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ እየተፈፀመ ያለው ስርቆት ለኦፕሬሽን ሥራው ፈተና እንደሆነበት የደቡብ ሪጅን 2 የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ታዬ እንዳስታወቁት ሪጅኑ ከሚያስተዳድራቸው የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች መካከል በአብዛኛዎቹ ላይ ተደጋጋሚ የስርቆት ወንጀሎች እየተፈፀመባቸው ይገኛል። በአሁኑ ወቅትም በወላይታ ሶዶ -ይርጋለም -ገናሌ ዳዋ ባለ 400 ኪሎ ቮልት  መስመር  በሪጅኑ ውስጥ  ከሚገኙ 102 የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች መካከል በተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ 55  ምሰሶዎች ላይ ስርቆት ተፈፅሞባቸዋል። ከእያንዳንዱ ምሰሶ ከ300 እስከ500 ብረቶች ተፈትተው እንደተወሰዱ ያነሱት ዳይሬክተሩ የተፈቱትን ወደነበረበት ለመመለስ ለአንድ ታወር ብቻ እስከ 500 ሺህ ብር  እንዲሁም ምሰሶው ከወደቀ መልሶ ለመገንባት ደግሞ ከሦስት እስከ አምስት ሚሊዮን ብር እንደሚጠይቅ ተናግረዋል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ በሀላባ - ሶዶ እና ሶዶ - ሳውላ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ ተደጋጋሚ ስርቆቶች እየተፈፀሙ ነው። በመስመሮቹ ላይ የሚፈፀመው ስርቆት ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዳያገኝ ከማድረጉም ባለፈ ተቋሙን ለከፍተኛ ኪሳራ እየዳረገው ይገኛል ብለዋል። በሪጅኑ የጥገና ሠራተኛ የሆኑት ተማም መሀመድ በበኩላቸው ስርቆት የተፈፀሠባቸው ምሶሶዎች ወድቀው ሌላ ተጨማሪ ጉዳት ሳያደርሱ ለመጠገን  ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነ ተናግረዋል። የምሰሶዎችን ደህንነት ለማረጋገጥ መደበኛ ፍተሻ እንዲሁም ተደጋጋሚ ስርቆት በሚፈፀምባቸው አካባቢዎች ላይ ደግሞ በየሳምንቱ የፍተሻ ሥራዎች እንደሚከናወን ባለሙያው ጠቁመዋል። የስርቆት ወንጀሉ በተደጋጋሚ በመፈፀሙ ምክንያት የመለዋወጫ ዕቃ እጥረት እንዳጋጠመ እና በአሁኑ ወቅትም ጥገናዎችን ማሻሻያ  (modify) በማድረግ ለመስራት እንደተገደዱ አመልክተዋል። በአሁኑ ወቅት ስርቆት የተፈፀመባቸው አንዳንድ ምሰሶዎች ከዚህ በፊት ተደጋጋሚ ስርቆት ተፈፅሞባቸው ተጠግነው የነበሩ እንደሆነም ተገልጿል። በስርቆት ወንጀል የተጠረጠሩ አካላት ላይ የሚወሰደው እርምጃ አስተማሪ አለመሆኑ እና በየደረጃው ያሉ የመንግስት አካላት ትኩረት ሰጥተው ባለመስራታቸው ስርቆቱን መግታት አለመቻሉን ገልፀዋል። የታወር ስርቆትን ለመከላከል በየደረጃው የሚገኙ የመንግስት አካላት እና ህብረተሰቡ በኃላፊነት ስሜት ጥበቃ ማድረግ እንዳለባቸውም አሳስበዋል። የደቡብ ሪጅን 2 የኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ 1 ሺህ 200 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመርና ስምንት ማከፋፈያ ጣቢያዎችን እያስተዳደረ ይገኛል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 05 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+5

የማመንጫ ጣቢያዎች ጥገና በራስ አቅም መከናወኑ የሠራተኛውን ተነሳሽነት ጨምሯል ………///…….. የአዋሽ 2ኛ እና 3ኛ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የጥገና ሥራ በተቋሙ ሠራተኞች የራስ አቅም መከናወኑ ሠራተኛው በባለቤትነት መንፈስ እንዲሰራ እና አቅሙን አሟጦ እንዲጠቀም እንዳስቻለው የጣቢያዎቹ የጥገና ክፍል ሥራ አስኪያጅ ተናገሩ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ሮቤል አበበ እንደተናገሩት ማመንጫ ጣቢያዎቹ ከአቅማቸው በታች እንዳያመነጩ ለማድረግ የተለያዩ የጥገና ሥራዎች በራስ አቅም ተከናውነዋል፡፡ የጥገና ሥራው "አሴት ኮንትሮል" በሚባል ሲስተም በመታገዝ እያንዳንዱ ሥራ ተመዝኖ የሚከናወን ሲሆን ሲስተሙ ችግሮችን በማመልከት የጥገና ሥራዎች በወቅቱ እንዲከናወኑ እንደሚያግዝ ተናግረዋል፡፡ አቶ ሮቤል እንዳሉት የጀኔሬተር ማቀዝቀዣ ራዲያተር፣ የተለያዩ ፓምፖች እና ከጣቢያው በሚወጡ መስመሮች ላይ የተለያዩ ችግሮችን በራስ አቅም በመጠገን ችግሮችን መፍታት ተችሏል፡፡ ራዲያተሩ በራስ አቅም ባይጠገን ኖሮ የጣቢያው ዩኒቶች ከአቅማቸው በታች እንዲሰሩ ከማድረጉም በተጨማሪ ሙሉ በሙሉ ሥራ አስከማቆም ይደርሱ ነበር ብለዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ የአዋሽ ውሃ ድፍርስ በመሆኑ ወደ ራዲያተሩ የሚገባው ውሃ በራዲያተሩ ላይ ችግር እንዳይፈጥር እና ሌሎች ባዕድ የሆኑ ነገሮች እንዳይገቡ የሚያደርጉ የተለያዩ አሰራሮችን በራስ አቅም ተተግብረዋል፡፡ በጣቢያውዎቹ ላይ ብቃት ያላቸው ባለሙያዎችን ለማፍራት ልምድ ያላቸውን ከአዳዲስ ባለሙያዎች ጋር በማቀናጀት እንዲሰሩ እየተደረገ እንደሆነም አመልክተዋል፡፡ ጣቢያዎቹ ረጅም ጊዜ ያገለገሉ ቢሆንም ወቅቱን የጠበቀ የጥገና ሥራ ስለሚደረግላቸው በአሁኑ ወቅት እያንዳንዱ የጣቢያው ዩኒት ከ12 - 14 ሜጋ ዋት እያመነጨ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ ከጥገና ሥራዎች በተጨማሪ የሥራና የመኖሪያ አካባቢን ምቹ ለማድረግ የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አቶ ሮቤል አስታውቀዋል፡፡ የአዋሽ 2ኛ ማመንጫ ጣቢያ በ1958 ዓ.ም እንዲሁም የአዋሽ 3ኛ በ1963 ዓ.ም ወደ ኦፕሬሽን የገቡ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በጣቢያዎቹ ላይ 120 የሚጠጉ ቋሚና ጊዜያዊ ሠራተኞች ይገኛሉ፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 02 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+5

ወደ ኬንያ የተጀመረው ኃይል የማስተላለፍ ሥራ በሁለቱ ሀገራት ባለሙያዎች በትብብር እየተሰራ ነው ……….///………. የኢትዮ -ኬኒያ ኃይል የማስተላለፊያ መስመር ያለምንም ችግር አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ ከኬኒያ የኮንቨርተር ስቴሽን የኦፕሬሽን ባለሙያዎች ጋር በትብብር እየተሠራ መሆኑን የወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ስቴሽን የኦፕሬሽንና ጥገና ዳይሬክተር ገለፁ። ዳይሬክተሩ አቶ ሀብታሙ ግርማ እንደገለፁት በሁለቱ ሀገራት የሚገኙ የኮንቨርተር ስቴሽኖች የኦፕሬሽን ሥራ ያለምንም ችግር እንዲከናወን የሁለቱ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና የጥገና ባለሙያዎች በወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ስቴሽን የልምድ ልውውጥ ማካሄድ ጀምረዋል። የልምድ ልውውጡ የጥገናና የኦፕሬሽን ሥራውን በጋራ ማከናወን በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ትኩረት ማድረጉን አቶ ሀብታሙ ተናግረዋል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ የልምድ ልውውጡ ባለሙያዎቹ የኦፕሬሽን ሥራውን በተቀመጠው አሰራርና ስታንዳርድ መሠረት በኃላፊነት እንዲሰሩ ለማድረግ ጉልህ ፋይዳ አለው። የወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ስቴሽን ሜካኒካል ኢንጂነር መላኩ አግማስ በበኩላቸው የኮንቨርተር ስቴሽኑ የተገነባበት ቴክኖሎጂ አዲስ በመሆኑ የልምድ ልውውጡ ሊያጋጥም የሚችለውን የዕውቀት ክፍተት በመሙላት የኦፕሬሽን ሥራውን በአስተማማኝ መልኩ ለማከናወን ያግዛል ብለዋል። ከልምድ ልውውጡ ያገኙትን ዕውቀትና አዲስ የአሰራር ስርዓት ተግባራዊ በማድረ የኦፕሬሽን ሥራው ጤናማ በሆነ መልኩ እንዲከናወን ለማድረግ የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡም አረጋግጠዋል። በልምድ ልውውጡ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት በኬኒያ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኩባንያ - ኬትራኮ ባለሙያ እና የቡድኑ አስተባባሪ ቪክቶር አክቤት በበኩላቸው በተለያየ ጊዜ በሚከናወኑ የኢንስፔክሽንና የጥገና ሥራዎች ላይ የኢትዮጵያን ልምዶች መመልከታቸውን እና ከኢትዮጵያ ባለሙያዎች ያገኙት የአሰራር ልምድ በኦፕሬሽን ሥራው ላይ ለሚያከናውኑት ተግባር እንደሚያግዛቸው ተናግረዋል። ከዚህ በፊት የኩባንያቸው የባለሙያዎች ቡድን ተመሳሳይ የልምድ ልውውጦችን እንዳደረገ አስታውሰው በቀጣይ ሌላ ተጨማሪ የባለሙያዎች ቡድን ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት የልምድ ልውውጥ እንደሚያደርግ ገልፀዋል። በልምድ ልውውጡ ላይ የፍተሻ፣ የጥገናና የኦፕሬሽን ቁጥጥር ሥራ ስለሚከናወንበት መንገድ ለኬኒያ የባለሙያዎች ቡድን ገለፃ ተደርጎለታል፡፡ የልምድ ልውውጡን ለማጠናከር የወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ስቴሽን የኦፕሬሽንና ጥገና የባለሙያዎች ቡድን ወደ ኬኒያ በማምራት ከኬንያ አቻው ጋር የልምድ ልውውጦችን እንደሚያካሂድ ይጠበቃል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 01 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+6