ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 542 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 329 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 179 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 542 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 03 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 31، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 26.36‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.21‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 097 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 520 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 04 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 542
المشتركون
-124 ساعات
-167 أيام
+3130 أيام
أرشيف المشاركات
photo content
+3

ክለቡ በውድድር ዓመቱ ካደረጋቸው 18 ጨዋታዎች መካከል የተሸነፈው በአንድ ጨዋታ ብቻ ነው …….///…… ወደ ቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የተቀላቀለው ኢትዮ- ኤሌክትሪክ በውድድር ዓመቱ ካደረጋቸው 18 ጨዋታዎች መካከል 11 ጨዋታዎችን አሸንፎ፣ በስድስቱ አቻ በመውጣትና በአንድ ጨዋታ ብቻ በመሸነፍ ጠንካራ ተፎካካሪነቱን አሳይቷል፡፡ በአሰልጣኝ ክፍሌ ቦልተና መሪነት የ2014 ዓ.ም የከፍተኛ ሊግ ውድድሩን የተቀላቀለው አንጋፋው ኢትዮ ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን ከፍተኛ ትንቅንቅ የታየበትን ምድብ ሀ በመምራት 26 ጎሎችን አስቆጥሮ በ39 ነጥብ ሊጉን በመሪነት አጠናቋል፡፡ በ2010 ዓ.ም ከፕሪሚየር ሊግ ወደ ከፍተኛ ሊግ የወረደው አንጋፋው ክለብ ከ4 የውድድር ዘመን በኋላ ዋንጫ በማንሳት ጭምር ያለመውን ማሳካት ችሏል፡፡ በአጠቃላይ በዓመቱ 18 ጨዋታዎችን ያደረገው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ11 ጨዋታዎች አሸንፎ፣ በስድስቱ አቻ ወጥቶ በአንድ ጨዋታ ብቻ ተሸንፎ በ39 ነጥብ ሊጉን በመሪነት አጠናቋል፡፡ አንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ምንያህል ተሾመን ጨምሮ እንደ ፀጋ ደርቤ እና ኢብራሂም ከድር ያሉ ተስፈኛ ወጣቶችን አሰባጥሮ ወደ ውድድር የገባው ኢትዮ ኤሌክትሪክ (ኮረንቲ) የተጫዋቾችን የልምድ ሚዛን ጠብቆ በመጓዝ ለድል ሊበቃ ችሏል፡፡ ከሻምፒዮንነቱ ባሻገር ኮከብ አሰልጣኝ፣ ኮከብ ጎል አግቢ እና ኮከብ ግብ ጠባቂ በማስመረጥ በውድድር ዓመቱ ድርብርብ ውጤት አስመዝግቦ ታሪካዊ አሻራ ማሳረፍ ችሏል፡፡ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ባለፉት የእግር ኳስ ዘመናት እንደ ፈቃደ ሙለታ፣ ቅጣው ሙሉ፣ ጠንክር አስናቀ፣ ዮርዳኖስ ዓባይ፣ ሲሳይ ተሰማ፣ ኤሊያስ ጁሀር እና አንዋር ሲራጅ ያሉ አይረሴ ተጫዋቾችን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በማበርከት የሀገር አለኝታነቱን ያስመሰከረ የ60 ዓመት ታሪክ ያለው ክለብ ነው፡፡ ክለቡ በተጫዋቾች ብቻ ሳይሆን ታማኝ ደጋፊዎችን በማፍራት የሚታወቅ ሲሆን ዋንጫውን በተረከበበት ወቅት አሁን በህይወት ለሌሉትና በክለቡ የደጋፊዎች ታሪክ ሁሌም ለማይረሱት ነፍስሔር ሐጂ ኑር ሁሴን እና ነፍስሔር በቀለ ኮረንቲ የአንድ ደቂቃ የመታሰቢያ ፀሎት በማድረግ አስቧቸዋል፡፡ የኢትዮ- ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን ወደ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን ተከትሎ ትናንት ምሽት በስካይ ላይት ሆቴል ለተጫዋቾቹና ለክለቡ አባላት ዕውቅና እና ሽልማት ሰጥቷል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 30 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content

ለኢትዮ - ኤሌክትሪክ የእግርኳስ ክለብ የዕውቅና እና ሽልማት መርሐግብር ተካሔደ ……..////………. የኢትዮ- ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን ወደ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን ተከትሎ ትናንት ምሽት በስካይ ላይት ሆቴል የዕውቅና እና ሽልማት መርሐግብር ተካሒዷል። በመርሐ-ግብሩ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የክለቡ ፕሬዝዳንት አቶ ጫላ አማን ክለቡ ወደ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዳግም መመለሱ እንዳስደሰታቸው ገልፀዋል። ክለቡ በቀጣይ ዓመት ጠንካራና ፈታኝ የውድድር ጊዜ እንደሚጠብቀው የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ ለውጤታማ ጉዞው ከወዲሁ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት መጀመር እንዳለባቸው አሳስበዋል። የሁለቱ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች፣ የስፖርት ማህበሩ አባላት እንዲሁም መላው የስፖርት ቤተሰብ ለክለቡ ስኬታማነት ያደረጉት አስተዋጽኦ ትልቅ ድርሻ ያለው መሆኑን አውስተው ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በ1953 ዓ.ም የተመሰረተው የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ በአሁኑ ሰዓት ከ337 በላይ ስፖርተኞችን በተለያዩ ዘርፎች እያሰለጠነ እንደሚገኝ አቶ ጫላ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ በበኩላቸው እግር ኳስ ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚ መገንባት ያለው ፋይዳ የጎላ መሆኑን ጠቅሰው ክለቡ ዳግም ወደ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መመለሱ እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል። ክለቡ በቀጣዩ ዓመት በፕሪሚየር ሊጉ ተፎካካሪ ለመሆን ትልቅ የቤት ሥራ ስለሚጠብቀው ከወዲሁ ጠንክሮ መስራት እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል። በመርሐ-ግብሩ ለክለቡ ውጤት ማደግ አስተዋፅኦ ላደረጉ ተጨዋቾችና የስፖርት ክለቡ አባላት ዋንጫና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል። ቡድኑ አንድ ጨዋታ እየቀረው ፕሪሚየር ሊጉን መቀላቀል በመቻሉ 11 ሚሊዮን ብር ለተጨዋጮችና ድጋፍ ሰጪ አባላትም ተበርክቷል። የስፖርት ክለቡ ውጤት እንዲያመጣ የክትትልና ድጋፍ አስተዋፅኦ ላደረጉት የሁለቱ ተቋማት ዋና ሥራ አስፈፃሚዎችም ሽልማት ተሰጥቷል። ክለቡ በ2014 ዓ.ም የብሔራዊ ሊግ ሻምፒዮን ሆኖ ያገኘውን ዋንጫ ተጨዋቾች፣ አሰልጣኙና ፕሬዝዳንቱ በጋራ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚና ለስፖርት ክለቡ ጠቅላላ ጉባዔ ሰብሳቢ አቶ ሽፈራው ተሊላ አስረክበዋል። በዕውቅና እና ሽልማት መርሐግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያን ጨምሮ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ እና የከፍተኛ የሥራ አመራሮች፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የኢትዮ- ኤሌክትሪክ የእግር ኳስ ክለብ ከ4 ዓመት የከፍተኛ ሊግ ቆይታ በኋላ ድጋሚ ወደ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ማደጉን ከዚህ በፊት መዘገባችን ይታወሳል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 30 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+8

የሱልልታ -ደብረ ማርቆስ መስመር ጥገና ተጠናቀቀ ………////……... በመሬት መንሸራተት የተነሳ ጉዳት ደርሶበት የነበረው የሱልልታ -ደብረ ማርቆስ ባለ 400 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማ
የሱልልታ -ደብረ ማርቆስ መስመር ጥገና ተጠናቀቀ ………////……... በመሬት መንሸራተት የተነሳ ጉዳት ደርሶበት የነበረው የሱልልታ -ደብረ ማርቆስ ባለ 400 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ተጠናቀቀ። ለጥገና ሥራው ሲባል ብሔራዊ የኃይል ግሪድ ለሁለት ተከፍሎ ከመጋቢት 20 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ጥገናው ሲከናወን ቆይቷል። በዚህም በግሪዱ ላይ የደረሰው ጫና ከ 4 በመቶ ሳይበልጥና የጎላ የኃይል መቆራረጥ ሳያጋጥም ዛሬ የጥገና ሥራው ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል። ጥገናው በተቋሙ የራስ ኃይል የኮንስትራክሽን ቢሮ ስምንት ሚሊየን ብር በጀት ተይዞለት የተሰራ ሲሆን በውጭ ሀገር ተቋራጭ ቢሰራ ከአንድ ሚሊየን ዶላር ወይም ወደ ሃምሳ ሚሊየን ብር ይጠይቅ እንደነበር ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል። የጥገና ሥራው እስኪጠናቀቅ ድረስ ያጋጥመውን ችግር ታግሳችሁ በትዕግስት ለጠበቃችሁን ደንበኞቻችን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምስጋናውን ያቀርባል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 27 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+2

ከአዋሽ 2 ወደ አሰላ የተዘረጋው መስመር በተፈፀመበት ዝርፊያ ኤሌክትሪክ በከፊል ተቋርጧል ………///………. ከአዋሽ 2 ወደ አሰላ የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ ትናንት መጋቢት 24 ቀን 2014 ዓ.ም ዝርፊያ ተፈጽሟል፡፡ በዶዶታ ወረዳ እና ጌራ ከተማ አቅራቢያ በተፈፀመው የምሰሶ አካላት ዝርፊያ ሁለት ምሰሶዎች በመውደቃቸው የተነሳ አሰላ ከተማን ጨምሮ በዙሪያው ባሉ አካባቢዎች በከፊል ኤሌክትሪክ ተቋርጧል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጥገና ቡድን ዝርፊያ ወደተፈፀመበት አካባቢ የተንቀሳቀሰ ሲሆን ጥገናውን በፍጥነት ለመጀመር የሚያስችል አሰሳ እያካሄደ ነው፡፡ ጥገናው ከሳምንት ያላነሰ ጊዜ ሊወስድ እንደሚችል ተገምቷል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ዝርፊያ እየተደጋገመ ሲሆን ይህም ለኃይል መቋረጥ ምክንያት እየሆነ ነው፡፡ በመሆኑም ህብረተሰቡ በኤሌክትሪክ መሰረተልማት ላይ ዝርፊያ የሚፈጽሙ ግለሰቦችን ሲመለከት በአቅራቢያው ለሚገኙ የፀጥታ አካላት እንዲያሳውቅ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያሳስባል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 25 ቀን 2014 ዓ/ም

የሱልልታ -ደብረ ማርቆስ መስመር የጥገና ሥራ በብሔራዊ ግሪድ ላይ የጎላ ተጽዕኖ ሳያሳድር እየተገባደደ ነው ………////……... የሱልልታ -ደብረ ማርቆስ ባለ 400 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር የጥገና ሥራ በብሔራዊ የኃይል ቋት ወይም ግሪድ ላይ የጎላ ተጽዕኖ ሳያሳድር እየተገባደደ ነው። ከማክሰኞ መጋቢት 20 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ጥገናው እየተከናወነ የሚገኘው የሱልልታ -ደብረ ማርቆስ _ ባህርዳር መስመር እና የምሰሶ ጥገና ሥራ በተያዘለት መርሃግብር መሰረት እየተከናወነ ይገኛል፡፡ በጥገና ሥራው የተነሳ በግሪድ ላይ የደረሰው ጫና ከ 4 በመቶ ያልበለጠ መሆኑን ከቀናት በፊት መዘገባችን ይታወሳል፡፡ የተጀመረው እና 5 ቀኑን ያስቆጠረው የጥገና ሥራን በ7 ቀን ሰርቶ ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል። በአሁኑ ሰዓት በመሬት መንሸራተት ምክንያት የተጎዱ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎችን መልሶ የመትከል ሥራው የተጠናቀቀ ሲሆን የመስመር ዝርጋታና የማገናኘት ሥራ እየተሰራ ነው። የጥገና ሥራውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል የኮንስትራክሽን ቢሮ ሲሆን ቢሮው አዳዲስ የማከፋፈያ ጣቢያና ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክቶችን ከመገንባት ጀምሮ የጥገና ሥራዎችን ይገኛል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከሱሉልታ - ደብረ ማርቆስ በተዘረጋው ባለ 400 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች በአባይ ሸለቆ እና ሉማሜ ወረዳ ውስጥ በመሬት መንሸራተት የተነሳ መጎዳታቸው የሚታወስ ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 25 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+9

photo content
+3

ፎቶ ዜና
+9
ፎቶ ዜና

photo content
+1

የኢትዮ ኤሌክትሪክ የእግር ኳስ ክለብ ባቱ ከነማን በማሸነፍ የከፍተኛ ሊግ ሻምፒዮን ሆነ ……..///…….. አስቀዶሞ ወደፕሪሚየር ሊጉ መቀላቀሉን ያረጋገጠው አንጋፋው የኢትዮ ኤሌክትሪክ የእግር ኳስ ስፖርት ክለብ የ2014 ዓ.ም. የከፍተኛ ሊግ ሻምፒዮን የመጨረሻ ጨዋታውን በድል አጠናቋል፡፡ በ2014 ዓ.ም የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የምድብ ሀ ሻምፒዮኑ ኢትዮ ኤሌክትሪክ በባህር ዳር ስታዲየም ከባቱ ከነማ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 2 ለ 0 በማጠናቀቅ የከፍተኛ ሊግ ሻምፒዮንነት ዋንጫውን ተረክቧል፡፡ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከእረፍት በፊት በሁለተኛው እና በ14ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች 2ለ0 ጨዋታውን አጠናቋል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ2014 የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ሻምፒዮን በመሆን የ2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ ቤት ኪንግ ፕሪምየር ሊግ ን ከተቀላቀሉት ሦስት ክለቦች አንዱ በመሆን ከአራት ዓመት በኋላ ወደ ፕሪምየር ሊጉ ተመልሷል። ኢትዮጵያ መድን እና ለገጣፎ ለገዳዲም የ2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ ቤት ኪንግ ፕሪምየር ግን የተቀላቀሉ ሌሎች ክለቦች ሆነዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ኢትዮ ኤሌክትሪክ የእግር ኳስ ስፖርት ክለብ 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በሚያከብርበት ጊዜ ላይ ወደ ፕሪሚየር ሊግ ተመልሶ በማደጉ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል፡፡ የስፖርት ክለቡ ፕሬዝዳንት አቶ ጫላ አማን በበኩላቸው ክለቡ የ2014 የከፍተኛ ሊግ ሻምፒዮን በመሆኑ እንኳን ደስ አለን ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 23 ቀን 2014 ዓ/ም

የተቋሙ የህፃናት ማቆያ ማዕከል ግንባታ ተጠናቆ በይፋ ተመረቀ …….////…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መሰሪያ ቤት የተገነባው የህፃናት የቀን ማቆያ ማዕከል/ Children Day Care Center/ ዛሬ በይፋ ተመረቀ፡፡ ማዕከሉን በይፋ የመረቁት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት የተቋሙ ሴት ሠራተኞች በስራቸው ውጤታማ እንዲሆኑ ለማድረግ የማዕከሉ መገንባት ከፍተኛ እገዛ ያድርጋል፡፡ በቀጣይም ለማዕከሉ የሚያስፈልጉ ቀሪ ግብዓቶችን በአፋጣኝ አሟልቶ በቅርቡ ሥራ ለማስጀመር ትኩረት ተሰጥቶት እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች፣ ወጣቶችና ህፃናት ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ በበኩላቸው እንደገለፁት ሴት ሠራተኞች ከወሊድ በኋላ ወደ ስራ ገበታቸው ሲመለሱ ስራቸውን በትጋት እንዲሰሩ እና በልጆቻቸው ምክንያት ከስራ ገበታቸው እንዳይቀሩና እንዳያረፍዱ ያግዛል፡፡ ሠራተኞቹ የልጆቻቸን ጤናና ደህንነትለመከታተልም የህፃናት ማቆያ ማዕከሉ አይተኛ ሚና እንደሚጫወት ገልፀዋል፡፡ ማእከሉ ዕድሚያቸው ከ6 ወር አስከ አራት ዓመት የሚደርሱ ከአርባ እስከ ሃምሳ የሚሆኑ ህጻናትን ተቀብሎ የማስተናገድ አቅም እንዳለው የጠቆሙት ዳይሬክተሯ በሚቀጥለው ሳምንት በጊዚያዊነት ስምንት ህጻናትን ተቀብሎ ስራ እንደሚጀምር ተናግረዋል፡፡ ግንባታውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ አቅም የስራ ክፍል ማከናወኑ ተገልጿል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የስራ መሪዎች ‹‹ለሥርዓተ-ጾታ እኩልነት የመሪዎች ሚና ›› በሚል ርዕስ የፓናል ወይይት በዛሬው ዕለት አካሂደዋል ፡፡ የፓናል ውይይቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች፣ ወጣቶችና ህፃናት ጉዳይ መምሪያ ከኢትዮጵያ ሴቶች የኢነርጂ ባለሙያዎች ማህበር (Ethiopian woman in energy association ) ጋር በመተባበር መዘጋጀቱ ተገልጿል፡፡ የፓናል ውይይቱን በንግግር የከፈቱት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች፣ ወጣቶችና ህፃናት ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ እንደተናገሩት በተቋሙ በአሁኑ ወቀት በሥርዓተ-ጾታ እኩልነት ዙሪያ ያለውን ክፍተት በመለየት እና መፍትሄ ለማምጣት የከፍተኛ የስራ መሪዎች ሚና ወሳኝ በመሆኑ ይህ የውይይት መድረክ መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሴቶች የኢነርጂ ባለሙያዎች ማህበር ተጠባባቂ ፕሬዜዳንት ወ/ሮ ልእልና ክፍሌ በበኩላቸው የውይይት መድረኩ የሥርዓተ- ጾታ እኩልነት ለማረጋገጥ የስራ መሪዎች ሚና ምንመሆን እንዳለበት የሚጠቁምና ችግሮችን ለመቅረፍ ምን መስራት ይገባል የሚለውንላይ ግንዛቤ ለመፍጠር ይረዳል ብለዋል፡፡ በፓናል ወይይቱ ላይ ተቋሙ በሥርዓተ-ጾታ እኩልነት ዙሪያ እየሰራቸው ያሉ ጉዳዮች ተነስተው ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡ በመድረኩ የተቋሙ ከፍተኛ የስራ መሪዎችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ህግ ሴቶች ማህበር ፣የዓለም ባንክ እና የኢትዮጵያ ሴቶች የኢነርጂ ባለሙያዎች ማህበር ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 23 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+6

የሰሜን ምስራቅ አካባቢ የኦፕቲካል ፋይበር መስመሮች ጥገና ተጠናቀቀ ………////……… በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ህወኃት በከፈተው ጦርነት ከፍተኛ ውድመት አጋጥሞ የነበረውን የከፍተኛ ኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮች እና የኦፕቲካል ፋይበር ገመዶች የመጠገን ሥራ ተጠናቀቀ፡፡ ከደብረሲና - ሸዋሮቢት - ከሚሴ - ኮምቦልቻ - አቀስታ - ዓለም ከተማ ባለ132 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ፤ ከደብረብርሃን - ኮምቦልቻ - ሠመራ እና ከኮምቦልቻ - አላማጣ እስከ ቆቦ ድረስ ባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመር እንዲሁም ከደብረታቦር እስከ ጋሸና ባለ 230 ኪ.ቮ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር በሚያልፍበት አካባቢ የሚገኙ ከተሞችና መንደሮች ላይ ከህዳር 24 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ በተደረገው ጥገና አካባቢዎቹ ኤሌክትሪክ መልሰው እንዲያገኙ መደረጉ ይታወሳል፡፡ በተያያዘም ከደሴ - ወልዲያ የ ባለ66 ኪሎ ቪልት መስመር ጥገና በማካሄድ የወልዲያ እና አካባቢው ከተሞች ኃይል እንዲያገኙ ተደርገዋል፡፡ የመልሶ ጥገና ሥራውን ከተቋሙ ስምንት ሪጅኖች እንዲሁም ከተቋሙ የራስ ኃይል የተውጣጣ የጥገና ቡድን በከፍተኛ ርብርብ ሲያከናውን ቆይቷል፡፡ ይሁንና ህብረተሰቡ ለበርካታ ሳምንታት እና ወራት በጭለማ ውስጥ እንዳይቆይ ለማድረግ ሲባል የኦፕቲካል ፋይበር መስመር ጥገናው በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ለተወሰኑ ሰዓታት ኤሌክትሪክ በማቋረጥ ሲሰራ ቆይቶ ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ተጠናቋል፡፡ በቀጣይ መስመሩ አገልግሎት እየሰጠ ችግሮች ቢገጥሙት ችግሮቹን የሰሜን ምስራቅ ሪጅን የጥገና ቢሮ እንዲፈታው እና እንደሚከሰተው ችግር ስፋት ደግሞ እገዛ በሚያስፈልገው ቦታ ላይ ከማዕከል የሚንቀሳቀስ የቴክኒክ ድጋፍ ቡድን እገዛ እንዲያደርግ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡ በአማራና አፋር ክልል የደረሰውን የኤሌክትሪክ መሰረተልማት ለመጠገን ለመለዋወጫ አቅርቦት የወጣውን ወጪ ሳይጨምር ለሥራው ብቻ ከ6 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ተደርጓል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 23 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+3

የሱሉልታ - ደብረ ማርቆስ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊ መስመር እየተጠገነ ነው ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከሱሉልታ - ደብረ ማርቆስ በተዘረጋው ባለ 400 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ በአባይ ሸለቆ ውስጥ በመሬት መንሸራተት የተነሳ የደረሰበትን ጉዳት የመጠገን ስራ እየተከናወነ ነው። ከማክሰኞ መጋቢት 20 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በመካሄድ ላይ ያለው የከፍተኛ ቮልቴጅ መስመር ጥገና ለሰባት ቀናት ኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦ የሚከናወን ቢሆንም በርካታ አካባቢዎች ኃይል እንዳያጡ ለማድረግ ግሪዱ ለሁለት ተከፍሎ አገልግሎት እንዲሰጥ እየተደረገ ይገኛል። በጥገና ሥራው የተነሳ በግሪዱ ላይ የደረሰው ጫና ከ 4 በመቶ ያልበለጠ ሲሆን ይህም የግሪድ ሲስተሙ የተረጋጋ እንዲሆንና ያልተቆራረጠ ኃይል ለህብረተሰቡ ለማቅረብ እንደሚያስችል ይታመናል። ይሁንና ግሪዱ ለሁለት ተከፍሎ በመስራቱ የተፈጠረው ጫና አነስተኛ ቢሆንም በአንዳንድ አካባቢዎች ከስርጭት መስመሮች መቋረጥ ጋር ተያይዞ የሲስተም አለመረጋጋትና በአንዳንድ አካባቢዎች የኃይል መቆራረጥ መኖሩን ተረድተናል። ስለሆነም የጥገና ሥራው እስኪጠናቀቅ ድረስ የሚኖረውን የኃይል መቋረጥ የቆይታ ጊዜ ለመቀነስ ሰፊ ሥራዎች እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ በመሆኑም ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞቻችን ይህንን ተገንዝባችሁ የተጀመረው የጥገና ስራ እስከሚጠናቅቅ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን እናሳስባለን። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 22 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content