ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 543 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 332 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 157 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 543 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 27 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 10، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -16، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 25.06‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.33‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 895 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 539 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 7.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 28 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 543
المشتركون
-1624 ساعات
-97 أيام
+1030 أيام
أرشيف المشاركات
ጣቢያው ከ 28 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል ……….///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአሸጎዳ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 28 ነጥብ 565 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ካህሰ ፀሐይ እንደገለፁት የኃይል ማመንጫ ጣቢያው በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 45 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማመንጨት አቅዶ የነበረ ቢሆንም ማሳካት የቻለው የዕቅዱን 63 ነጥብ 47 በመቶ ነው። አፈጻጸሙ ከእቅዱ አንጻር ያነሰው ለረጅም ጊዜ ሥራ አቁመው የነበሩ ተርባይኖችን ጠግኖ ወደ ሥራ ለማስገባት በቂ የጥገና ባለሙያና መለዋወጫ ባለመኖሩ እንዲሁም ተርባይኖችች ለረጅም ጊዜ ሳይሰሩ በመቆየታቸው ምክንያት ተጨማሪ ቴክኒካል ችግር ይዘው በመገኘታቸው ነው ብለዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ጣቢያው ካሉት 84 ተርባይኖች አሁን ላይ 25 ተርባይነችን ወደ ሥራ ማስገባት ተችሏል። ተቋሙ የመለዋወጫ ችግሩን ለመፍታት እና ኤ ኤፍ ዲ ከተባለ የፈረንሳይ ተቋም ጋር በመነጋገር ሙሉ ተርባይኖችን ወደ ሥራ ለማስገባት በሂደት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱ ቀሪ ወራት ተጨማሪ ተርባይኖች ወደ ሥራ ስለሚገቡ የነበሩ እጥረቶችን በማረም የታቀደውን ዓመታዊ የኃይል ምርት ለማሳካት ርብርብ እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡ 30 ባለ ሁለትና 54 ባለ ሶስት ክንፍ በድምሩ 84 ተርባይኖች ያሉት የአሸጎዳ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ 120 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 03 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1445ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል በሠላም አደረሳችሁ! በዓሉ የጤናና የደስታ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል "ንፁህ ኢነ
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1445ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል በሠላም አደረሳችሁ! በዓሉ የጤናና የደስታ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 01 ቀን 2016 ዓ.ም

የተቋሙ ሠራተኞችና አመራሮች ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ሰራተኞች ማዕድ አጋሩ ………..///………. በነገው ዕለት የሚከበረውን የዒድ አልፈጥር በዓል ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የእስልምና እምነት ተከታይ የሆኑ 36 የተቋሙ ሴት የፅዳት ሠራተኞች ማዕድ አጋርተዋል። ማዕድ በማጋራት ሥነስርዓቱ ላይ በመገኘት ስጦታ ለሠራተኞቹ የተዘጋጀውን ስጦታ ያበረከቱት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ናቸው፡፡ የዒድ አልፈጥር እና የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ሴት ሠራተኞች ማዕድ ለማጋራት ከተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ገንዘብ የማሰባሰብ ሥራ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ሲከናወን መቆየቱን የገንዘብ አሰባሳቢ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ አብደላ ሻንቆ ተናግረዋል። ስጦታው እስከተከናወነበት ሰዓት ድረስም 173 ሺህ 260 ብር መሰብሰቡን ሰብሳቢው ጠቁመዋል። ከዚህ ውስጥ በዛሬው ዕለት የእስልምና እምነት ተከታይ ለሆኑ 36 የተቋሙ ሴት የፅዳት ሠራተኞች ለእያንዳንዳቸው የ1500 ብር የዓይነትና የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ ተደርጓል። በተቋሙ ሠራተኞችና አመራሮች የተጀመረው ማዕድ የማጋራት ሥራ አስተባባሪ ከተገኘ ሠራተኛው በተለያዩ ማህበራዊ ችግሮች ላይ ተሳትፎውን በማጎልበት ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ዝግጁ ስለመሆኑ ትምህርት ተገኝቶበታል ብለዋል። ሠራተኛው እያደረገ ያለውን ድጋፍ አመስግነው በቀጣይ መሠል ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። ከሳምንታት በኋላ ለሚከበረው የትንሳዔ በዓል ለኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ተመሳሳይ ድጋፍ ለማድረግ ገንዘብ የማሰባሰቡ ሥራ እንደቀጠለ እና ሁሉም ሠራተኛ በበጎ አድራጎት ሥራው ላይ በመሳተፍ ማህበራዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣም ጥሪ አቅርበዋል። ድጋፍ የተደረገላቸው ሠራተኞች በበኩላቸው የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች በአሁኑ ወቅት ያለውን የኑሮ ሁኔታ ተረድተው ላደረጉት ድጋፍ አመስግነዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 01 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

ተቋሙ ከአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችለው ስምምነት ተፈራርመ ……..//………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ በከፍተኛና መካከለኛ አመራር ልማት ዙሪያ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱን የፈረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ናቸው። በመግባቢያ ስምምነቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት ተቋሙ የተጣለበትን ሀገራዊ ተልዕኮ በብቃት ለመወጣትና በኃይል ዘርፍ ሥር ነቀል ለውጥ ለማምጣት የሚያስችል አመራር መፍጠር ያስፈልጋል፡፡ የኃይል ዘርፉ ከፍተኛ የመሪነት አቅምን የሚጠይቅ በመሆኑ የመግባቢያ ስምምነቱ ብቁ አመራር በመፍጠር በአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕል ለመሆን የያዝነውን እቅድ ከግብ በማድረስ በኩል ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡ አሁን ላይ ተቋሙ የሀገር ውስጥ የኃይል ፍጆታን በመሸፈን የጎረቤት ሀገራትን በኃይል እያስተሳሰረ መሆኑን የገለጹት ዋና ሥራ አስፈጻሚው በኃይል ዘርፉ ብቁ የሆነ የልህቀት ማዕከል ለመገንባት ተቋሙ የያዘውን ዕቅድ ወደ መሬት ለማውረድ የመግባቢያ ስምምነቱ እንደሚረዳ ገልፀዋል። የመግባቢያ ስምምነቱን ወደ መሬት በማውረድ በአጭር ጊዜ በኃይል ዘርፍ ለተሻለ ውጤት የሚተጋ አመራር እንደሚፈጥር እምነታቸው መሆኑን ኢንጂነር አሸብር ገልጸዋል። የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሀገራችን በኃይል ራሷን እንድትችል ከማድረግ ባሻገር ለጎረቤት ሀገራት በመሸጥ የውጭ ምንዛሬን እያስገነ ያለ ተቋም መሆኑን ጠቁመዋል። የተቋማቱ ግንኙነት የቆየ ቢሆንም ባለፉት አራት ወራት ከሁለቱም ተቋማት የተውጣጣ ቡድን በጋራ ለመስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ሲያደረግ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ የመግባቢያ ስምምነቱ ሀገሪቱ በዘርፉ ያላትን እምቅ አቅም አሟጦ በመጠቀም ወደ ሀብት መቀየር የሚችል ብቁና ጠንካራ አመራሮችን ለማፍራት የሚረዳ መሆኑን የገለጹት አቶ ዛዲግ ስምምነቱ ሁለቱ ተቋማት በአመራር ልማት፣ በአመራር ዕውቅና አሰጣጥና በሃሳብ ማበልጸጊያ ማዕከል ግንባታ ዙሪያ በትብብር ለመስራት የሚያስችላቸው እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡ አካዳሚው የተፈረመውን የመግባቢያ ስምምነት ወደ ተግባር በመቀየር በዘርፉ ያለውን የአመራር አቅምን በቀጣይነት ለማሳደግ እንደሚሠራ አረጋግጠዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 01 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

photo content
+8

ስለ ጣቢያው አሠራርና ቴክኖሎጂ ማወቅ ለጣቢያው ተገቢውን እገዛ ለማድረግ ያስችላል ………..///……… በወላይታ ሶዶ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ኮንቨርተር ጣቢያ ላይ የሚደረጉ ጉብኝቶች የጣቢያውን ሠራተኞችን የሥራ ተነሳሽነት እንደሚያሳድጉት የጣቢያው ኃላፊና ሠራተኞች ተናገሩ። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች ጣቢያውን ጎብኝተዋል፡፡ የኮንቨርተር ጣቢያው ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ግርማ እንደተናገሩት ጉብኝቱ በስራ ሂደት ላይ ከኦፕሬሽን እና ከአስተዳደር ጋር በተያያዘ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለሚመለከተው አካል በቀላሉ ለማሳወቅ እና ችግሮች የሚፈቱበትን መንገድ ለማመቻቸት ዕድል ይፈጥራል። ጉብኝቱ ጣቢያው ስለሚጠቀመው እና ልዩ ስለሚያደርገው ቴክኖሎጂ ለማስተዋወቅ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ የተቋሙ ሠራተኞች ስለ ቴክኖሎጂው ያላቸው ግንዛቤ በማሳደግ የሠራተኛውን የሥራ ተነሳሽነት እንደሚጨምር አመልክተዋል። በጣቢያው የኦፕሬሽንና የጥገና ባለሙያ አቶ ዓለሙ አድማስ በበኩላቸው ጉብኝቱ የተቋሙ ማህበረሰብ ለጣቢያው የሰጡትን ትኩረት ለማወቅ ያግዛል። የጥገናና የኦፕሬሽን ሥራውን ለማስቀጠልና የዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲኖር ለማድረግ የተቋሙ ማህበረሰብ ስለ ጣቢያው አሠራርና ስለሚጠቀመው ቴክኖሎጂ ማወቅ እንደሚጠበቅበት ባለሙያው አመልክተዋል። በጉብኝቱ ላይ ከተሳተፉት መካከል የሰሜን ሪጂን የማስተላለፊያ መስመሮችና ፋይበር ኦፕቲክስ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ህንፃ አረጋዊ እንዲህ ዓይነት ጣቢያ ጎብኝተው እንደማያውቁ ገልፀው በጉብኝቱ ከተደረገው ገለፃ ስለ ቴክኖሎጂው ግንዛቤ ማግኘታቸውን እና ጣቢያው ከሌሎቹ የተለየ ትኩረት እንደሚፈልግ መረዳታቸውን ተናግረዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 01 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ተቋማቱ አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ዛሬ ይፈራረማሉ …….//………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት በዛሬው ዕለት እንደሚፈራረሙ የተቋሙ የስልጠናና የሰው ሀብት ልማት መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር )እንደገለጹት የመግባቢያ ስምምነቱ ብቁ ተቋማዊ አመራርን ለመፍጠር የሚያስችል ነው ተብሏል። የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የሀገሪቱን የአመራር አቅም የማሳደግ ተልዕኮውን በአግባቡ መወጣት እንደሚያስችለው የጠቆሙት ኃላፊው ስምምነቱ የጋራ ተልዕኳቸውን እንዲያሳኩ እንደሚያስችላቸው ጠቁመዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 01 ቀን 2016 ዓ.ም

ተቋሙ የኢፍጣር መርሃ ግብር አካሄደ .......////.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የረመዳን ፆምን ምክንያት በማድረግ የእስልምና እምነት ተከታይ ለሆኑ የተቋሙ ሠራተኞች፣ ደንበኞች እና ባለድርሻ አካላት በስካይ ላይት ሆቴል የኢፍጣር ወይም የእራት ግብዣ መርሃ ግብር አካሄደ። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በአንድነት የእራት ግብዣ መርሃ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የረመዳን ጾም ሙስሊሙ ማህበረሰብ ሥጋዊ ፍላጎትን በመንፈሣዊ ፅናት በማሸነፍ ራሱን ለፈጣሪ ማስገዛት የህይወት መመሪያው የሚያደርግበት ወር መሆኑን አንስተዋል። የተዘጋጀው መርሃግብር እንደ ኢትዮጵያውያን ወግና ባህል ማዕድን በጋራ በመቋደስ ስለስኬቶቻችን፣ ስለወደፊት መዳረሻዎቻችን እና ስለፈተናዎቻችን ለመነጋገር ታስቦ መሆኑን ሥራ አስፈፃሚው ጠቅሰዋል። ከአምስቱ የእስልምና እምነት መሠረቶች መካከል አንዱ የሆነው ፆም የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት ከአላህ እዝነት ለማግኘት ትልቅ ጥረት የሚደረግበት እንደሆነም ነው የገለፁት። ተቋሙ በህዝብና በመንግሥት የተሰጠውን ተልዕኮ በብቃት ለመወጣት ከምንጊዜውም በላይ እየሰራ ነው ያሉት ሥራ አስፈፃሚው የህዝቡን፣ የደንበኞችንና የሀገርን ፍላጎት ማርካት የሚያስችሉ ዕቅዶች አዘጋጅቶ በትግበራ ላይ መሆኑን ተናግረዋል። ስለሆነም የተቋሙን ራዕይ ለማሳካት ሁሉም የተቋሙ ሠራተኛ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪያቸውን አቅርበዋል። ለእስልምና እምነት ተከታዮችም ለ1445ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል። በኢፍጣር መርሃግብሩ ላይ የታደሙት የተቋሙ አመራርና ሠራተኞች በበኩላቸው በዝግጅቱ መደሰታቸውንና የእኔነት ስሜት እንደፈጠረባቸው ገልፀዋል። እንደዚህ ዓይነት መርሃ ግብሮች በቀጣይም ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ በማንሳት ለተደረገላቸው የአንድነት የእራት ግብዣ ተቋሙንና ዋና ሥራ አስፈፃሚውን አመስግነዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢ/ር አሸብር ባልቻን ጨምሮ የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፣ ደንበኞችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ታድመዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ሚያዚያ 01 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

photo content
+9

photo content
+9

የደጀን ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የፍተሻ ሥራ በቅርቡ ይጀመራል ……..///……… የደጀን ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የፍተሻ ሥራ በቅርቡ እንደሚጀመር በፕሮጀክቱ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች አስተባባሪ ገለጹ፡፡ አስተባባሪው አቶ ተስፋሚካኤል አሰፋ እንደገለጹት በግንባታ ላይ የሚገኘው የደጀን የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ 90 ሜጋ ዋት የመሸከም አቅም ያላቸው አንድ ባለ 63 እና አንድ ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመሮች አሉት፡፡ አምስት ባለ 33 እና አምስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ያሉት የማከፋፈያ ጣቢያው የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራ ከ87 በመቶ በላይ እንደተጠናቀቀና በዕቃ አቅርቦት ችግር ምክንያት ያልተከናወኑ ቀሪ ሥራዎች ከፍተሻ ሥራው ጎን ለጎን እንደሚከናወኑም አስተባባሪው ጠቁመዋል፡፡ የጣቢያው የፍተሻ ሥራ በቅርቡ እንደሚጀመር ያነሱት አቶ ተስፋሚካኤል የግንባታና የፍተሻ ሥራዎችን በተያዘው የበጀት ዓመት ሙሉ በሙሉ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ የፕሮጀክቱ ሲቪል ሥራዎች የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ሚሊዮን ታምራት በበኩላቸው 83 በመቶ የሚሆነው የስዊችያርድ የሲቪል ግንባታ ሥራ የተጠናቀቀ ሲሆን የመኖሪያ ቤት ግንባታን ጨምሮ የማከፋፈያ ጣቢያው አጠቃላይ የሲቪል ሥራ 65 በመቶ ላይ ደርሷል፡፡ የስዊችያርድ አጥር፣ የውጭ ተፋሰስ፣ የመኖሪያ ቤት ግንባታና የጣቢያው የውስጥ ለውስጥ መንገድ ሥራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ያነሱት ሥራ አስኪያጁ ስዊችያርዱን ጠጠር የማልበስ እና ማከፋፈያ ጣቢያውን ከዋናው መንገድ የሚያገናኝ የ1 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት መንገድ ግንባታ ሥራዎች በቀጣይ እንደሚከናወኑ አስታውቀዋል፡፡ በተያያዘ ዜና የደጀን ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት አካል የሆነው የደጀን -ደብረ ማርቆስ የማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ሥራ 86 በመቶ ላይ መድረሱን የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ እንዳለ ላቀው ተናግረዋል፡፡ በመስመሩ ላይ ከሚተከሉ 111 የኃይል ተሸካሚ ምሶሶዎች መካከል የ98ቱ የተከላ እና የ40 ምሶሶዎች የመስመር ዝርጋታ ሥራዎች መከናወናቸውንም አስተባባሪው ገልፀዋል፡፡ የጸጥታ ስጋት፣ የሲሚንቶና ብረት እጥረት እንዲሁም የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች አቅርቦት መዘግየት በፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ላይ ችግር ሆኖ መቆየቱን ያስታወሱት ኃላፊዎቹ ቀሪ ሥራዎችን ለማጠናቀቅም ከዕቃ አቅርቦትና ከጸጥታ ጋር በተገናኘ የሚስተዋሉ ችግሮች መፍትሔ ሊሰጣቸው ይገባል ብለዋል፡፡ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ፕሮግራም 1 ፕሮጀክት ማኔጅመንት 2 ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ መሐመድ ሽኩር በበኩላቸው በፕሮጀክቱ ላይ የተስተዋሉ ችግሮች ፕሮጀክቱ በተያዘለት መርሀ ግብር መሰረት እንዳይጠናቀቅ ማድረጉን ገልፀው ችግሮችን ለመፍታትም የተለያዩ ሥራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የሲሚንቶ እና የብረት እጥረቱ እንደተቀረፈ ያነሱት አቶ መሐመድ ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልጉ ቀሪ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች እስከ ግንቦት መጀመሪያ ባለው ጊዜ ውስጥ እንደሚቀርቡ በአቅራቢው በኩል ይሁንታ መሰጠቱን አስታውቀዋል፡፡ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀም 87 ነጥብ 5 በመቶ የደረሰ ሲሆን ሥራው ሲጠናቀቅ በደጀን ከተማና በዙሪያው ለሚገኙ ወረዳዎች እና ኢንዱስትሪዎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ያግዛል፡፡ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ በጀት እየተከናወነ የሚገኘው የደጀን-ደብረ ማርቆስ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ በራስ ኃይል መምሪያ በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን በዕቃ አቅርቦቱ ደግሞ ፓወር ቻይና የተባለ ኩባንያ እየተሳተፈበት ይገኛል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

ባለፉት ዘጠኝ ወራት በተፈፀመ ስርቆት 22 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ወድቀዋል ……..///……… በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል በሚገኙ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ በሚከናወነው ሥራ ላይ ተግዳሮት እየሆነ መምጣቱን የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና የሪጂን ማስተባበሪያ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ መንግስቱ እንደተናገሩት ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሁሉም ሪጂኖች በሚገኙ የኃይል ማስተላለፈያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ የተለያየ መጠን ያለው ስርቆት ተፈፅሟል። ባለፉት ዘጠኝ ወራት በኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ ሽቦ ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በተፈፀመ ስርቆት 22 ምሰሶዎች መውደቃቸውን እና ከዚህ ውስጥ ሰባቱ በሰሜን ምዕራብ ሪጂን በተፈፀመ ስርቆት የወደቁ መሆናቸውን ገልፀዋል። አስር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎችን ፈታትቶ ለመውሰድ በተፈፀመ ከፍተኛ ስርቆት ምክንያት በጊዜያዊነት ኃይል ማስተላለፍ አቋርጠው እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በስርቆት ምክንያት ከወደቁ ምስሶዎች በተጨማሪ ከመሬት እንቅስቃሴ ጋር በተያያዙ እና በሌሎች ሰው ሰራሽ ምክንያቶች ደግሞ 13 ምሰሶዎች መውደቃቸውንም አስታውቀዋል። በዘርፉ የሪጂን የኃይል ማስተላለፊያ መስመስና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተሮች እንደገለፁት አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ የተለያዩ ሥራዎች አየተከናወኑ ቢሆንም እየተባባሰ የመጣው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች አካላት ስርቆት በኦፕሬሽን ሥራው ላይ ፈተና እየሆነ ይገኛል። የስርቆት ችግሩ ከመደበኛ ሥራቸው ይልቅ በአስቸኳይ የጥገና ሥራዎች ላይ እንዲያተኩሩ እያስገደዳቸው ስለመሆኑም አመልክተዋል። የስርቆት ወንጀሎችን ቀድሞ ለመከላከል በተቋሙና በሪጂኖች የተለያዩ ሥራዎች ቢከናወኑም ችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ በመሆኑ ከተቋሙ አቅም በላይ እየሆነ መምጣቱን ነው ኃላፊዎቹ ያነሱት። በመሆኑም ችግሩን ለመፍታት ተቋሙ ከከፍተኛ የመንግስት አካላት ጋር በመወያየት ዘላቂ የሆነ መፍትሔ ማስቀመጥ ይኖርበታል ብለዋል። በኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች የኃይል መቆራረጥ እንዲያጋጥም ከማድረግ ባለፈ ተቋሙን ለከፍተኛ ኪሳራ እየዳረገው ይገኛል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

የጣቢያውን ሠራተኞች አቅም ለማሳደግ ከመቀሌ ዩኒቨርስቲ ጋር በትብብር እየተሰራ ነው ........//........ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተከዜ የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሠራተኞችን አቅም ለመገንባት ከመቀሌ ዩኒቨርስቲ ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ጣቢያው አስታወቀ። የጣቢያው የሰው ኃይል፣ ንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ መኮንን ገ/ሊባኖስ እንደተናገሩት የሠራተኞችን አቅም ለማጎልበት የሥራ ላይ ሥልጠና ከመስጠት ባለፈ ከመቀሌ ዩኒቨርስቲ ጋር ተነጋግሮ መምህራንን ሠራተኞቹ ወዳሉበት ቦታ በማስመደብ የቅዳሜና እሁድ የትምህርት መርሃግብር ተጀምሯል፡፡ ጣቢያው የመምህራንን ማረፊያ፣ የመመላለሻ ትራንስፖርት፣ የመማሪያ ክፍል እና በኃይል ማመንጫ ቤቱና በማከፋፊያ ጣቢያው በተግባር የታገዘ ትምህርት የሚማሩበትን ሁኔታ ማመቻቸቱን ገልጸዋል። እንደ አቶ መኮንን ገለጻ ጣቢያው ባመቻቸው የትምህርት እድል እስከ አሁን 26 የሚደርሱ ሠራተኞች የተመረቁ ሲሆን 14 የሚሆኑት ደግሞ በትምህርት ላይይገኛሉ፡፡ በጣቢያው የኦፕሬሽንና ጥገና ክፍል ባለሙያ በርኸ ደስታ ሠራተኛው ስራውን እየሰራ አቅሙን የሚያሳድግበትና የእውቀት አድማሱን የሚያሰፋበት ዕድል መፈጠሩ የሚበረታታ መሆኑን ገልጿል። የጣቢያውን ሥራ በተሻለ ዕውቀት በማከናወን ውጤት ለማስመዝገብ አቅሙ የተገነባ ሠራተኛ መኖሩ አስፈላጊ ነው የሚለው ባለሙያው በቀጣይ ሙሉ የትምህርት ወጪቸውን የሚሸፈንበት ሁኔታ እንዲመቻች ጠይቋል። የትምህርት ዕድሉ ተጠቃሚ የሆነው ሌላኛው የጣቢያው ባለሙያ ዮናስ ገብረ ዮሐንስ በበኩሉ የትምህርት ዕድሉ ሙያዊ አቅማቸውን ለማሳደግና የተሻለ ደረጃ ለመድረስ የሚረዳ መሆኑን ተናግሯል። ቀደም ሲል ሠራተኛው ትምህርት ለመማር ሲል ሥራ ለቆ እስከመሄድ ያስብ ነበር የሚለው ባለሙያው አሁን ግን ሠራተኛው ተረጋግቶ ሳይጉላላ ትምህርቱን እየተማረ መሆኑን ገልጿል። የመቀሌ ዩኒቨርስቲ መምህር የሆኑት ሙሴ ኃየሎም ዩኒቨርስቲው የሚሰጠው ትምህርት ተማሪዎቹ በተግባር የሚያውቁትን ዘመኑ ከደረሰበት የእውቀት ደረጃ ጋር አዋህደው እንዲጠቀሙ የሚያስችል ነው ብለዋል። መቀሌ ዩኒቨርስቲ የጣቢያውን ውጤታማነት ለማሳደግ በሚያስችሉ የሰው ሀብት ልማት ላይ ከጣቢያው ጋር በትብብር መስራቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለጹት መምህር ሙሴ በሀገሪቱ የኤሌክትሪክ ኃይል ዕድገት ላይ የበኩላችውን አሻራ ለማሳረፍ እድል በማግኘታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። የተከዜ የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ 172 ሠራተኞች አሉት። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 27 ቀን 2016 ዓ.ም