ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 534 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 338 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 162 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 534 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 29 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 6، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 25.10‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.85‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 901 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 619 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 8.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 30 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 534
المشتركون
-124 ساعات
-167 أيام
+630 أيام
أرشيف المشاركات
photo content
+1

photo content

photo content
+2

ተቋሙ ሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነት ለማረጋገጥ ባከናወናቸው ሥራዎች የብር ደረጃ ዕውቅና ሲሰጠው መሰረታዊ የሰራተኛ ማህበሩ ደግሚ የወርቅ ደረጃ ተሸላሚ ሆኗል ………..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምቹ የሥራ ሁኔታ እንዲፈጠርና ሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነት እንዲረጋገጥ በማድረጉ ዕውቅና ተሰጠው፡፡ ተቋሙ ዕውቅና የተሰጠው ኢትዮጵያ የዓለም የሥራ ድርጅት አባል የሆነችበት 100ኛ ዓመት በተከበረበት እና ብሔራዊ የአሰሪና ሠራተኛ ጉባዔ በተካሄደበት ሥነ ሥርዓት ላይ ላይ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በመንግስት የልማት ድርጅቶች መካከል በተደረገ ውድድር ሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነት ለማረጋገጥ ባከናወናቸው ሥራዎች የብር ደረጃ ተሸላሚ በመሆን የምስጋና የምስክር ወረቀት እና ዋንጫ ተበርክቶለታል፡፡ የተቋሙ መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር ደግሞ የወርቅ ደረጃ ተሸላሚ ሆኗል፡፡ የምስክር ወረቀት እና ዋንጫውን የዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይና የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ ተቀብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ የዓለም የሥራ ድርጅት አባል የሆነችበት 100ኛ ዓመት በተከበረበት እና ብሔራዊ የአሰሪና ሠራተኛ ጉባዔ በተካሄደበት ሥነ ሥርዓት ላይ ከተካሄደው የዕውቅና መርሐግብር በተጓዳኝ አውደርዕይ ተከፍቶ ለዕይታ በቅቷል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 26 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

የማመንጫ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንን ለማሳለጥ የሚያግዝ ሥራ እየተከናወነ ነው ……….///……... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጫ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም የማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽንን ለማሳለጥ የሚያግዝ ፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል ዝግጅት መጀመሩን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የዕቅድና አፈፃፀም ክትትልና ትንተና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ታገል ደገፋ እንደገለፁት የአሰራር ሥርዓትን ለማዘመን ተግባራዊ በሆነው ሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ሲስተም የሚተገበረው ሞጁል የአራት የሥራ ዘርፎችን የአሰራር ሥርዓቶች ለማዘመን ያስችላል። ከሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ የአሰራር ሥርዓት ጋር ተያይዞ ተቋማዊ የለውጥ አስተዳደር ሥራን የሚመራ የትግበራ ቡድን ተዋቅሮ የተለያዩ እንቅሰቃሴዎችን እያደረገ እንደሚገኝ ሥራ አስኪያጁ ጠቅሰዋል። ፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል የኃይል ማመንጫ፣ የማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ንብረቶችን የሚመዘግብ ከመሆኑም ባሻገር በዕቅድ ላይ የተመሠረቱ የጥገና ሥራዎችን ለማከናወን ፋይዳው የጎላ መሆኑን አቶ ታገል ተናግረዋል። የአሰራር ሥርዓቱ በዋናነት የንብረት አስተዳደር መዋቅርን እንዲሁም የተቋም ሀብት ዕቅድን መሠረት የሚያደርግ መሆኑንም ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅት ለመረጃ መሰብሰቢያ የሚያገለግሉ ረቂቅ የመረጃ መዋቅር እና የቢዝነስ ብሉ ፕሪንት ዝግጅት ላይ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል። ከዚህ በፊት ይከናወኑ የነበሩ የጥገና ሥራዎች በሲስተም የተደገፈ የመረጃ ሥርዓት ያልነበራቸው ከመሆናቸውም ባሻገር ወጥነት የማይስተዋልባቸው እንደነበሩ ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል። የጥገና ሞጁሉ ድንገተኛና በዕቅድ የሚከናወን ጥገና፣ የካሊብሬሽን እና ተያያዥ የአሰራር ሥርዓቶችን ያቀፈ መሆኑንም ነው አቶ ታገል የተናገሩት። ሞጁሉ ሲጠናቀቅ ለጥገና ሥራዎች ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸው የጥገና ዕቃዎች መለዋወጫ ማውጫ እና ቁልፍ የመረጃ ማሰባሰቢያ ቋት የአሰራር ሥርዓቶች እንደሚኖሩት ገልፀዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የጥገና ሞጅሉ የፍተሻና መለኪያ መሳሪያዎች የጥራት ደረጃን ለማወቅ፤ በተቋሙ ውስጥ የሚገኙ ባለሙያዎችን አቅም ለማሳደግ፤ የውጭ ምንዛሬን ለማዳን እንዲሁም የሥራ ጥራትን ለመጨመር አስተዋጽኦው የጎላ ነው። ሞጁሉ ሙሉ በሙሉ መተግበር ሲጀምር የኃይል ማመንጫዎች፣ ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የአሰራር ሥርዓት ለማዘመን፣ ጠንካራ የሀብት ቁጥጥር ሥርዓት ለመዘርጋት፣ የተቋሙን ወጭ ለመቀነስና ሥራን ለማቀላጠፍ እንዲሁም መረጃዎችን ለማጥራት አስተዋፅኦው ከፍ ያለ መሆኑን ጠቅሰዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 25 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችሉ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እየተከናወኑ ነው .......…//…...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለህብረተሰቡ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ተጨማሪ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እያከናወነ እንደሚገኝ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ አስታወቁ፡፡ የዋና ሥራ አስፈፃሚው ተወካይና የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ እንደገለፁት ተቋሙ የሀገሪቱን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት የሚያስችል የሦስት ዓመት የግሪድ ስትራቴጂክ ዕቅድ ቀርፆ መተግበር ጀምሯል። ተቋሙ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ ከፍተኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ከተጠቃሚው ህብረተሰብ ጋር ያላቸውን ቁርኝት የሚዳስስ ጥናት ማድረጉን ተናግረዋል፡፡ ግንባታቸው እየተከናወነ የሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በምን ያህል ኪሎ ሜትር ርቀት ውስጥ ለምን ያህል የህብረተሰብ ክፍል ተደራሽ ይሆናሉ የሚለው ጉዳይ በጥናቱ ላይ መካተቱን ገልፀዋል፡፡ እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካዩ ገለፃ ጥናቱ በቀጣይ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ወደ ግንባታ ሊገቡ የታሰቡ የከፍተኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችንም ታሳቢ አድርጓል፡፡ የሦስት ዓመቱ ስትራቴጂክ ዕቅድ ሲጠናቀቅ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ተደራሽነት በ30 እና 60 ኪሎ ሜትሮች ርቀት ውስጥ ምን ሊመስሉ እንደሚችሉ በጥናቱ መካተቱንም ነው ጨምረው የጠቀሱት፡፡ በጥናቱ መሰረት በሀገር አቀፍ ደረጃ በ30 ኪሎ ሜትር ሽፋን ውስጥ 51 በመቶ እንዲሁም በ60 ኪሎሜትር ዙሪያ 87 በመቶ የሚሆነው የህብረተሰብ ክፍል በከፍተኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኃይል አቅርቦት እያገኘ እንደሚገኝ አብራርተዋል፡፡ እንደ አቶ አንዱዓለም ገለፃ በስትራቴጂክ ዕቅድ ዘመኑ መጨረሻ ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት የሚጀምሩትን የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ጨምሮ በ30 ኪሎ ሜትር ሽፋን ወደ 59 በመቶ እንዲሁም በ60 ኪሎሜትር ርቀት ደግሞ ወደ 91 በመቶ በማሳደግ ህብረተሰቡ አስተማማኝና ያልተቆራረጠ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኝ እየተሰራ ነው፡፡ የከፍተኛ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለህብረተሰቡና ለከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ቅርብ እየሆኑ በመጡ ቁጥር ያልተቆራረጠ የኤሌክትሪክ ኃይል በጥራት በማቅረብ ኢኮኖሚውን እንደሚያግዝ ይታመናል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ህዳር 24 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

photo content
+1

በኢትዮጵያ ግዙፍ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ሊገነባ ነው ........///...... በኢትዮጵያ ብሎም በምስራቅ አፍሪካ በማመንጨት አቅሙ የመጀመሪያ የሆነ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ለመገንባት የሚያስችል ሥምምነት ተፈረመ። የመግባቢያ ሥምምነቱን የገንዘብ ሚኒስቴር አሜአ ፓወር ከተሰኘ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ኩባንያ ጋር  ተፈራርሟል፡፡ 300 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው ይህ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በሶማሌ ክልል አይሻ ወረዳ ላይ ይገነባል። የንፋስ ኃይል ማመንጫ ግንባታው ሲጠናቀቅ በዓመት በአማካኝ 1 ነጥብ 22 ቴራ ዋት ኃይል የሚያመነጭ ሲሆን ግንባታው በ18 ሺህ ሔክታር መሬት ላይ ያርፋል። ሥምምነቱ በመንግሥት እና በግል አጋርነት ማዕቀፍ የሚሰራ ትልቁ ኢንቨስትመንት እንደሆነም ነው የተገለፀው። 600 ሚሊዬን የአሜሪካን ዶላር በጀት የተመደበለትን ፕሮጀክት ተግባራዊ ለማድረግ የ3 ዓመታት ጥናት ሲደረግ ቆይቷል። የኃይል ማመንጫ በግንባታ እና በኦፕሬሽን ወቅት በሺህዎች ለሚቆጠሩ ሠራተኞች ጊዜያዊና ቋሚ የሥራ ዕድል ይፈጥራል ተብሎ እንደሚጠበቅ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መረጃ ያሳያል። ሥምምነቱ ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ላይ መሰረት ላደረገ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ስትራቴጂዋ ተጨማሪ ግብዓት ይሆናል ተብሎ ታምኖበታል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በመሆን አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ በንፁህና ታዳሽ የኃይል ልማት ዘርፍ ላይ እንደሚሰሩም ነው የተገለፀው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ህዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ የስራ መደቦች ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መስከረም 08 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው በተሰጠው የጽሁፍና የተግባር ፈተና ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከህዳር 24 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ ብረታብረት ፊት ለፊት በሚገኘው ዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናዉን በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈጽሙ እናሳውቃለን፡፡ ማሳሰቢያ፡- ስማችሁ ያልተጠቀሰ ተወዳዳሪዎች የማለፊያ ነጥብ ያላገኛችሁ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ህዳር 22 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የድል ጉዞውን አጠናክሮ ቀጥሏል ..........///........... በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ዛሬ በተካሄደው የ4ኛ ሳምንት መርሐግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ተጋጣሚውን ወልዲያ ከተማን አንድ ለባዶ አሸንፏል። የክለቡ የፊት አውራሪ መሳይ ሰለሞን በ22ኛው ደቂቃ ላይ ለኢትዮ-ኤሌክትሪክ ብቸኛዋን ጎል ከመረብ አሳርፏል። በመጀመሪያው አጋማሽ የመሀል ሜዳ ፍፁም የበላይነት ይዞ የተጫወተው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በአጥቂ ስፍራ ተጫዋቾቹ ናትናኤል ሰለሞን እና መሳይ ሰለሞን ተደጋጋሚ የጎል ሙከራዎች ማድረግ ችሏል። ወልዲያ ከተማ በአንፃሩ በመከላከል እና በመልሶ ማጥቃት አቻ ለመሆን ሙከራ ቢያደርግም ሳይሳካለት ቀርቷል። በሁለተኛው አጋማሽ 20ኛው ደቂቃ ላይ የተከላካይ ክፍል ተጫዋች የሆነውን ሙሉቀን ደሳለኝ በቀይ ካርድ ያጣው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ቀሪዎቹን ደቂቃዎች በጎደሎ ለመጫወት ተገዷል። በሊጉ ያደረጋቸውን አራት ጨዋታዎች ሙሉ በሙሉ በማሸነፍ በ12 ነጥብ እና ስድስት ንፁህ ጎል ምድብ <<ሀ>>ን እየመራ የሚገኘው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመጪው ረቡዕ ህዳር 26 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:30 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም ከኮልፌ ክ/ከተማ ጋር ጨዋታውን የሚያካሂድ ይሆናል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ህዳር 22 ቀን 2016 ዓ.ም

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የድል ጉዞውን አጠናክሮ ቀጥሏል ..........///........... በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ዛሬ በተካሄደው የ4ኛ ሳምንት መርሐግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ተጋጣሚውን ወልዲያ ከተማን አንድ ለባዶ አሸንፏል። የክለቡ የፊት አውራሪ መሳይ ሰለሞን በ22ኛው ደቂቃ ላይ ለኢትዮ-ኤሌክትሪክ ብቸኛዋን ጎል ከመረብ አሳርፏል። በመጀመሪያው አጋማሽ የመሀል ሜዳ ፍፁም የበላይነት ይዞ የተጫወተው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በአጥቂ ስፍራ ተጫዋቾቹ ናትናኤል ሰለሞን እና መሳይ ሰለሞን ተደጋጋሚ የጎል ሙከራዎች ማድረግ ችሏል። ወልዲያ ከተማ በአንፃሩ በመከላከል እና በመልሶ ማጥቃት አቻ ለመሆን ሙከራ ቢያደርግም ሳይሳካለት ቀርቷል። በሁለተኛው አጋማሽ 20ኛው ደቂቃ ላይ የተከላካይ ክፍል ተጫዋች የሆነውን ሙሉቀን ደሳለኝ በቀይ ካርድ ያጣው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ቀሪዎቹን ደቂቃዎች በጎደሎ ለመጫወት ተገዷል። በሊጉ ያደረጋቸውን አራት ጨዋታዎች ሙሉ በሙሉ በማሸነፍ በ12 ነጥብ እና ስድስት ንፁህ ጎል ምድብ <<ሀ>>ን እየመራ የሚገኘው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመጪው ረቡዕ ህዳር 26 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:30 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም ከኮልፌ ክ/ከተማ ጋር ጨዋታውን የሚያካሂድ ይሆናል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ህዳር 22 ቀን 2016 ዓ.ም ተ.ቁ የተወዳዳሪዎች ስም ፆታ ኮድ ውጤት ከ 50% ከ 30% ከ 70% የቃለመጠይቅ ውጤት ከ 100% ድምር ውጤት ደረጃ ምርመራ 1 ፋሲካ በቀለ ተሰማ ሴ C/C/G/018 38.5 23.1 65 88.1 1ኛ አልፈዋል 2 መቅደስ ተካልኝ ወ/አረጋይ ሴ C/C/G/011 32 19.2 64 83.2 2ኛ አልፈዋል 3 ሙላቷ ብርሃኑ እንዳይላሉ ሴ C/C/G/046 27 16.2 66 82.2 3ኛ አልፈዋል 4 ቤተልሔም አባይ ተካ ሴ C/C/G/051 34 20.4 61 81.4 4ኛ ተጠባባቂ 5 ብርቱካን ግርማ ብርሃኑ ሴ C/C/G/059 33 19.8 60 79.8 5ኛ ተጠባባቂ 6 ጥሩሴት አዳሙ መንግስቱ ሴ C/C/G/083 32.5 19.5 58 77.5 6ኛ ተጠባባቂ 7 በፀሎት ደስታ ተፈራ ሴ C/C/G/023 44 26.4 50 76.4 7ኛ ተጠባባቂ 8 ትዕግስት ታደለ ዳባ ሴ C/C/G/086 32 19.2 57 76.2 8ኛ ተጠባባቂ 9 ጥሩነሽ ገለታው ማሞ ሴ C/C/G/004 36 21.6 52 73.6 9ኛ ተጠባባቂ

photo content
+1

የኃይል ማመንጫ ጣቢያው 111 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ አመንጭቷል ……..///…….. የአዳማ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በበጀት ዓመቱ አራት ወራት 111 ጊጋ ዋት ኤሌክትሪክ ማመንጨቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ መለሰ ሲሎ እንደገለጹት ጣቢያው በአራት ወራት ለማምረት ካቀደው 111 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ውስጥ 111 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ በማመንጨት የዕቅዱን 99 ነጥብ 3 በመቶ ማሳካት ችሏል፡፡ ጣቢያው እያንዳንዳቸው 1 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት ኃይል ማመንጨት ከሚችሉ 102 ተርባይኖች መካከል በአሁኑ ወቅት ከሦስቱ ተርባይኖች በቀር ሁሉም ተርባይኖች በሙሉ አቅማቸው ኃይል እያመነጩ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል፡፡ ለጥገና ተብሎ ሥራ ያቆሙት ሦስቱ ተርባይኖች አስፈላጊው ጥገና ተደርጎላቸው በቅርቡ ወደ ሥራ ይመለሳሉ ያሉት ሥራ አስኪያጁ ይህም ጣቢያው በበጀት ዓመቱ መጨረሻ ለማምረት ያቀደውን 429 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ለማምረት እንደሚያስችለው አብራርተዋል፡፡ የጣቢያው ኦፕሬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ጌታቸው በበኩላቸው ጣቢያው ደህንነቱ ተጠብቆ አስተማማኝ ኃይል እንዲሰጥ የ24 ሰዓት ክትትል እየተደረገለት እንደሆነ አንስተዋል፡፡ የአዳማ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ጨምሮ የተገነቡና በግንባታ ላይ ያሉ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ፕሮጀክቶች የሀገሪቱን የኃይል ስብጥር ከማሳደግ ባለፈ የታዳሽ የኃይል ምንጮችን አጠቃቀም እንደሚያሳድግ ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ከጥቅምት እስከ ሚያዚያ ባለው ጊዜ ከፍተኛ ንፋስ በመኖሩ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች በአመዛኙ የተሻለ ምርት ስለሚሰጡ በበጋ ወቅት የግድቦች የውሃ መጠን ለመቆጠብ ዕድል ይሰጣሉ፡፡ የአዳማ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2007 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረ ጣቢያ ነው፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 19 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

የኢነርጂ ሜትር የገጠማ ሥራ በራስ አቅም ማከናወን ተችሏል ………///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምዕራብ እና ሰሜን ሪጅን በሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኢነርጂ ሜትሮችን በተቋሙ በራስ አቅም እየተተከለ መሆኑን የማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ገለጸ፡፡ በዘርፉ የስማርት ሜትር ፕሮጀክት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሃይማኖት ተፈራ እንደገለጹት በሁሉም ሪጅኖች በሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኢነርጂ ሜትር ቆጣሪ ገጠማ ለማከናወን ሲመንስ ፕሮፐርቲ ሊሚትድ ከተባለ የደቡብ አፍሪካ ኩባንያ ጋር ስምምነት ተደርሶ ሥራው ሲከናወን ነበር፡፡ ይሁንና በሰሜን የሀገራችን ክፍል በተካሄደው ጦርነት እና በምዕራብ ኦሮሚያ ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት ሥራ ተቋራጩ የተከላ ሥራውን በዕቅዱ መሰረት ማከናወን አልቻለም፡፡ በመሆኑም ከተቋራጩ ጋር የነበረው ስምምነት እንዲቋረጥና በሁለቱ ሪጅኖች ሰላም ሲሰፍን በተቋሙ የራስ አቅም እንዲከናወን የተቋሙ ከፍተኛ ሥራ አመራር በወቅቱ ውሳኔ ማሳለፉን ሥራ አስኪያጇ አስታውሰዋል፡፡ በውሳኔው መሰረት ሥራውን በራስ አቅም ለማከናወን ባለሞያዎችን ከማብቃት ጀምሮ የተለያዩ ሥራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ሥራ አስኪያጇ አስረድተዋል፡፡ በሰሜኑ ኢትዮጵያ የተደረሰውን የሠላም ስምምነት ተከትሎ በሪጅኑ የኢነርጅ ሜትር ይተከልባቸዋል ተብሎ በዕቅድ ከተያዙት 10 ማከፋፈያ ጣቢያዎች መካከል በስምንቱ ላይ በራስ አቅም ተከላው መጠናቀቁንና በሁለቱ ደግሞ በቀጣይ እንደሚከናወን ወ/ሮ ሃይማኖት ተናግረዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጇ ገለጻ በሪጅኑ ይተከላሉ ከተባሉ 126 የኢነርጂ ሜትሮች ውስጥ 97ቱ በስምንቱ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የተተከሉ ሲሆን ቀሪ 29 ኢነርጅ ሜትሮች ደግሞ በሁለቱ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚተከሉ ይሆናል፡፡ በምዕራብ ሪጅን በሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚተከሉ የኢነርጅ ሜትሮችን በራስ አቅም የመግጠም ሥራ መጀመሩንም ሥራ አስኪያጇ አመልክተዋል፡፡ የገጠማ ሥራው ከምዕራብና ከሰሜን ሪጅኖች እንዲሁም ከተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት በተውጣጡ ባለሙያዎች መከናወኑንም አስረድተዋል፡፡ የተቋሙ ሠራተኞች ከዚህ በፊት ሥራ ተቋራጩ ሲያከናውን በነበረው ሥራ ላይ ሲሳተፉ እንደነበር ያስታወሱት ኃላፊዋ ይህም በራስ አቅም ለተከናወነው ሥራ እገዛ ማድረጉን ነው የገለጹት፡፡ በራስ አቅም ለተከናወነው የገጠማ ሥራ ከ520 ሺህ ብር በታች ወጪ መደረጉን እና ይህ ሥራ በተቋራጩ ይከናወን ቢባል ከ1 ነጥብ 85 ሚሊዮን ብር እና ከ25 ሺህ የአሜሪካን ዶላር በላይ ይጠይቅ እንደነበር ወ/ሮ ሃይማኖት አስታውቀዋል፡፡ ከዚህ በፊት በሥራ ተቋራጩ አማካኝነት 9 መቶ 86 የኢነርጅ ሜትሮች በ1 መቶ ዘጠኝ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ተገጥመዋል፡፡ በ130 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚተከሉ የኢነርጅ ሜትሮችን ለማቅረብ፣ ለመግጠም፤ ለመፈተሸና ለመሞከር በአለም ባንክ የሚሸፈን ከ25 ነጥብ 28 ሚሊዮን በላይ ብር እና ከ2 ነጥብ 17 ሚሊዮን በላይ የአሜሪካ ዶላር በጀት ተይዞ ነበር፡፡ በሁለቱ ሪጅኖች በራስ አቅም ለሚከናወነው ሥራ ከ 3 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ እና 43 ሺህ 1 መቶ የአሜሪካ ዶላር ከውሉ ላይ ተቀናሽ በማድረግ በጀት ተይዟል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 18 ቀን 2016 ዓ.ም