ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 530 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 328 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 176 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 530 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 06 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 6، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -3، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 27.84‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.05‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 323 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 492 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 07 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 530
المشتركون
-324 ساعات
-97 أيام
+630 أيام
أرشيف المشاركات
photo content
+4

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ውሃ ሙሊትን ምንም ዓይነት ተዓምራዊ ኃይል አያስቆመውም …………/////………… የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌትን ለማከናወን ምንም ዓይነት ተዓምራዊ ኃይል እ
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ውሃ ሙሊትን ምንም ዓይነት ተዓምራዊ ኃይል አያስቆመውም …………/////………… የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌትን ለማከናወን ምንም ዓይነት ተዓምራዊ ኃይል እንደማያስቆመው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር ገልፀዋል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ የበለስ ጃዊ ባለ 132/33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ በተመረቀበት ሥነ ስርዓት ላይ እንደተናገሩት የግድቡን ግንባታ እና በያዝነው ዓመት የሚካሄደውን ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት በተያዘለት ጊዜ ለማከናወን የሚያስቆም ምንም ዓይነት ምድራዊ ኃይል አይኖርም፡፡ የሁለተኛውን ዙር የውሃ ሙሌት ለማከናውን የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ እንደሚገኝ የጠቆሙት ርዕሰ መስተዳድሩ ፕሮጀክቱ በታሰበው ጊዜ እንደሚሳካ አልጠራጠርም ብለዋል፡፡ እንደ አቶ አገኘሁ ገለፃ የኢትዮጵያን የወደፊት ብልፅግና እና ሉዓላዊነት ማንም ኃይል ሊገታው አይችልም፤ ሊፈቀድለትም አይገባም፡፡ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በተያዘው የበጀት ዓመት በሁለት ተርባይኖች ኃይል ማመንጨት እንደሚጀምርና የግንባታ ስራው ተጠናቆ ኃይል ማመንጨት ሲጀምር በአሁኑ ወቅት በክልሎች ላይ ያለውን የኃይል ፍትሃዊነትና ተደራሽነት ችግር እንደሚፈታም ገልፀዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት የህዳሴ ግድብ በተሻለ አፈፃፀም ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ያነሱት አቶ አገኘሁ የፕሮጀክቱ ግንባታ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ እንዲደርስ ሌት ተቀን በመስራት ላይ ለሚገኙት ሠራተኞችም ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በመጀመሪያ ዙር እንዲይዝ የታቀደለትን 4 ነጥብ 9 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ባሳለፍነው ሐምሌ 2012 ዓ.ም

ዋና ሥራ አስፈፃሚውና አምባሳደሩ የመልካ ዋከና የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ጎበኙ ………////……….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ እና በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር የመልካ ዋከና የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ጎበኙ፡፡ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ አሸብር ባልቻ ጣቢያው ከ30 ዓመት በላይ ያገለገለ በመሆኑ የማሻሻያ ሥራዎች እንደሚፈልግ ለአምባሳደሩ ገልፀውላቸዋል፡፡ የጣቢያውን አቅም ለማሳደግ ቀደም ሲል የመግባቢያ ሥምምነት መፈረሙን በማስታወስ የተጀመሩት ቴክኒካል ጥናቶች ሂደቶች እንዲፋጠኑና ለማሻሻያ ስራው ሩሲያ አስፈላጊውን ድጋፍ እንድታደርግ ጠይቀዋል፡፡ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተርኪን በበኩላቸው በቀድሞዋ ሶቭየት ህብረት ካምፓኒ ለተገነባው የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የማሻሻያ ሥራ ሩሲያ አስፈላጊውን እንደምታደርግ አረጋግጠዋል፡፡ በጉብኝቱ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ አምባሳደር ሌንጮ ባቲና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮች ተገኝተዋል፡፡ የመልካ ዋከና የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 153 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው ሲሆን ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው በ1980 ዓ.ም. ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 03 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content
+4

photo content
+1

photo content
+3

የኤሌክትሪክ ኃይልን ፍትሐዊ በሆነ መልኩ ተደራሽ ማድረግ ይገባል - የአብክመ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር ............./////.............. የጃዊ - በለስ ባለ 132/33 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ተመርቋል፡፡ በምርቃት ሥነ - ስርዓቱ ላይ የተገኙት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አቅሙን በየጊዜው እያሳደገ የሀገሪቱን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት እየሰራ ያለው ሰራ የሚበረታታ ነው፡፡ ይሁን እንጅ በክልሉ የሚስተዋለውን የኃይል ፍትሀዊነትና የተደራሽነት ችግር በመቅረፍ ለሚነሱ የኃይል ጥያቄዎች አፋጣኝ ምላሽ መስጠት ይገባል ብለዋል፡፡ በኃይል ተደራሽነት ችግር ክልሉ በተለያየ መልኩ መጎዳቱን ያስታወሱት ርዕሰ መስተደድሩ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ግን ችግሮቹ እየተቀረፉ መምጣታቸውን ገልፀዋል፡፡ በክልሉ የተገነቡትም ሆነ ወደፊት የሚገነቡት ኢንደስትሪዎችና ፋብሪካዎች የኃይል አቅርቦት ስለሚያስፈልጋቸው ትኩረት ሰጥቶ በመስራት አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጥበት ጠይቀዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት የክልሉ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽፋን ከ50 በመቶ በታች እንደሆነም የጠቆሙት ርዕሰ መስተዳድሩ ክልሉ የሚገባዉን እንጅ ከሚገባው በላይ ኃይል እየጠየቀ አይደለም ብለዋል። የበለስ ጃዊ ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ መገንባት ባለሃብቶች ወደ አካባቢው በመግባት በአግሮ ፕሮሰሲንግ ላይ እንዲሳተፉ ዕድል ስለሚፈጥር እና ለወጣቶችም ሰፊ የስራ ዕድል ስለሚከፍት ማከፋፈያ ጣቢያው ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው ነው አቶ አገኘሁ የገለፁት፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ብቻ መገንባቱ ፋይዳ ስለሌለው የሚመለከተው አካል የማሰራጫ መስመሮችን በአጭር ጊዜ ውስጥ በመገንባት በጃዊ ከተማና አካባቢው የሚስተዋለውን የኃይል ችግር በአፋጣኝ እንዲፈታ አሳስበዋል፡፡ የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ በበኩላቸው የፕሮጀክቱ መገንባት ስኳር ፋብሪካዎች የሚገጥማቸውን የኃይል አቅርቦት ለመፍታትና ለጃዊ ከተማና አካባቢው የኤሌክትሪክ ኃይል በተገቢው ሁኔታ ለማድረስ ያግዛል ብለዋል፡፡ ጣቢያው ከበለስ ስኳር ፋብሪካ ተረፈ ምርት የሚመነጨውን ኃይል ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት በማስገባት የኃይል አቅርቦትን ለማሳደግ ያግዛል፡፡ የመነጨውን ኃይል በአግባቡ ለተጠቃሚው ለማድረስ የማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በስፋት መገንባት እንደሚያስፈልግም ዶ/ር ስለሺ አስታውቀዋል፡፡ በአምስት ዓመት ውስጥ "ብርሃን ለሁሉም" የሚለውን ፕሮግራም ለማሳካት በግሪድና ከግሪድ ውጭ አገልግሎት የሚሰጡ በርካታ የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ በመከናወን ላይ መሆናቸውን ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ በበኩላቸው ሀገሪቱ ለጀመረችው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መዋቅራዊ ሽግግር የሚውል የኤሌክትሪክ ኃይል ከተለያዩ የኃይል ምንጮች ለማምረት እየተሠራ እንደሚገኝ ገልፀዋል። የኤሌክትሪክ ኃይል ለአንድ ሀገር እድገትና ከኋላ ቀርነት ለመላቀቅ ፋይዳው የጎላ በመሆኑ መንግስት ለዘርፋ ትኩረት በመስጠት በርካታ መዋዕለ ነዋይ መድቦ የኃይል መሰረተ ልማቶችን በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ፍትሐዊ በሆነ መልኩ ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት ተሠጥቶት በመሰራት ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡ እንደ አቶ አሸብር ገለፃ ከአዳዲስ ፕሮጀክቶች ግንባታ በተጨማሪ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙትን የማዘመንና አቅም የማሳደግ ሥራም እየተከናወነ ነው፡፡፡ በሀገሪቱ አሁን ያለውን 4 ሺህ 400 ሜጋ ዋት አጠቃላይ የማመንጨት አቅም በቀጣዮቹ ሥስት ዓመታት ወደ 12 ሺህ ሜጋ ዋት ለማድረስ እየተሰራ መሆኑንም ስራ እስፈፃሚው ጠቁመዋል፡፡ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ብቻ ፋይዳ እንደሌለው የተናገሩት አቶ አሸብር የመነጨውን ኃይል ፍትሐዊ በሆነ መልኩ ወደ ተለያዩ አካባቢዎች የሚያደርሱ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታን ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ 397 ሚሊዮን ብር በሆነ ወጪ የተገነባው የበለስ- ጃዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ የፋይናንስ ምንጩ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ሲሆን የማማከርና የግንባታ ስራውም በተቋሙ የራስ ኃይል የተከናወነ ነው። የካቲት 30 ቀን 2013 ዓ/ም

photo content
+7

ሴቶች ለመልካም ማህበረሰብ ግንባታ ያላቸው ድርሻ ከፍተኛ ነው ተባለ .............////......... ሴቶች በተቋማዊ እና ሀገራዊ ግንባታ ካላቸው ግንባር ቀደም ሚና ባለፈ ለመልካም ማህበረሰብ ግንባታ የሚያበረክቱት አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የንብረትና አገልግሎት ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ስመኝ አያሌው ዓለም አቀፍ የሴቶችን ቀን ምክንያት አድርገው ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለፁት ሴቶች በልጆች አስተዳደግ እና በቤተሰብ አስተዳደር ያላቸው ችሎታ እና አስተዋይነት ለመልካም ማህበረሰብ ግንባታ ትልቅ ድርሻ አለው። "ሴቶች በውሳኔ ሰጭነትም ሆነ በተለያዩ ኃላፊነቶች በሴትነታችን ብቻ ሳይሆን በችሎታችን እና በብቃታችን መመረጥ የሚያስችለን አቅም አለን"ያሉት ወ/ሮ ስመኝ ለዚህም ሰፊ እድሎች ሊመቻቹ እንደሚገባ ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ በበኩላቸው የሴቶች ጉዳይ የሰብዓዊነት፣ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳይ በመሆኑ ሴቶች ችሎታቸውን በሁሉም ዘርፎች እንዲያጎለብቱ እድል መስጠት ያስፈልጋል ብለዋል። በተቋሙ ያሉ ብዙዎቹ ሴት ሠራተኞች ባሉባቸው ተደራራቢ ኃላፊነቶች ሙያቸውን እንዳላሳደጉ የገለፁት ኃላፊዋ ይህን ታሳቢ ያደረገ ድጋፍ እንደሚደረግላቸውም ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም የዘንድሮውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (March 8) በምስራቅ ሪጅን ድሬደዋ ከተማ በድምቀት አክብሯል። በተያያዘ ዜና የአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሠራተኞችም ዓለምአቀፉን የሴቶች ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች አክብረዋል። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (March 8) በዓለም 110ኛ እና በአገራችን ደግሞ ለ45ኛ ጊዜ "ሴቶችን የሚያከብር ማህበረሰብ እንገንባ "በሚል መሪ ቃል እየተከበረ ይገኛል። የካቲት 30 ቀን 2013 ዓ/ም

ኢትዮ ኤሌክትሪክ ክለብ ለገቢ ማስገኛ የሚያገለግሉ ሱቆችን ገንብቶ አስመረቀ አንጋፋው የኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ በተለምዶ አጠራር ጎፋ መብራት ኃይል በሚገኘው የተቋሙ ግቢ የውስጥ ገቢውን ለማሳደግ ያስገነባቸውን 38 ሱቆች ከትናንት በስቲያ አስመርቋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ፣የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ፣የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ኢንስትራክተር ሠውነት ቢሻው እና የፌደሬሽኑ ጽ/ቤት ኃላፊ ባህሩ ጥላሁን የተጠናቀቁትን የሱቅና የስፖርት ቤቶች በጋራ መርቀው ከፍተውታል፡፡ ክለቡ ከሚከራዩ ሱቆች በተጨማሪ ለተጫዋቾች ልብስ መቀየሪያ የሚያገለግሉ ክፍሎች፣ መታጠቢያ ቤቶች እና የተመልካቾች መቀመጫ ትሪቡን ገንብቶ ለምረቃ አብቅቷል፡፡ በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት ኢንስትራክተር ሠውነት ቢሻው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ክለብ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ያበረከተው አስተዋጽኦ እጅግ ጉልህ መሆኑን በመግለፅ በአንድ ወቅት ከአስራ አንዱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጨዋቾች መካከል ዘጠኙ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ክለብ ያፈራቸው ተጫዋጮች እንደነበሩ አስታውሰዋል፡፡ የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ክለብ ፕሬዚዳንት አቶ ጫላ አማን የኢትዮ ኤሌክትሪክ ክለብ በኢትዮጵያ አንጋፋና ዕድሜ ጠገብ ክለብ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አንድ ክለብ ውጤታማ ሆኖ እስከመጨረሻው ለመዝለቅ ከደጋፊ እና ከሌሎች ምንጮች የራሱ ገቢ ሊኖረው ይገባል ያሉት አቶ ጫላ የነዚህ ሱቆች ግንባታም የክለቡን የገቢ ምንጭ ለማሳደግ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አቶ ጫላ አክለውም ለግንባታው መጠናቀቅ ጉልህ ድርሻ ላበረከቱ የግንባታው ተቋራጮች፣ሠራተኞችና የስፖርት ቤተሠቦች ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የእግር ኳስ ቡድኖች የተጫወቱ ሲሆን በውጤቱም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከጨዋታ ብልጫ ጋር 3ለ1 በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት መሆን ችሏል፡፡ የኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚተዳደር አንጋፋ ክለብ ነው፡፡ የካቲት 29 ቀን 2013 ዓ/ም

photo content
+2

የበለስ – ጃዊ የኃይል ማስተላለፊያና የጃዊ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተመረቀ። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያውን በዛሬው ዕለት የመረቁት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገርና የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ስለሺ በቀለ ናቸው። የበለስ ጃዊ ማስተላለፊያ መስመር 61 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን የማከፋፈያ ጣቢያው ደግሞ 132/33 የሆነ አቅም አለው። ጣቢያው ለበለስ ስኳር ፋብሪካና ለአካባቢው ኃይል በአስተማማኝ ሁኔታ ለመስጠት ያስችላል። ተጨማሪ መረጃዎችን ይዘን እንመለሳለን።

ማሳሰቢያ በጢስ አባይ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በሚካሄደው ጥገና ምክንያት የጢስ አባይ ፏፏቴ ውሃ ከነገ የካቲት 27 ቀን 2013 ዓ/ም ጀምሮ መጠኑ ጨምሮ ስለሚለቀቅ ከፏፏቴው ግርጌ በሚገኙ አካ
+1
ማሳሰቢያ በጢስ አባይ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በሚካሄደው ጥገና ምክንያት የጢስ አባይ ፏፏቴ ውሃ ከነገ የካቲት 27 ቀን 2013 ዓ/ም ጀምሮ መጠኑ ጨምሮ ስለሚለቀቅ ከፏፏቴው ግርጌ በሚገኙ አካባቢዎች የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንዲችሉ ይህን መልዕክት በማጋራት መልዕክቱን በማድረስ እንድትተባበሩን እንጠይቃለን። የካቲት 26 ቀን 2013 ዓ/ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

የሚዲያ ጥቆማ - ለሁሉም መገናኛ ብዙሃን
የሚዲያ ጥቆማ - ለሁሉም መገናኛ ብዙሃን

photo content

የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ 68 በመቶ ደርሷል ………….////…………. በማሻ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው የማሻ - መቱ ባለ 230/33 ኪ.ቮ. የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት አጠቃላይ አፈጻጸም 68 በመቶ መድረሱን የማከፋፈያ ጣቢያው የሳይት ተቆጣጣሪ መሐንዲስ አቶ ፍቃዱ ሁጤሳ ገለፁ፡፡ መሐንዲሱ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ አንድ አዲስ ባለ 230/33 ኪ. ቮ. ከፍተኛ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና 161 ኪ.ሜ. ርዝመት ያለው የባለ 230 ኪ. ቮ. የኃይል መስመር ዝርጋታን ያጠቃልላል፡፡ እንደ አቶ ፍቃዱ ገለጻ በማከፋፈያ ጣቢያው እስከ አሁን የኤሌክትሮ መካኒካልና የብረታ ብረት ተከላና ለኤሌክትሪክ ገመዶች ቀበራ የሚውል ግንባታ እንዲሁም ሁለት ባለ 31 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመር ተከላ ሥራዎች ተጠናቀዋል፡፡ የመቆጣጠሪያ ቤት፣ የሰራተኞች መኖሪያ ቤት፣ የጥበቃ ቤት ግንባታና የፍሳሽ ማስወገጃ ግንባታዎች የማጠናቀቂያ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ በቀጣይም የጠጠር ንጣፍ፣ የውስጥ አጥር፣ የሲዊችያርድ ግንባታ እና የኬብል ዝርጋታ ሥራዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው እንደሚከናወኑ መሐንዲሱ ጠቁመዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የማከፋፈያ ጣቢያው አጠቃላይ አፈጻጸም 68 በመቶ ደርሷል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ከነባሩ የመቱ ባለ 230/66/33/15 ኪ ቮ. የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተነስቶ አዲስ እስከሚገነባው የማሻ ማከፋፈያ ጣቢያ ድረስ የሚዘረጋው የ75 ኪ.ሜ ባለ 230 ኪ. ቮ. ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ሥራ በቅርቡ ለመጀመር የተለያዩ ስራዎች ተጀምረዋል፡፡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታው 161 ባለ 230 ኪ.ቮ ኃይል ተሸካሚ ማማ ተከላ እና ሽቦ ዝርጋታ ስራ ይኖረዋል፡፡ የፕሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ የትናየት ይመር እንደተናገሩት የማከፋፈያ ጣቢያውን እና የመስመር ዝርጋታውን ስራ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ከአለም ባንክ በተገኘ የብድር 301 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር ተመድቦለታል፡፡ ሥራውን ለመጨርስ 18 ወራት የተያዘለት ሲሆን ግንባታውን ሲኖ ሃይድሮ ኮርፖሬሽን የተባለው የቻይና ኩባኒያ ሲያከናውን በአማካሪነት ደግሞ ኢ. ኤል. ሲ. ELC የተባለ የጣሊያን ኩባኒያ እየተሳተፉበት ይገኛሉ፡፡ ሶስት ባለ 33 ኪ.ቮ. ወጪ መስመር ያሉት ይህ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ ለማሻና ለአካባቢው አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ከማድረጉ ባሻገር የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያን ኃይል ትስስር በማሳለጥ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ከአዲስ አበባ በ700 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ በከፋ ሸካ ዞን ማሻ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው የማሻ - መቱ ባለ 230/33 ኪ.ቮ. የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የተጀመረው ህዳር 2012 ዓ.ም. ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 19 ቀን 2013 ዓ.ም