ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 546 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 351 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 178 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 546 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 02 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 27، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 8، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 25.76‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.84‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 005 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 463 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 9.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 03 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 546
المشتركون
+824 ساعات
-227 أيام
+2730 أيام
أرشيف المشاركات
ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ የስራ መደቦች ላይ ባለሙያዎችን ለመቅጠር ግንቦት 08 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀ
+3
ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ የስራ መደቦች ላይ ባለሙያዎችን ለመቅጠር ግንቦት 08 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመልካቾች በሙሉ ሐምሌ 28 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሜክሲኮ በሚገኘው ኬ ኬር ህንፃ ዋናው መ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ 20ኛ /ሃያኛ ፎቅ/ የፅሑፍ ፈተና የሚሰጥ ስለሆነ ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ በፈተናው ቦታ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

የማራቶን ባለድሏ የኢትዮ ኤሌክትሪክ አትሌት ጎተይቶም ገብረስላሰ እና የአትሌቲክስ ቡድኑ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው ………..////…….. በአሜሪካ ኦሪገን በተካሄደው 18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና 4 ወርቅ፣ 4 ብር እና 2 ነሐስ በአጠቃላይ 10 ሜዳሊያዎችን ይዞ የተመለሰው ባለ ድሉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን አባላት በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በብሔራዊ ቤተመንግስት በተካሄደው የአቀባበል እና የምስጋና መርሐግብር ላይ የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ለአትሌቶቹ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ለሁሉም አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው የገንዘብ ሽልማት የተበረከተ ሲሆን እንደተሳትፏቸው መጠንና እንዳስመዘገቡት ስኬት ተጨማሪ ሽልማት ተበርክቷል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮ ኤሌክትሪክ አትሌት ጎተይቶም ገብረስላሰ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላታል። የስፖርት ክለቡ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ እጅጉ ለአትሌቷ እንኳን ደስ አለሽ በማለት የአበባ ጉንጉን አበርክተውላታል። አትሌት ጎተይቶም ለበርካታ ዓመታት ርቆን የነበረውን የማራቶን ድል 2 ሰዓት 18 ደቂቃ ከ11 ሰከንድ በመግባት የዓለም ሻምፒዮና ሪከርድን ጭምር በመስበር ለሀገሯ የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝታለች። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 21 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+6

ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ለማልማት የሚያስችል እምቅ ሀብት ቢኖራትም በተለያዩ ችግሮች የተነሳ በሚፈለገው መልኩ ለመጠቀም አልቻለችም .......////......... ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ለማልማት የሚያስችል እምቅ የተፈጥሮ ሀብት ቢኖራትም በሚፈለገው መልኩ አልምቶ ለመጠቀም በዘርፉ የሠለጠነ የሰው ኃይል እጥረት፣ የፋይናንስ እና የመሳሪያዎች አለመሟላት እንቅፋት እንደሆነባት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ ገለፁ። በእንፋሎት ኃይል ማመንጫ ጉድጓድ ቁፋሮ ለተሰማሩ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሠራተኞች ጃኮብስ በተሰኘ የኒውዚላንድ ኩባንያና በአፍሪካ ህብረት ትብብር የተዘጋጀውን ሥልጠና የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይና የኃይል ማመንጫዎች ግንባታ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሰፋ ንጉሴ ሲከፍቱ እንደገለጹት በአየር ንብረት ለውጥ የተነሳ የሚከሰተውን የኃይል እጥረት ለመቋቋም የኃይል ስብጥርን ለማመጣጠን ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት አብዛኛወን ኃይል የምታመነጨው ከውሃ በመሆኑ ለአየር ንብረት ተጽእኖ ተጋላጭ ነው። ስለሆነም በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚከሰተውን የኃይል እጥረት ለመቋቋም እና የማይበገር የአረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባት እየተሰራ ላለው ስራ የእንፋሎት የኤሌክትሪክ ኃይል የራሱን አስተዋጽኦ ያበረክታል። ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ ኃይል የሚውል እስከ 10 ሺህ ሜጋ ዋት የሚደርስ እምቅ የእንፋሎት ሀብት እንዳላት የጠቆሙት አቶ አሰፋ ሀገሪቱ ያላትን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት በሚፈለገው መልኩ አልምቶ ጥቅም ላይ ለማዋል በዘርፉ የሠለጠነ የሰው ኃይል አለመኖር፣ የፋይናንስ እና የተለያዩ መሳሪያዎች እጥረት እንቅፋት እንደሆነ ተናግረዋል። ስልጠናው የእንፋሎት ሀብትን ለማልማት እየተሰሩ ባሉ የጉድጓድ ቁፋሮ ስራዎች ላይ እያጋጠሙ ያሉ ክፍተቶችን ለመሙላትና በዘርፉ የሰለጠኑ ባለሙያዎችን ለማፍራት ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል፡፡ የእንፋሎት ኃይልን ለማልማት ኒውዝላንድ እያደረገችው ያለውን ድጋፍ አመስግነው በቀጣይ የምታደርገውን የአቅም ግንባታ ስራ አጠናክራ እንድትቀጥል ጠይቀዋል፡፡ በኢትዮጵያ የኒውዚላንድ አምባሳደር ማይክል ኡፕቶን በበኩላቸው ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ለረጅም ጊዜ የዘለቀ ግንኙነት እንዳለትና በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በትብብር እየሰሩ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ የእንፋሎት ሀብትን ለማልማት የምታደርገውን ጥረት በአቅም ግንባታ ሥልጠናዎች እየደገፈች የምትገኘው ኒውዚላንድ በእንፋሎት ኃይል ቴክኖሎጂ ላይ ያላትን የዳበረ ልምድ እንዳላት ለማካፈል ከኢትዮጵያ ጋር አብራ በመስራቷ ደስተኛ መሆናቸውንም ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅት እየተሠጠ ያለው ስልጠናም ለእቀወቀትና ቴክኖሎጅ ሽግግሩ ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል፡፡ በቀጣይ ዘርፉን ለማልማት እየተሰራ ያለውን የአቅም ግንባታ ስራ እና አብሮ የመስራት ልምድን ሀገራቸው አጠናክራ እንደምትቀጥልም አምባሳደሩ አረጋግጠዋል፡፡ ስልጠናውን ስምንት የእንፋሎት ኃይል ጉድጓድ ቁፋሮ ባለሙያዎች እየተከታተሉት መሆኑን ማወቅ ተችሏል። በኢትዮጵያ የስምጥ ሸለቆ አካባቢዎች ለእንፋሎት ኃይል ማመንጫ የሚውል እምቅ ሀብት ያለባቸው 24 ቦታዎች በጥናት መለየታቸውን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 20 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+4

የኢትዮ-ኬንያ የኃይል ሽያጭ ስምምነት ተጠናቀቀ ………………///…………… ለዓመታት ድርድር ሲደረግበት የቆየው የኢትዮ- ኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ስምምነት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ ስምምነቱን የኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እና የኢፌዲሪ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እዮብ ተካልኝ በተገኙበት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የኬንያ ኤሌክትሪክ መብራትና ኃይል ኩባንያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ኢንጂነር ጎፌሪ ሙሊ ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ ኢትዮጵያ አሁን ላይ 200 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለኬንያ ለመሸጥ የሚያስችላት ሲሆን በቀጣይ ደግሞ ኢትዮጵያ ለኬንያ የምታቀርበውን የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን እስከ 400 ሜጋ ዋት ከፍ ለማድረግ ያለመ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር እያካሔደች የምትገኘው የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ስምምነት በሀገራቱ መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ትስስር ይበልጥ እንዲጠናከር ከማድረጉም ባሻገር ፋይዳው የጎላ እንዲሆን አድርጎታል፡፡ ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከሱዳን እና ጅቡቲ ጋር የኃይል ሽያጭ እያካሄደች ሲሆን ከሶማሌ ላንድ፣ ታንዛኒያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ለማከናወን የመግባቢያ ስምምነት ፈርማለች፡፡ የግንባታ ሥራው በ2008 ዓ.ም የተጀመረው የኢትዮ-ኬንያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ከ183 ሚሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ ተገንብቶ መጠናቀቁን ከዚህ በፊት መዘገባችን ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 20 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+4

አዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫጣቢያ በበጀት ዓመቱ 133.75 ጊጋ ዋት ሰዓት ማመንጨት መቻሉን አስታወቀ ……….////…….. አዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በበጀት ዓመቱ 144 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማመንጨት አቅዶ 133 ነጥብ 75 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማመንጨቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጇ ወ/ሮ አይናለም ወልደሚካኤል እንደገለፁት ጣቢያው የዕቅዱን 92.88 በመቶ ማሳካት ችሏል። የጣቢያውን አሰራር ለማዘመን የመለዋወጫ ዕቃዎች ዳታ ቤዝ መዘጋጀቱን የገለፁት ወ/ሮ አይናለም የጥገና ሥራዎችን የሚያቀላጥፉ እና ጉልበት የሚቀንሱ ማሽኖችን በጣቢያው ወርክሾፕ መሰራቱን አስታውቀዋል። የተለያዩ የኃይል ማመንጫ ዕቃዎች ጥገና በራስ ኃይል በማከናወን ከ100 ሺህ ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ ማዳናቸውንም ነው ስራ አስኪያጇ የገለፁት። ከኃይል ማምረት ጎን ለጎን የቅድመ መከላከል፣ የኢንስፔክሽን እና የጥገና ሥራዎችን ከዕቅድ በላይ ማከናወን መቻሉን ጣቢያው አስታውቋል። እንደ ወ/ሮ ዓይናለም ገለፃ ኃይል ከማመንጨት ባሻገር ጣቢያው ለአካባቢው ማህበረሰብ የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን ከ25 ኪሎ ሜትር በላይ መንገድ ገንብቶ ለአካባቢው ማህበረሰብ የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። 51 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው አዳማ 1 በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 18 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+1

በአሜሪካ ኦሪገን ሲካሄድ በሰነበተው 18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በወንዶች እና ሴቶች ማራቶን እንዲሁም በ10ሺ እኛ 5 ሺ ሜትር ሴቶች 4 ወርቅ አግኝታለች፡፡ በ3 ሺ ሜትር መሰናክል
+1
በአሜሪካ ኦሪገን ሲካሄድ በሰነበተው 18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በወንዶች እና ሴቶች ማራቶን እንዲሁም በ10ሺ እኛ 5 ሺ ሜትር ሴቶች 4 ወርቅ አግኝታለች፡፡ በ3 ሺ ሜትር መሰናክል በሴት እና ወንድ እንዲሁም በወንዶች ማራቶን እና በ1500 ሜትር ሴቶች የብር ሜዳሊያ ተገኝቷል፡፡ በሴቶች 3ሺ መሰናክል እና በ5ሺ ሜትር ሁለት የነሐስ ሜዳያ የተገኘ ሲሆን በድምሩ 10 ሜዳሊያዎችን በማግኘት ከአፍሪካ ቀዳሚ፣ ከዓለም ደግሞ ከአሜሪካ በመቀጠል 2ኛ ደረጃ ላይ በመቀመጥ በሻምፒዮናው ታሪክ ከፍተኛው ሜዳሊያ በማግኘት አጠናቃለች፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 18 ቀን 2014 ዓ.ም

🇪🇹 ኢትዮጵያ በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶች 5 ሺህ ሜትር ውድድር በአትሌት ጉዳፍ ፀጋይ እና ዳዊት ስዩም አማካኝነት ተጨማሪ የወርቅ እና የነሃስ ሜዳሊያ አግኝታለች። እንኳን ደስ አለን! �
🇪🇹 ኢትዮጵያ በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶች 5 ሺህ ሜትር ውድድር በአትሌት ጉዳፍ ፀጋይ እና ዳዊት ስዩም አማካኝነት ተጨማሪ የወርቅ እና የነሃስ ሜዳሊያ አግኝታለች። እንኳን ደስ አለን! 🇪🇹

photo content
+2

የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆት በሪጅኑ የኦፕሬሽን ስራዎች ላይ ፈተና ሆኗል ……///…… በኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ እየተፈጸመ ያለው ስርቆት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የኦፕሬሽን ስራዎች ላይ ፈተና ሆኖ እንደነበር በኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የአዲስ አበባ ሪጅን አስታወቀ፡፡ የሪጅኑ የስራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በበጀት ዓመቱ አፈፃፀም እና በ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት አካሂደዋል፡፡ በውይይቱ ላይ የተገኙት የሪጅኑ የትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን መምሪያ ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ዮሐንስ ተስፋዬ እንደተናገሩት በማስተላለፊያ መስመር ምሶሶዎች ላይ እየተፈጸመ ያለው የስርቆት ወንጀል በኦፕሬሽን ስራዎች ላይ ፈተና ሆኗል፡፡ ተወካይ ዳይሬክተሩ እንዳሉት በበጀት ዓመቱ በሪጅኑ በሚገኙ የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ የስርቆት ወንጀሎች በመበራከታቸው ምክንያት፤ መስመሩን ለመጠገን ሲባል ኃይል የሚቋረጥበት የሰዓት ድግግሞሽ ጨምሯል፡፡ ይህም አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ በሚሰራው ስራ ላይ እንቅፋት ፈጥሮ ነበር ብለዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ በ50 የማስተላለፊያ መስመር መሶሶዎች ላይ የተለያየ መጠን ያላቸው የስርቆት ወንጀሎች መፈጸማቸውንም ተጠቁሟል፡፡ የኦፕሬሽን ስራውን አስተማማኝ ለማድረግ በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ መደበኛና አስቸኳይ የፍተሻና የጥገና ስራዎች መከናወናቸውን የተናገሩት ተወካዩ የጥገና ሥራውን በተያዘው መርሃ ግብር መሰረት ለመፈጸም ከካሳ ክፍያ ጥያቄዎች ጋር በተያየዘ የሚስተዋሉ የወሰን ማስከበር ችግሮች እንቅፋት እንደነበሩም አመልክተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እያስተዳደራቸው የሚገኙ የ15 እና የ33 ኪሎ ቮልት የስርጭት መስመሮች የሚያጋጥማቸው ችግር መደጋገም የኦፕሬሽን ስራውን ከማደናቀፍ በዘለለ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሥር ባሉ ከፍተኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለተለያዩ ዕቃዎች መበላሸት ምክንያት ሆኗል፡፡ የኦፕሬሽን ስራውን ለማዘመን የመቆጣጠሪያ ዘዴዎችን፣ የፕሮቴክሽን ሲስተሙንና በሌሎች ጉዳዮች ላይ ዘመናዩ የሆኑ የተለያዩ መሳሪያዎችን ለመጠቀም እንቅስቃሴ ሲደረግ እንደነበርም ተወካይ ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ በ2015 በጀት ዓመት የታቀደውን ለማሳካትና የኦፕሬሽን ስራውን አስተማማኝ ለማድረግ ከስርቆት፣ ከወሰን ማስከበር፣ ከመለዋወጫ እቃዎች አቅርቦት እና ከ15ና 33 ኪሎ ቮልት የማሰራጫ መስመሮች ጋር በተያያዘ ያሉ ችግሮች ዘላቂ መፍትሔ ሊሰጣቸው እንደሚገባ አቶ ዮሐንስ ተናግረዋል፡፡ የውይይቱ ተሳታፊዎች በቀረበው የ2014 ሪፖርት እና በ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ የኦፕሬሽንና አስተዳደራዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ አስተያየቶችንና ጥያቄዎችን አቅርበው ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ሪጅኑ የተለያየ የኪሎ ቮልት መጠን ያላቸውን 31 ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና 1 ሺህ 444 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን በማስተዳደር መደበኛና አስቸኳይ የፍተሻና የጥገና ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ በየዓመቱ በሀገሪቱ ከሚመረተው የኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ እስከ 45 በመቶ የሚሆነውን የሚጠቀመው የአዲስ አበባ ሪጅን እንደሆነ በውይይቱ ወቅት ተጠቅሷል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም

የቃል ፈተና ጥሪ ማስታወቂያ በቻይልድኬር ጊቨርስ የሥራ መደብ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ግንቦት 08 ቀን 2014 ዓ.ም ማስታወቂያ ወጥቶ ሐምሌ 12 ቀን 2014 ዓ.ም የጽሑፍ ፈተና መሰጠቱ ይታወቃል፡፡ ሆ
የቃል ፈተና ጥሪ ማስታወቂያ በቻይልድኬር ጊቨርስ የሥራ መደብ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ግንቦት 08 ቀን 2014 ዓ.ም ማስታወቂያ ወጥቶ ሐምሌ 12 ቀን 2014 ዓ.ም የጽሑፍ ፈተና መሰጠቱ ይታወቃል፡፡ ሆኖም የጽሑፍ ፈተና ከወሰዳችሁት ውስጥ የማለፊያ ነጥብ ያመጣችሁ ተወዳዳሪዎች የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች በተገለፀው መሰረት ሐምሌ 21 ቀን 2014 ዓ.ም የቃል ፈተና የሚሰጥ ስለሆነ በዋና መስሪያ ቤት ኬኬር ህንፃ ሁለተኛ ፎቅ ሰራተኛ ምደባ ቢሮ ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ላይ እንድትገኙ እናስታውቃለን፡፡

ከ71 በመቶ በላይ ክፍት የሥራ መደቦች በውስጥ ዕድገት፣ በዝውውርና በምደባ እንዲሟላ ተደርጓል -----//////------- በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 1 ሺህ 205 ክፍት የሥራ መደቦች በውስጥ ሰራተኞች እንዲሟሉ ማድረጉን በኢትዮዽያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስፈፃሚው አቶ አታላይ አበበ እንደገለፁት 932 የሥራ መደቦች በዕድገት፣166 የሥራ መደቦች በዝውውር እንዲሁም 107 መደቦች በምደባ እንዲሟሉ ተደርጓል፡፡ በበጀት ዓመቱ የሥራ መደቦቹን በተፈላጊ ሰው ለማሟላት በተሰራው ሥራ 71 ነጥብ 9 በመቶ ያህሉ ክፍት ቦታዎች ከተቋሙ ሠራተኞች በዕድገት፣ በዝውውርና በምደባ የተሟሉ ሲሆን 6 ነጥብ 03 በመቶው ደግሞ በውጪ ቅጥር የተሟሉ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ አንዳንድ የሥራ መደቦችን በሶስተኛ ወገን ለማሰራት በተያዘው አቅጣጫ መሰረት በበጀት ዓመቱ 349 የጥበቃ፣10 የአትክልተኛ እና 10 የፅዳት መደቦች በሶስተኛ ወገን እንዲሟሉ ተደርጓል ብለዋል፡፡ የሰው ኃይል ፍላጎትን ከክፍሎች የሰው ኃይል ዕቅድ ጋር በማጣጣም በተቋሙ የሰው ኃይል ምደባ አፈፃፀም መመሪያ መሰረት ከማከናወን አንፃር የተያዘው ዕቅድ 92 ነጥብ 9 በመቶ መሳካቱን ሥራ አስፈፃሚው አመልክቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+1

ተቋሙ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የ95 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ኢነርጂ ኤክስፖርት አድርጓል ……..////……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተጠናቀቀው የ2014 በጀት ዓመት ለጎረቤት ሀገራት የ95 ነጥብ 45 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ማከናወኑን የማርኬቲንግ እና ቢዝነስ ልማት መምሪያ አስታወቀ፡፡ በበጀት ዓመቱ ለሱዳን እና ጅቡቲ 1 ሺህ 636 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ 89 ነጥብ 6 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ከ1 ሺህ 7 መቶ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኤሌክትሪክ በማቅረብ የ95 ነጥብ 4 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሽያጭ መከናወኑን መምሪያው አስታውቋል፡፡ ይህም ከዕቅዱ የ5 ነጥብ 84 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ብልጫ እንዳለው ለማወቅ ተችሏል፡፡ ወደ ሀገራቱ በተናጠል ለሱዳን 1 ሺህ 109 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ በማቅረብ የ54 ነጥብ 66 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም ለጅቡቲ 6 መቶ አስራ አንድ ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ በማቅረብ የ40 ነጥብ 78 ሚሊዮን ዶላር ሽያጭ ተከናውኗል፡፡ ተቋሙ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለውጭ ሀገራት ያቀረበው የኃይል ሽያጭ ከ2013 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ5 ነጥብ 4 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ብልጫ አለው፡፡ ለበጀት ዓመቱ ዕቅድ መሳካት እና የሽያጭ ዕድገት የኃይል ማመንጫ ግድቦች በቂ ውሃ መያዛቸው እና የኃይል መቆራረጥ መቀነሱ በምክንያትነት ይጠቀሳሉ፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ 94 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን መምሪያው አስታውቋል፡፡ ገቢው የተሰበሰበው ለኢትዮ-ቴሌኮም፣ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እና ዌብስብሪክስ አይቲ ሶሊዩሽን ከተጠቀሙበት የፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content

photo content

የፈተና ውጤት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የካቲት 25 ቀን 2014 ዓ.ም በሪሼፕሽን 1ኛ የሥራ መደብ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም ከተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው በተሰጠው ፈተና ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከሐምሌ 18 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በዋና መስሪያ ቤት ኬኬር ህንፃ ሁለተኛ ፎቅ የሰራተኛ ምደባ ቢሮ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናስታውቃለን፡፡