ar
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

الذهاب إلى القناة على Telegram

Addis abeba Ethiopia

إظهار المزيد
4 770
المشتركون
-23224 ساعات
-1 7917 أيام
-3 26430 أيام
أرشيف المشاركات
ግብጽ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ጉዳይ ከአምስት ሀገራት ጋር ምክክር ጀመረች ፕሬዝዳንት አልሲሲ የሚመሩት ይህ መድረክ ኒው አላሜን በተሰኘችው የወደብ ከተማ እየተካሄደ ነው ግብጽ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ጉዳይ ከአምስት የአረብ ሀገራት ጋር ምክክር ጀመረች፡፡ የግብጹ ፕሬዝዳንት ያዘጋጁት የአረብ ጉባኤ በሜድትራኒያኗ የወደብ ከተማ ኒው አላሜን ከተማ በመካሄድ ላይ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ በዚህ ጉባኤ ላይ ግብጽን ጨምሮ ባህሬን፣ ኢራቅ፣ አረብ ኢምሬት እና ጆርዳን የተሳተፉ ሲሆን የጉባኤው አጀንዳ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዋነኛው እንደሆነ ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ መሪዎቹ በዚህ ጉባኤ ላይ ከህዳሴው ግድብ በተጨማሪም በየመን፣ ሶሪያ እና ሊቢያ ስላሉ ግጭቶች ጉዳዮች እንደሚወያይም በዘገባው ላይ ተጠቅሷል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የእስራኤል ጋዛ ጦርነት፣ ሌላኛው የጉባኤው አጀንዳ እንደሚሆን የተጠቀሰ ሲሆን በዚህ ጉባኤ ላይ ሌሎች የአረብ ሊግ አባል ሀገራት ስለመሳተፋቸው አልተጠቀሰም፡፡ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ካሉት 13 ተርባይኖች መካከል ዩኒት 9 የሚባለው ሁለተኛው ተርባይን የተሳካ ተከላ እና ሙከራ ከተደረገ በኋላ ኃይል የማመንጨት ስራው ባሳለፍነው ሳምንት መጀመሩ ይታወሳል፡፡ ይህ የግድቡ ሁለተኛው ዩኒት 270 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳለው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በምረቃው ወቅት ገልጸዋል። ባሳለፍነው የካቲት ወር 2014 ዓ.ም ግድቡ ካሉት ተርባይኖች ውስጥ አንዱ የሆነው እና ዩኒት 10 የሚል መጠሪያ ያለው ተርባይን 270 ሜጋ ዋት ኃይል ማመንጨት መጀመሩ ይታወሳል። ይህን ተከትሎም ታላቁ የኢትዮጵ ህዳሴ ግድብ የዛሬውን ጨምሮ በአጠቃላይ 540 ሜጋዋት የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት ላይ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማብሰሪያ ስነ ስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር በሶስተኛው ዙር ውሃ ሙሌት 22 ቢሊየን ሜትር ኪዩብ ገደማ ውሃ መያዝ የሚያስችል እና ሁለት ተርባይኖችን ማንቀሳቀስ የሚያስችል ስራ መሰራቱን አስታውቀዋል “ሆኖም የታችኛው ተፋሰስ ሀገራተ ላይ የውሃ እጥረት እንዳያጋጥም ኢነርጂ እያመነጨን በታቸኛው ውሃ ማስተንፈሻ (ቦተም አውት ሌት) በኩል ውኃ በከፍተኛ ሁኔታ አንድም ቀን ሳይቋረጥ እንዲሄድ እየተደረገ ነው” ሲሉ አክለዋል። ኢትዮጵያ፣ሱዳንና ግብጽ በግድቡ አስተዳደር ጉዳይ ዙሪያ የሶስትዮች ንግግር እና ድርድር ከመጀሩ ዓመታት ቢያስቆጥሩም እስካሁን ወደ ስምምነት አልመጡም፡፡

የማለዳ ዐበይት ዜናዎች 1፤ የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ለሁለት ዓመት ያዘገየውን የዞን አደረጃጀት በተያዘውሳምንት እንደሚያጸድቅ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል። አዲሶቹ አራት ዞኖች፣ ሰሜን ሲዳማ፣ ምሥራቅ ሲዳማ፣ ማዕከላዊ ሲዳማ እና ደቡብ ሲዳማ ተብለው ተከፍለዋል። ሀዋሳ፣ አለታ ወንዶ፣ ይርጋለም እና ዳዬ ከተሞች ደሞ የዞኖቹ ማዕከሎች ሲሆኑ፣ ሀዋሳ የከተማ አስተዳደር ትሆናለች። የክልሉ መንግሥት የዞን አደረጃጀት ጥያቄውን እስካሁን ያቆየው፣ ክልሉ በሁለት እግሩ እስኪቆም ድረስ እንደሆነ የክልሉ ምክር ቤት ምንጮች ተናግረዋል። 2፤ የሱማሊያው ጠቅላይ ሚንስትር ሐምዛ አብዲ ባሬ አልሸባብ በሞቃዲሾው አያት ሆቴል ለፈጸመው እገታና ጥቃት መንግሥታቸው ሃላፊነት እንደሚወስድ መናገራቸውን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ባሬ ከጥቃቱ ጋር በተያያዘ ሃላፊነታቸውን ያልተወጡ የመንግሥት ባለሥልጣናት ተጠያቂነት አይቀርላቸውም ብለዋል። ጸጥታ ኃይሎች 21 ሰዎች የተገደሉበትንና 117 ሰዎች የቆሰሉበትን ጥቃት ለመመከት ቅንጅት እንዳልነበራቸው ታዛቢዎች ተናግረዋል። 3፤ ሱዳን በጎርፍ በተጠቁ ስድስት ግዛቶቿ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጇን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀው፣ በሪቨር ናይል፣ ገዚራ፣ ዋይት ናይል፣ ዌስት ኮርዶፋን፣ ሳውዝ ዳርፉር እና ከሰላ ግዛቶች ነው። መንግሥት ለጎርፉ ተጎጅዎች የአስቸኳይ ሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦቶችን ማስተባበር ጀምሯል። በጎርፉ እስካሁን 80 ሰዎች ሕይወታቸውን ያጡ ሲሆን፣ ከ136 ሺህ በላይ ሰዎች ደሞ ለጉዳት ተዳርገዋል። ክከፍተኛ ዝናብ መጣሉና የጎርፍ አደጋው እስከ ጥቅምት ይቀጥላል ተብሎ ይጠበቃል። 4፤ የናይል ተፋሰስ አገሮች የሆኑት ታንዛኒያ፣ ሩዋንዳ እና ቡሩንዲ በጋራ ያስገነቡት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ 95 በመቶ መጠናቀቁን የታንዛኒያው ሲትዝን ጋዜጣ ዘግቧል። በታንዛኒያ እና ሩዋንዳ ድንበር ላይ የተገነባው የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 80 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ያመነጫል ተብሎ ይጠበቃል። ግንባታው የተከናወነው፣ ከዓለም ባንክ፣ የአፍሪካ ልማት ባንክና ከሌሎች ምንጮች በተገኘ 468 ሚሊዮን ዶላር ብድርና ዕርዳታ ነው። [ዋዜማ ራዲዮ]

አፍሪካዊያን በምግብ ራሳቸውን ለመቻል ከኢትዮጵያ ትምህርት ሊወስዱ እንደሚገባ ቢዝነስ ደይሊ አመላከተ አፍሪካዊያን በምግብ ራሳቸውን ለመቻል ከኢትዮጵያ ትምህርት ሊወስዱ እንደሚገባ የቢዝነስ ደይሊ ዘገ
አፍሪካዊያን በምግብ ራሳቸውን ለመቻል ከኢትዮጵያ ትምህርት ሊወስዱ እንደሚገባ ቢዝነስ ደይሊ አመላከተ አፍሪካዊያን በምግብ ራሳቸውን ለመቻል ከኢትዮጵያ ትምህርት ሊወስዱ እንደሚገባ የቢዝነስ ደይሊ ዘገባ አመላከተ። ቢዝነስ ዴይሊ በዘገባው እንደገለጸው በአለም በተፈጠረው የምግብ እጥረት በተለይም በሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ምክንያት የአፍሪካ አህጉር በምግብ እጥረት እየተፈተነ መሆኑን ጠቅሶ፤ ኢትዮጵያ ግን በምግብ ፍጆታ ራሷን ለመቻል በተለይም የስንዴ ምርትን በኩታ ገጠም እርሻ በስፋት እያመረተች እንደምትገኝና ከዚህ ተግባሯም አፍሪካዊያን ተሞክሮዋን ሊወስዱ እንደሚገባ አትቷል። በሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ምክንያት በአፍሪካ የምግብ እጥረት መከሰቱን የጠቀሰው ዘገባው፤ የምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ኢትዮጵያ ግን አዲስ ስትራቴጅ በመንደፍ የስንዴ ምርትን ከመቼውም ጊዜ በላይ በስፋት እያመረተች መሆኗን ጠቅሷል። በዚህም ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2021 የነበራትን የ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ቶን የስንዴ ምርት ወደ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ቶን ስንዴ ከፍ በማድረግ ማምረት መቻሏን ገልጿል። ኢትዮጵያ በ2023 በምግብ ራሷን ለመቻልና ለአፍሪካ ሀገራት ስንዴን ኤክስፖርት ለማድረግ አቅዳ እየሰራች መሆኑንም ዘገባው አስታውሷል። የቢዝነስ ዴይሊ ጸሀፊ አክለውም አፍሪካዊያን ስንዴን ከውጭ ከማስገባት ይልቅ ያላቸውን አቅምና ሀብት ተጠቅመው በምግብ ራሳቸውን ሊችሉ እንደሚገባ አመላክቷል።

ዩክሬን 9ሺህ ወታደሮቿ በሩሲያ ጦር እንደተገደሉባት ገለጸች አንድ ሚሊዮን ዩክሬናዊያን የሩሲያን ጦር እየተዋጉ እንደሆነ ተገልጿል ዩክሬን ዘጠኝ ሺህ ወታደሮቿ በሩሲያ ጦር እንደተገደሉባት ገለጸች። ዩ
ዩክሬን 9ሺህ ወታደሮቿ በሩሲያ ጦር እንደተገደሉባት ገለጸች አንድ ሚሊዮን ዩክሬናዊያን የሩሲያን ጦር እየተዋጉ እንደሆነ ተገልጿል ዩክሬን ዘጠኝ ሺህ ወታደሮቿ በሩሲያ ጦር እንደተገደሉባት ገለጸች። ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃልኪዳን ጦር ወይም ኔቶን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ከሩሲያ ጋር ጦርነት ከጀመረች ዛሬ ስድስት ወራት አስቆጥሯል። በዚህ ጦርነት ምክንያት ከ10 ሚሊዮን በላይ ዩክሬናዊያን ወደ ጎረቤት ሀገራት ሲሰደዱ በዓለም ላይ ደግሞ የነዳጅ እና ምግብ ዋጋ እንዲጨምር አድርጓል። የዩክሬን መከላከያ ዋና አዛዥ ቫለሪ ዛሉዚኒ ስድስት ወራት ባስቆጠረው ጦርነት ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ዋና አዛዡ በመግለጫቸው እስካሁን ዘጠኝ ሺህ የዩክሬን ወታደሮች በሩሲያ ጦር መገደላቸውን ተናግረዋል ብሎ ሮይተርስ ዘግቧል። ሀገራቸውን ከሩሲያ ለመጠበቅም አንድ ሚሊዮን ዩክሬናዊያን በሁሉም ግንባሮች ከሩሲያ ጦር ጋር እየተዋጉ እንደሆነም አዛዡ አክለዋል። አሜሪካንን ጨምሮ የአውሮፓ ሀገራት በሩሲያ ላይ ማዕቀቦችን በመጣል ላይ ሲሆኑ በሌላ በኩል ደግሞ ለዩክሬን የጦር መሳሪያ በመለገስ ላይ ናቸው። አሜሪካ ከሰሞኑ ለዩክሬን ተጨማሪ 800 ሚሊዮን ዶላር ዋጋ ያላቸው የጦር መሳሪያ ድጋፍ አጽድቃለች። ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ከሩሲያ ጋር ቀጥታ ጦርነት ውስጥ ላለችው ዩክሬን ተጨማሪ 800 ሚሊዮን ዶላር ዋጋ ያላቸው የጦር መሳሪያ ድጋፍ ፈርመዋል። አሜሪካ የጦር መሳሪያውን ድጋፍ ያደረገችው ዩክሬን የኑክሌር ጥቃት ከሩሲያ ሊያጋጥማት ይችላል በሚል ነው።

ነሐሴ 16 ቀን 2014 ዓ.ም የመከላከያ ፋዉንዴሽን የሰራዊቱን የቤት ፍላጎት ለማሟላት ከኦቪድ ግሩፕ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ጋር ዉል ተፈራረመ፡፡ የመከላከያ ፋዉንዴሽን ዋና ስራ አስኪያጅ
ነሐሴ 16 ቀን 2014 ዓ.ም የመከላከያ ፋዉንዴሽን የሰራዊቱን የቤት ፍላጎት ለማሟላት ከኦቪድ ግሩፕ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ጋር ዉል ተፈራረመ፡፡ የመከላከያ ፋዉንዴሽን ዋና ስራ አስኪያጅ ሜ/ጀኔራል ኩምሳ ሻንቆ እንደተናገሩት ሰራዊታችን በግዳጅ ላይ እያለ ስለ ቤት እና ቤተሰብ አኗኗር እንዳያስብ ደረጃዉን የጠበቀ ቤት ገንብተን ለማስረከብ እየሠራን ነው። 17ሺ የመከላከያ ሰራዊት የመኖሪያ ቤት ለማግኘት መመዝገባቸዉን የገለፁት የፋዉንዴሽኑ ምክትል ሥራ አስፈጻሚ ኮ/ል ታደሰ ጌታቸዉ ከዚህ ውስጥ 20% ቅድመ ክፍያ ከፍለው የተመዘገቡ ከ4 ሺህ በላይ መሆናቸውን እና ከ11ሺህ በላይ ደግሞ ቅድመ ክፍያውን ሳያሟሉ የተመዘገቡ መሆናቸውን ገልፀዋል። ኮ/ል ታደሰ ጌታቸዉ አክለውም የሰራዊቱ ቤተሰብ የቤት ባለቤት ሲሆን በግዳጅ ለይ ያለዉ ሰራዊት ስለ ቤተሰብ ማሰብ ትቶ ከመንታ ሃሳብ በመላቀቅ ግዳጁን ብቻ በብቃት እንዲወጣ ያግዘዋል ብለዋል፡፡ የኦቪድ ግሩፕ ግምባታዉን በ14 ወራት ወስጥ አጠናቆ እንደሚያስረክብ እና አጠቃላይ ለግምባታዉ የሚያስፈልጉ 1.7 ቢሊየን ብር በላይ በቅድመ ክፍያ ግምባታዉን እንደሚጀምር የኦቪድ ግሩፕ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዮናስ ታደሰ ተናግረዋል፡፡ ዋና ሥራ አስኪያጁ በተለይም በዚህ ወቅት ለጀግናዉ መከላከያ ሰራዊት የመኖሪያ ቤት ለመገንባት እድሉን ስላገኘን ደስተኞች ነን ብለዋል፡፡ ግምባታዉንም በተያዘለት ቀነ ገደብ አጠናቆ ለማስረከብ ሃያ አራት ስዓት ያለ እረፍት እንደሚሰሩ አቶ ዮናስ ታደሰ ገልጸዋል፡፡

ለመከላከያ ሠራዊት አባላት መኖሪያ ቤት ለማስገንባት የሚያስችል ስምምነት ተካሄደ!! የግንባታ ውሉን የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሜጀር ጄኔራል ኩምሳ ሻንቆ እና የኦቪድ ኮንስትራክ
ለመከላከያ ሠራዊት አባላት መኖሪያ ቤት ለማስገንባት የሚያስችል ስምምነት ተካሄደ!! የግንባታ ውሉን የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሜጀር ጄኔራል ኩምሳ ሻንቆ እና የኦቪድ ኮንስትራክሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዮናስ ታደሰ ተፈራርመዋል። የሚገነቡት ቤቶች ባለ ሦስት እና አራት መኝታ ሲሆኑ በ14 ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቁም በሥነ ሥርዓቱ ወቅት ተጠቁሟል። ቤቶቹም ባለ ሰባት ወለል 128 ቤቶች እና ባለ ዘጠኝ ወለሉ ደግሞ 120 ቤቶች መሆናቸው ተገልጾ ኩምካንግ አሉሚኒየም ፎርምወርክ በተባለ ቴክኖሎጂ እንደሚገነቡ ተነግሯል። በአጠቃላይ 248 ቤቶች የሚገነቡ ሲሆን ከ1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደሚደረግባቸውም ተገልጿል።የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ዛሬ ከተፈጸመው ውሉ በተጨማሪ በአዲስ አበባ፣ ሐዋሳ፣ አዳማ፣ ቢሾፍቱ እና ባሕርዳር ከተሞች ከ2100 ቤቶች በላይ በመገንባት ላይ መሆኑም ተገልጿል።

ሩሲያ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ሰላም ለማስፈን የጀመረውን ጥረት በአወንታዊንት እንደምትመለከት አስታወቀች የፌደራል መንግስት የተናጠል ተኩስ አቁም ማወጁ፣ ተጥሎ የነበረውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማንሳት
ሩሲያ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ሰላም ለማስፈን የጀመረውን ጥረት በአወንታዊንት እንደምትመለከት አስታወቀች የፌደራል መንግስት የተናጠል ተኩስ አቁም ማወጁ፣ ተጥሎ የነበረውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማንሳት፣ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ለመጀመር በሂደት ላይ መሆኑ እና ሌሎች የሰላም አማራጮች እየተከተለ መሆኑ ግጭቱን ለማስቆም ጥሩ እርምጃ መሆኑንም ሩሲያ አክላለች። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ከህወሃት ጋር የተደረገውን ጦርነት ለመፍታት እየሄደችበት ያለውን ሂደት እንደምታደንቅ የገለጸችው ሩሲያ የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ መልዕክተኛ ኦልሴጎን ኦባሳንጆ በኩል እየተካሄዱ ያሉ ጥረቶችን እንደምትደግፍም ገልጻለች።

የግብፅ፣ የሳዑዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች፣ የግሪክ እና የግሪክ የቆጵሮስ አስተዳደር ልዩ ሃይሎች ዛሬ እሁድ እለት የጋራ ወታደራዊ ልምምድ መጀመራቸውን የግብፅ ጦር አስታወቀ። የወታደራዊ
የግብፅ፣ የሳዑዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች፣ የግሪክ እና የግሪክ የቆጵሮስ አስተዳደር ልዩ ሃይሎች ዛሬ እሁድ እለት የጋራ ወታደራዊ ልምምድ መጀመራቸውን የግብፅ ጦር አስታወቀ። የወታደራዊ መግለጫው ሄርኩለስ-2022 በመሀመድ ናጊብ ወታደራዊ ጣቢያ እና በሰሜናዊ ወታደራዊ ዞን ውስጥ ባሉ ሌሎች የስልጠና ቦታዎች ለብዙ ቀናት እንደሚቀጥል ገልጿል። አሜሪካ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ባህሬን በታዛቢነት በስልጠናው እየተሳተፉ ነው። የልምምዱ የመጀመሪያ ምዕራፍ ፅንሰ ሀሳቦችን አንድ ለማድረግ ያለመ ሲሆን በስልጠናው ላይ ጥቅም ላይ የሚውሉ የጦር መሳሪያዎችና መሳሪያዎች ኤግዚቢሽን እንዲሁም በሳይበር ደህንነት እና በአለም አቀፍ የሰብአዊ ህጎች ዙሪያ ትምህርቶችን ያካተተ ነው ብሏል። ሄርኩለስ-2021 የግብፅ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ሃይሎች የተሳተፉበት ባለፈው አመት መስከረም ወር በግሪክ ተካሂዷል።

ሸኔ በዚሁ መልኩ እየተደመሰሰ ይገኛል። በወያኔ ሳንባ የሚተነፍሰው አሸባሪው ሸኔ በአሁኑ ወቅት አንድ በአንድ እየተለቀመ ይገኛል። አብዛኞቹ ደግሞ እየሆነ ያለውን ሂደት እያዩ እጃቸውን እየሰጡ ይገኛሉ
+3
ሸኔ በዚሁ መልኩ እየተደመሰሰ ይገኛል። በወያኔ ሳንባ የሚተነፍሰው አሸባሪው ሸኔ በአሁኑ ወቅት አንድ በአንድ እየተለቀመ ይገኛል። አብዛኞቹ ደግሞ እየሆነ ያለውን ሂደት እያዩ እጃቸውን እየሰጡ ይገኛሉ። 🙏 ድል ለጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን 🙏

✍️ቤተሰብ ይሁኑ! 👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
+9
✍️ቤተሰብ ይሁኑ! 👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter

ሩሲያ፤ ጥቃት ሊያደርስብኝ ነበር ያለችውን ድሮን መምታቷን ገለጸች ዩክሬን ስለጉዳዩ እስካሁን ያለችው ነገር የለም የሩሲያ እና የዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ 178 ቀናት ተቆጥረዋል የሩሲያ ጦር ፤ በጥቁ
ሩሲያ፤ ጥቃት ሊያደርስብኝ ነበር ያለችውን ድሮን መምታቷን ገለጸች ዩክሬን ስለጉዳዩ እስካሁን ያለችው ነገር የለም የሩሲያ እና የዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ 178 ቀናት ተቆጥረዋል የሩሲያ ጦር ፤ በጥቁር ባሕር ኃይል ማዘዣ ጣቢያ ላይ ጥቃት ሊያደርስ እንደነበር የገለጸውን ድሮን መምታቱን አስታወቀ፡፡ ከዚህ በፊት የዩክሬን ጦር በክሬሚያ የሚገኘውን የሩሲያ ጦር መርከብ በድሮን መምታቱን ገልጾ የነበረ ሲሆን ሞስኮ ደግሞ ዛሬ ድሮን መምታቷን ገልጻለች፡፡ ሩሲያ ድሮኑን መምታቷን የገለጸችው በክሬሚያ ግዛት በምትገኘው ሴቫስቶፖል ከተማ ውስጥ ነው፡፡ የሴባስቶፖል ከተማ አስተዳዳሪ ሚካሄል ራዝቮጃቭ፤ ድሮኑ ሩሲያ ላይ ጥቃት ለመሰንዘር የተላከ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ድሮኑ ተመቶ በወደቀበት አካባቢ ትልቅ ጉዳት እንዳስከተለም ነው አስተዳዳሪው የተናገሩት፡፡ እንደተመታ እና እንደወደቀ የተገለጸው ድሮን በክሬሚያ ያለውን የሩሲያ ባህር ኃይልን ለማጥቃት የተላከ እንደነበር ሞስኮ ገልጻለች፡፡ ለዚህ ማሳያ ተደርጎ የተቀመጠው ደግሞ በፈረንጆች ሃምሌ 31 ቀን፤ ዩክሬን የሩሲያን የባህር ሃይል በድሮን ማጥቃቃቷ ነው፡፡ የሩሲያ መከላከያ መስሪያ ቤት፤ ዩክሬን ባለፈው ወር የሩሲያን ባህር ኃይል ማጥቃቱን ቀድሞ በመረዳቱ ጥቃቱን ማክሸፉን ገልጿል፡፡ በዚህም ምክንያት የሀገሪቱ አየር ኃይል ድሮኑ ጥቃት ከማድረሱ አስቀድሞ መቶ መጣሉ ነው የተገለጸው፡፡ የድሮኑን መመታት የገለጸው የሩሲያ ጦር ሲሆን፤ ከዩክሬን በኩል እስካሁን የተሰማ ነገር ስለመኖሩ የዜና ምንጮች የጠቀሱት ነገር የለም፡፡ የሩሲያ እና የዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ 178 ቀናት ተቆጥረዋል፡፡ በእስካሁኑ ሂደት የጥራጥሬ ምርቶች ያለምንም ችግር ለዓለም ገበያ እንዲቀርቡ ስምምነት ከመደረጉ ውጭ በሀገራቱ መካከል ውጤት ያመጣ ድርድር አልተደረገም።

ሩሲያ የአውሮፓ ሀገራት የተፈጥሮ ጋዝ የሚያገኙበትን ማስተላለፊያ ለሶስት ቀናት ልትዘጋ ነው የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመሩ መጥገና ምክንያት ሃምሌ ላይም ተዘግቶ ነበር የሩሲያው ጋዝፕሮም ኩባንያ ፤ የአ
ሩሲያ የአውሮፓ ሀገራት የተፈጥሮ ጋዝ የሚያገኙበትን ማስተላለፊያ ለሶስት ቀናት ልትዘጋ ነው የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመሩ መጥገና ምክንያት ሃምሌ ላይም ተዘግቶ ነበር የሩሲያው ጋዝፕሮም ኩባንያ ፤ የአውሮፓ ሀገራት የተፈጥሮ ጋዝ የሚያገኙበትን መስመር ሊዘጋ መሆኑን አስታውቋል፡፡ የሩሲያ የተፈጥሮ ጋዝ ወደ አውሮፓ የሚጓጓዝበት የኖርድ ስትሪም መስመርን ነው ጋዝፕሮም ሊዘጋ መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡  የተፈጥሮ ጋዝ ከሩሲያ ወደ አውሮፓ የሚገባው በኖርድ ስትሪም በኩል ቢሆንም በፈረንጆቹ ከነሃሴ 31 እስከ መስከረም ሁለት ድረስ ግን አገልግሎት አይሰጥም ተብሏል፡፡ ኖርድ ስትሪም ለሶስት ቀናት የሚዘጋው በጥገና ምክንያት መሆኑን ጋዝፕሮም አስታውቋል፡፡ የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ መስመሩ ጋዝን ከሩሲያ ወደ ጀርመን የሚያመላልስ መስመር ነበር፡፡ ድርጅቱ ለሶስት ቀናት እንደሚዘጋ ማሳወቁን ተከትሎ ጀርመን የነዳጅ ክምችቷን መቆጠብ ጀምራለች፡፡ ጋዝፕሮም የኖርድ ስትሪም ነዳጅ ማስተላለፊያን ለሶስት ቀናት እንደሚዘጋ ከገለጸ በኋላ በአውሮፓ የዋጋ ጭማሪ እንደሚከሰት ተገምቷል፡፡ ጀርመንም ይህንን ካየች በኋላ ለራሷ የሚበቃ ምርትን መቆጠብ ጀምራለች፡፡ በርሊን ቁጠባውን የጀመረችው በጋዝሮም መተማመን ስላልቻለችና እስከመጨረሻው ቢቋረጥ በሚል ስጋት መሆኑን አስታውቃለች፡፡ ጋዝፕሮም የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመሩን ሃምሌ ላይ ለ 10 ቀናት ዘግቶት መቆየቱ ይታወሳል፡፡ መስመሩ ከተጠገነ በኋላ መደበኛ ስራውን እንደሚጀምር ኩባንያው አስታውቋል፡፡ የኖርድ ስትሪም መስመር በቀን 167 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ማስተላለፍ የሚችል ሲሆን ከጥገና በኋላ ደግሞ 33 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ማስተላለፍ እንደሚችል ተገልጿል፡፡

#Update በሶማሊያ ሞቃዲሾ በሆቴል ላይ በተከሰተ ጥቃት የሞቱ ሰዎች ቁጥር 12 ደርሷል፡፡ በሞቃዲሾ በተከሰተዉ በዚህ የሆቴል ላይ ፍንዳታ የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 12 መድረሱ ተዘግቧል፡፡ ጥቃት አድ
#Update በሶማሊያ ሞቃዲሾ በሆቴል ላይ በተከሰተ ጥቃት የሞቱ ሰዎች ቁጥር 12 ደርሷል፡፡ በሞቃዲሾ በተከሰተዉ በዚህ የሆቴል ላይ ፍንዳታ የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 12 መድረሱ ተዘግቧል፡፡ ጥቃት አድራሾቹ ወደ ሆቴሉ ከመግባታቸዉ በፊት በቅድሚያ ዉጭ ላይ በነበሩ ሁለት መኪኖች ላይ ቦንብ አጥምደዉ መግባታቸዉ ነዉ የተገለጸዉ፡፡ ‹‹እስካሁን 12 ንጹሀን ሰዎች መሞታቸዉን አረጋግጠናል፣ ምርመራዉም እንደቀጠለ ነዉ ››ሲሉ የደህንነት ቢሮ ሀላፊ ለሮይተርስ ተናግረዋል፡፡ የሆቴሉ ትላልቅ ክፍሎች በጥቃቱ ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸዉም ነዉ የተዘገበዉ፡፡ የትናንቱ ጥቃት የሶማሊያዉ አዲሱ መሪ ሀሰን ሼክ ሞሀመድ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ የተከሰተ የመጀመሪያዉ ከባድ ጥቃት መሆኑ ነዉ የተገለጸዉ፡፡ ለጥፋቱም አልሸባብ ሀላፊነቱን እንደሚወስድ ተናግሯል፡፡ አልሸባብ የእራሱን እስላማዊ እና ወግ አጥባቂ መንግስት ለመመስረት ሲል የሶማሊያን መንግስት ከአስርት አመታት በላይ ሲዋጋ የቆየ የሽብር ቡድን ነዉ፡፡ ሮይተርስ በእስከዳር ግርማ

በሱዳን በዚህ ሳምንት ብቻ 77 ሰዎች በጎርፍ ተወስደዋል! ጥቂት የማይባሉ የሱዳን አካባቢዎች በከባድ ዝናብና ጎርፍ መቸገራቸው ተገለፀ።በዚህ ሳምንት ብቻ ብሉ ናይል ተብሎ በሚጠራው የሃገሪቱ አካባቢ
በሱዳን በዚህ ሳምንት ብቻ 77 ሰዎች በጎርፍ ተወስደዋል! ጥቂት የማይባሉ የሱዳን አካባቢዎች በከባድ ዝናብና ጎርፍ መቸገራቸው ተገለፀ።በዚህ ሳምንት ብቻ ብሉ ናይል ተብሎ በሚጠራው የሃገሪቱ አካባቢ ብቻ 77 ሱዳናውያን በጎርፍ ተወስደዋል ተብሏል። በአደጋው 9 ሺ ገደማ ቤቶች ሙሉ በሙሉ መውደማቸውና 27 ሺ በሚሆኑ ቤቶች ላይ ጉዳት መድረሱን ሲጂቲኤን ዘግቧል።እንደ ዘገባው ከሆነ በአደጋው ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ ሌሎች የህዝብ መገልገያ መሠረተ ልማቶች ወድመዋል።የአደጋው ሰለባዎችም መኖሪያቸውን አጥተው በጊዜያዊነት በድንኳን ውስጥ ለመጠለል እና እርዳታ ለመጠባበቅ ተገደዋል። via Alain

የደቡብ ኮሪያ ፕሬዝዳንት ዩን “አፋቸዉን እንዲዘጉ” ሰሜን ኮርያ ጠየቀች 👉“ለበቆሎ ኬክ ተብሎ እጣ ፈንታውን የሚሸጥ ማንም የለም" - ሰሜን ኮርያ የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን እህት የሆኑት
የደቡብ ኮሪያ ፕሬዝዳንት ዩን “አፋቸዉን እንዲዘጉ” ሰሜን ኮርያ ጠየቀች 👉“ለበቆሎ ኬክ ተብሎ እጣ ፈንታውን የሚሸጥ ማንም የለም" - ሰሜን ኮርያ የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን እህት የሆኑት ዮ ጆንግ የደቡብ ኮሪያን የእርዳታ ድጋፍ እናድርግላችሁ የሚለዉጥ ጥያቄ በግልጽ ዉድቅ አድርገዋል፡፡የደቡብ ኮሪያው ፕሬዝዳንት ዩን ሱክ-ዮል አስደሳች እቅድ ብለው በሰየሙት መርሃ ግብር ሰሜን ኮሪያ ከኒውክሌር እንቅስቃሴዋ ከታቀበች ደረጃ በደረጃ የኢኮኖሚ ዕርዳታ እንሰጣለን ሲሉ መናገራቸዉ የኪም እህትን አስቆጥቷል፡፡ ኪም ዮ ጆንግ በመንግስት የዜና ወኪል ኬሲኤንኤ በተለቀቀው መግለጫ ላይ እንደተናገሩት “አፉቸዉን ቢዘጉ የበለጠ ይጠቅሙን ነበር” ስትል የተናገረች ሲሆን “በጣም ቀላል እና አሁንም ልጅነት” ይታይባቸዋል ፤ ለሰሜን ኮሪያ የኢኮኖሚ ትብብርን በሚል የኑክሌር ጦር መሳሪያ ግንባታ እንደማይቆም ጠቁመዋል፡፡ “ለበቆሎ ኬክ ተብሎ እጣ ፈንታውን የሚሸጥ ማንም የለም”ስትል የኪም ጆንግ ኡን እህት አክላለች፡፡የደቡብ ኮሪያ የውህደት ሚኒስትር ኩዎን ያንግ-ሴ በኪም ዮ ጆንግ አስተያየት "በጣም ተጸጽተዋል" ሲሉ በደቡብ ኮርያ ፕሬዝዳንት ዮን ላይ ያቀረቡትን ትችት "በጣም አክብሮት እና ጨዋነት የጎደለው" ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ፑቲን አልተቻለም‼️ የሩሲያ TU-95 ቦምብ ተሸካሚ አውሮፕላኖች በዩክሬን ዳርቻ በኔቶ ድንበር አቅራቢያ ሲበሩ ውለዋል። ድላይ ሞል እንደዘገበው ከሆነ የሩሲያ ኒኩሌየር ቦንብ ተሸከሚ አውሮፕላኖች ከ7
ፑቲን አልተቻለም‼️ የሩሲያ TU-95 ቦምብ ተሸካሚ አውሮፕላኖች በዩክሬን ዳርቻ በኔቶ ድንበር አቅራቢያ ሲበሩ ውለዋል። ድላይ ሞል እንደዘገበው ከሆነ የሩሲያ ኒኩሌየር ቦንብ ተሸከሚ አውሮፕላኖች ከ70 አመት ቡኋላ ድምፃቸውን አጥፍተው በኔቶ ጦር አቅራቢያ ስር ሲበሩ ታይተዋል ብሏል። በዚህም ምክንያት በኔቶና በምዕራባውያኑ መንደር ከባድ መረባበሽና ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ወድቀዋል ያለ የእንግሊዝ ታርዝ ጋዜጣ ነው። ከዚህ በተጨማሪም በራሺያ ቁጥጥር ስር ካለው ከዩክሬን የኒኩለር ማብሊያ ጭስ እየወጣ መተየቱ አውሮፓውያንን ለጭንቀት ዳርጓል። የጭንቀቱ ምክንያት፦ ደግሞ የኒኩሌር ጨረርና ሬዲዮ አክቲቭ የአውሮፓን ሀገራት እጅግ በጣም ስለሚጎዳ ነው። Goodnight, See you tomorrow🙋❤🙏

ሁሉም የናይል አባል ሀገራት የሚተዳደሩበት ህጋዊ ማእቀፍ ያስፈልጋል ተባለ! ዘላቂነት ያለው የድንበር ተሻጋሪ ትብብር እውን እንዲሆን ሁሉም የናይል አባል ሀገራት የሚተዳደሩበትና የሚገዙበት ህጋዊ ማእ
ሁሉም የናይል አባል ሀገራት የሚተዳደሩበት ህጋዊ ማእቀፍ ያስፈልጋል ተባለ! ዘላቂነት ያለው የድንበር ተሻጋሪ ትብብር እውን እንዲሆን ሁሉም የናይል አባል ሀገራት የሚተዳደሩበትና የሚገዙበት ህጋዊ ማእቀፍ እንደሚያስፈልግ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) አመለከቱ። 30ኛው የናይል ሀገራት የሚኒስትሮች ካውንስል ጉባኤ በታንዛንያ እየተካሄደ ሲሆን በጉባኤው ላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የተፋሰሱ ሀገራት ትብብር በጠንካራ ህጋዊ መሰረት ላይ ለማንበር የጋራ ጥረት ተደርጓል። በዚህም አራት የናይል ቤዝን ኢንሼቲቭን (NBI) አባል ሀገራት የትብብር ማዕቀፉን (CFA) እንደ ብሔራዊ ህግ ማጽደቃቸውን ገልጸዋል። የትብብር ማእቀፉን ያፀደቁ ሀገራትን ቁጥር ለማሳደግ የናይል ቤዝን ኢንሼቲቭን (NBI) ወደታለመለት የኮሚሽን ደረጃ እንዲሸጋገር መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የትብብር ማዕቀፉን የማጽደቅ ሂደት ጊዜ ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ እንዳልሆነ የገለጹት ሚኒስትሩ ናይል ቤዚን ኢኒሽቲቭ (NBI) እንደ መሸጋገሪያ ማእቀፍ ሊያከናናቸው የማይችላቸው ስትራቴጂያዊ እና ሽግግራዊ ጉዳዮች መኖራቸውን ጠቁመዋል። በመሆኑም የናይል ተፋሰስ ልማት እና አስተዳደር ጉዳዮች ለማሳካት የትብብር ማእቀፉ መጽደቅ መሰረታዊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው አስረድተው ሁሉም አባል ሀገራት ቅድሚያ የሚሰጡት ጉዳይ መሆን እንዳለበትም መግለጻቸውን ሚኒስቴሩን ጠቅሶ ኢዜአ ዘግቧል። የናይል ተፋሰስ ኢኒሸቲቭ (NBI) የሽግግር ማእቀፍ ሆኖ በዘጠኝ መስራች አባል ሀገራት የጋራ ራእይ የተመሰረተና ቋሚ የናይል ወንዝ ተፋሰስ ኮሚሽን እስከሚመሰረት የሽሽግር ማእቀፍ ሆኖ እንዲያገልገል ታስቦ መቋቋሙ ይታወቃል።

🚨3ተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች 08:30 | ቶተንሀም ከ ዎልቭስ 11:00 | ክሪስታል ፓላስ ከ አስቶንቪላ 11:00 | ኤቨርተን ከ ኖቲንግሃም 11:00 | ፉልሀሞ ከ ብሬንትፎር
🚨3ተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች 08:30 | ቶተንሀም ከ ዎልቭስ 11:00 | ክሪስታል ፓላስ ከ አስቶንቪላ 11:00 | ኤቨርተን ከ ኖቲንግሃም 11:00 | ፉልሀሞ ከ ብሬንትፎርድ 11:00 | ሌስተር ሲቲ ከ ሳዉዝሀምፕተን 01:30 | ቦርንማዉዝ ከ አርሰናል 🗓 ዕሁድ ነሐሴ 15 2014 10:00 | ሊድስ ዩናይትድ ከ ቼልሲ 10:00 | ዌስትሃሞ ከ ብራይተን 12:30 | ኒዉካስል ከ ማንቸስተር ሲቲ 🗓 ሰኞ ነሐሴ 16 2014 04:00 | ማን ዩናይትድ ከ ሊቨርፑል