የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
الذهاب إلى القناة على Telegram
5 204
المشتركون
-11024 ساعات
-1 9137 أيام
-2 77030 أيام
أرشيف المشاركات
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ማክሰኞ ጥቅምት 13 ቀን 2016 ዓ.ም
ቀኑን ማክበር ለመጪው የወል ብሩህ ቀን ምቹ ሁኔታ መፍጠር ነው።
ለሰው ልጅ በዝች ምድር ላይ የመኖር ዕድል የተሠጠው ለአንዴ ብቻ ነው። ለአንዴ ብቻ የሚኖራትን ውድ ህይወት ለሌሎች ሠላምና ደህንነት ክብርና ነፃነት የሠጠን ማክበር ከዜጎች የሚጠበቅ ትንሹ ሐላፊነት ነው።
በዚህ ባህልና ወግ ሐይማኖትና እምነት ካለው ማህበረሰብ አካል ተገኝቶ ባህልና ወጉን በኢትዮጵያ ፍቅር ተክቶ በበዓል በአዘቦት ወጥቶ የሚያድር ሃያ አራት ሠዓታት የሚሠራ ፤የሚያገዝፍ የሚያኮራ ጀግናውን የሚያከብር ሀገር የመሻገር ዕድሉ ከፍተኛ ነው።
ዘር፣ ቀለም ፣እምነትና ሐይማኖት ሳይለያይ፤ የሁሉም አገልጋይ፤ የሁሉም ተወካይ፤ የሠላም መናኝ ዋጋ ከፍሎ ካኖራት ሠንደቅ ዓላማው ጋር ከፍ ብሎ እንዲታይ መፍቀድና እውቅና መስጠት፤ ለአንድነትና አብሮነት በርን አስፍቶ መክፈት፤ የጥላቻና ፅንፈኝነትን መንገድ መዝጋት ነው።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የሀገሩ እውነተኛ ተምሳሌት ነው። በመሆኑም የዚህን ጀግና መከላከያ ሠራዊት ቀን ማክበር ነገ ለሚመጣው ለሚጠብቀን የሁሉም ብሩህ ቀን ተባባሪና ባለቤት መሆን ነው።
" በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት"
116ኛው የሠራዊት ቀን ጥቅምት 15 ቀን እንዲሆን የተደረገው በሀገራችን ተጨባጭ የውትድርና ታሪክ ላይ ተመስርቶ ስለመሆኑ ተገለጸ።
በመከላከያ ጠቅላይ መምሪያ እየተካሄደ የሚገኘውን የፓናል ውይይት የመሩት የጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ ወታደራዊ አማካሪ እና የተኩስ አመራር ሃላፊ ሌተናል ጄኔራል አለምሸት ደግፌ እንዳሉት፦ በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የጦር ሚኒስቴር የተቋቋመው ከዛሬ 116 ዓመት በፊት ጥቅምት 15 እንደመሆኑ ሠራዊት በትውልድ ቅብብሎሽ የሚገነባ ስለመሆኑ ለማሳየት ሲባል የሠራዊት ቀን በዓልም በዚሁ ዕለት እንዲሆን ተወስኗል።
ከዚህ ቀደም የካቲት 7 የሰራዊት ቀን ተብሎ ይከበር እንደነበር ያስታወሱት ሌተናል ጄኔራል አለምሸት ደግፌ ይህ የኢትዮጵያን የውትድርና ታሪክ የዘነጋ በርካታ የሀገር ባለውለታዎችን የሚገፋ በመሆኑ የሰራዊት ቀን በትክክለኛው የኢትዮጵያ ውትድርና ታሪክ ጅማሮ ላይ ተመስርቶ መከበሩ ፋይዳው የላቀ ስለመሆኑም ነው የጠቆሙት።
የሰራዊት ቀንን ስናከብር አራት መሠረታዊ ጉዳዮችን ለማሰብ እንደሆነ ያብራሩት ሌተናል ጄኔራል አለምሸት ደግፌ የመጀመሪያውና ዋነኛው ስለ ሰላም ለማሰብ ነው ብለዋል።
ሰላም በመስዋዕትነት የሚገኝ ውድ ዋጋ እንደመሆኑ ሰላም ሲታሰብ ወታደርንም ማሰብ ግድ እንደሚል ነው ጄኔራሉ አያይዘው ያሥረዱት።
ሌላኛው የሠራዊት ቀን አከባበር ዓላማ ሰራዊቱን ለማመስገን፣ውትድርናን እንደሙያ ለማክበር ብሎም ስለ ሀገር ህልውና በቀጣይነት ለማሰብ እንደሆነም በጄኔራል መኮንኑ ተገልጿል።
የፓናል ውይይቱ "የሰራዊት ግንባታ መሠረተ-ሃሳብና የትውልድ ቅብብሎሽ" በሚል ርዕስ ቀጥሎ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
"በተፈተነ ጊዜ.ሀሉ የሚፀና የድል ሰራዊት"
ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች
🇪🇺በአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ
01:45 | ጋላታሳራይ ከ ባየር ሙኒክ
01:45 | ኢንተር ሚላን ከ ሳልዝበርግ
04:00 | ብራጋ ከ ሪያል ማድሪድ
04:00 | ዩኒየን በርሊን ከናፖሊ
04:00 | ቤኔፊካ ከ ሪያል ሶሴዳድ
04:00 | ሎንስ ከ ፒኤስቪ
04:00 | ማንቸስተር ዩናይትድ ከ ኮፐንሀገን
04:00 | ሴቪያ ከ አርሰናል
🌏በኤዢያ ቻምፒየንስ ሊግ
03:00 | አል ናስር ከ አል ዱሀይል
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቅዳሜ ጥቅምት 10 ቀን 2016 ዓ.ም
"መከላከያ የሠራዊቱን ሁለንተናዊ ኑሮ ለማሻሻል ከፍተኛ በጀት መድቦ እየሰራ ነው" ፦ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ።
የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከልን መርቀው ከፍተዋል።
ግንባታው ደረጃውን የጠበቀና ተቋሙ እያካሄደ ያለውን የፕሮፌሽናል ሠራዊት ሂደትን ዕውን የሚያደርግ ሲሆን የመከላከያ መሀንዲስ ዋና መምሪያ የገነባው የኮማንዶና አየር ወለድ ማሰልጠኛ ማዕከል እና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፣ ሚኒስትሮች ጄኔራል መኮንኖች እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በቢሾፍቱ በደማቅ ስነስርዓት ተመርቋል ።
ከኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከልና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት በተጨማሪ የመከላከያ መረጃ ዋና መምሪያ ፕሮጀክትም ተጠናቆ ርክክብ ተደርጓል።
116ኛው "በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት !" በሚል መሪ ቃል እየተከበረ የሚገኘው የመከላከያ ሠራዊት ቀን ላይ ትልልቅ ፕሮጀክቶች መጠናቀቃቸው ተቋሙ ሁለንተናዊ ለዉጥ ላይ መሆኑን ማሳያ እንደሆነም ተመላክቷል።
የዕለቱ የክብር እንግዳ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ "በተፈተነ ጊዜ የሚፀና የድል ሠራዊት" በሚል መሪ ቃል ለሚከበረው 116ኛው የሠራዊት ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት ፕሮጀክቱ ደረጃውን ጠብቆ ስለ ተሰራ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የመከላከያ መሀንዲስ ዋና መምሪያ ሥራዎችን በጥራትና በአጭር ጊዜ እየሰራ ስለሆነ ቀጣይም የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ለዋና መምሪያው መስጠት ይገባል ካሉ በኋላ በሥራው ለተባበሩ አካላት ምስጋና ያቀረቡት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ መከላከያ ሠራዊቱ የተቀበለውን ሀገራዊ ተልዕኮ በፈተናዎች ውስጥም ሆኖ ሀገር የማስቀጠሉን ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
የመከላከያ መረጃ ዋና መምሪያ ሀላፊም በበኩላቸው መከላከያ ሠራዊቱ የተሰጠውን ተልዕኮ በቆራጥነት እየፈፀመ መሆኑን አንስተው ተቋሙ የጀመረውን የለውጥ ሂደት ለማሳካት ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የመከላከያ መሀንዲስ ዋና መምሪያ ሀላፊ ሌተናል ጄኔራል ደስታ አብቼ ዋና መምሪያው በርካታ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በአራቱም የሀገሪቱ ማዕዘን በጥራትና በብቃት መሥራቱን ገልጸው ወደፊትም ይህን ውጤታማ ተልዕኮውን አጠናክሮ እንደምቀጥል ገልፀዋል።
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄነራል ሹማ አብደታ የመከላከያ መሀንዲስ ዋና መምሪያ የሚገነባቸው ግንባታዎች የሠራዊቱን ግዳጅ የሚያሳልጥ መሆኑን ጠቁመው ማሰልጠኛው ለትውልድ እንዲተላለፍ ማድረግ እንደሚገባ ነው የገለፁት።
በመድረኩ ለግንባታው መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማት እና ግለሰቦች የዕውቅናና የምስክር ወረቀት ተበርክቷል።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቅዳሜ ጥቅምት 10 ቀን 2016 ዓ.ም
116ኛው የሠራዊት ቀን በዓል በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተከበረ።
"በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት" በሚል መሪ ቃል እየተከበረ በሚገኘው 116ኛው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ቀን በዓል በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል።
በዝግጅቱ ላይ ዶክተር መንግስቴ ቱሉ ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ "የሰላም ሰራዊት" በሚል ርዕስ ጥናታዊ ፅሁፍ አቅርበው ውይይት ተካሂዶበታል።
በጥናታዊ ፅሁፉ የመከላከያ ሰራዊታችን በዘመናዊ መልኩ ከተደራጀ ከ1900 ዓ.ም ከአመሰራረቱ ጀምሮ የነበረውን እንቅስቃሴና ወቅታዊ ፈተናዎች ዙሪያ ሠፊ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
የፓናሉ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት በየዘመኑ ለሀገራቸው መስዋዕትነት የከፈሉ ኢትዮጵያውያን ጀግኖችን ለመዘከርና ሀገራቸውን በውትድርና እያገለገሉ የሚገኙ አባላትን ማመስገን በመቻላቸው መደሰታቸውን ገልፀዋል።
የጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን ለሀገር የከፈለውን የህይወት ዋጋ ለትውልዱ ለማሳወቅና ለመጪው ትውልድ ለማስተዋወቅ የሰራዊቱን ጀግንነት የሚያሳውቁ ጥበባዊ ስራዎች ሊሰሩ እንደሚገባም ጠቁመዋል።
በዝግጅቱ ላይ በሀገር ፍቅር ዘመናዊ የሙዚቃ ባንድና የውዝዋዜ ቡድን የተዘጋጁ የሀገር ፍቅርን የሚያጎሉና ጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችንን የሚያወድሱ ጥበባዊ ስራዎች ቀርበዋል።
በዝግጅቱ ሀገራቸውን በውትድርና ያገለገሉ ጀግኖች ፤ የሰራዊቱ ተወካዮችና ከከተማዋ የተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ ወጣቶች ተገኝተዋል።
SKY PRE MATCH
💦ማንቸስተር ሲቲ ከ ብራይተን 🔵
💦በማንችስተር ሲቲ በኩል
📊ሲቲ በፔፕ ጋርዲዮላ መመራት ከጀመረበት ጊዜ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሶስት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎችን የመሸነፍ ስጋት ውስጥ ገብቷል። ለመጨረሻ ጊዜ ይሄን ያህል ጊዜ በተከታታይ የተሸነፉት በመጋቢት 2016 በማኑዌል ፔሌግሪኒ ስር ነበር።
📊ሲቲ በሜዳው 20 ተከታታይ ጨዋታዎችን በሁሉም ውድድሮች አሸንፈዋል ይህም በፕሪምየር ሊግ ክለብ የተመዘገበው ትልቁ ሪከርድ ነው ማንቸስተር ዩናይትድ በታህሳስ 2010 እና በሴፕቴምበር 2011 መካከል በተከታታይ 20 ጨዋታዎች ካሸነፈበት ጋር እኩል በመሆን
📊ሮድሪ ለሲቲ ባደረጋቸው ያለፉት 35 ጨዋታዎች ሲቲ አልተሸነፈም።
📊ፊል ፎደን ከብራይተን ጋር ባደረጋቸው አምስት የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች 6 ጎሎችን አስቆጥሯል
📊በሲቲ ባለፉት ሁለት የሊግ ጨዋታዎች አንድ ሙከራ ያስመዘገበው ኤርሊንግ ሀላንድ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሶስት ተከታታይ የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ጎል ሳያስቆጥር ሊወጣ ይችላል
📊ጁሊያን አልቫሬዝ ለማንቸስተር ሲቲ በሜዳው በሁሉም ውድድሮች ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች 16 ጎሎችን ከመረብ አሳርፏል።
ብራይተን
በዘንድሮው የውድድር ዘመን በፕሪሚየር ሊጉ ከፍተኛ ግብ ያስቆጠሩት እነሱ ናቸው ምንም እንኩዋን የተቆጠረባቸው ግብ በዘንድሮው ዓመት ከHIGHEST GOAL CONCENDING ቡድኖች ጋር ሚያሰልፋቸው ቢሆንም
ብራይተን በ20 የፕሪምየር ሊግ ግጥሚያዎች ከአምናው ሻምፒዮና ጋር ያሸነፈው ብቸኛ ድል በየካቲት 2021 ከሊቨርፑል ጋር 1-0 ነበር
የብራይተን ተቀያሪዎች በዚህ ሲዝን 6 ግቦችን በፕሪምየር ሊግ አስመዝግበዋል(በሊጉ ከፍተኛው ነው)
ዳኒ ዌልቤክ ከማንቸስተር ሲቲ ጋር ባደረጋቸው 17 የፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች ጎል ማስቆጠር አልቻለም።
ይቀጥላል.....
ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር ሰላምን፣ ደህንነትን፣ ንግድና ዉህደትን ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገለጸች
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
👉 ዓርብ ምሽት ጥቅምት 9 ቀን 2016
👉 ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር ሰላምን፣ ደህንነትን፣ ንግድና ዉህደትን ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን የአገሪቷ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
👉 ሱማሊያ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አሊ ኦማር፤ ሶማሊያ ሰላምን፣ ደህንነትን፣ ንግድና ዉህደትን ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን የገለጹ ሲሆን፤ ነገር ግን እንደ ወድብ የመሰለ ስትራቴጂያዊ ንብረት የመልቀቅ ፍላጎት የላትም ማለታቸውን ብሉምበርግ ዘግቧል፡፡
👉 በሌላ በኩል የጅቡቲው ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌ ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት አሌክሲስ መሀመድ፤ “የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አቋም አሁን በቀጥታ ወደፊት ይምጣ እንጂ፤ ቀድሞ የነበረ አቋም ነው” ሲሉ ገልጸዋል፡፡
👉 አክለውም “ጅቡቲ ከጎረቤት አገሮች ጋር በተለይም ከኢትዮጵያ ጋር መልካም ግንኙነት ለመፍጠር ምን ጊዜም በሯ ክፍት ነው ያሉ ሲሆን፤ ኢትዮጵያ ቀይ ባህርን ለመጠቀም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ጥያቄ እስክታቀርብ ጅቡቲ እንደምትጠብቅ አመላክተዋል።
👉 በተጨማሪም ጅቡቲ ኢትዮጵያን የባህር በር አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን ከፍተኛ አማካሪው ጠቁመዋል።
"ከክብራችን ክብሯን ከጥቅማችን ጥቅሟን
ያልን ነንና፤ስለሷ አሻግረን እንመለከታለን"
የዓለማችን ማንኛውም ሀገር ባለጸጋ ሆነ ደሃ፣ትንሽ ሆነ ትልቅ ሉዓላዊ ነው እስከተባለ የራሱ ብሄራዊ ፍላጎትና ጥቅም አለው።
ያለ ብሄራዊ ፍላጎትና ጥቅም የሚታሰብ ሀገር አለ ከተባለ ያ ሀገር ህላዌው በተገቢው ስለመጠበቁ ያጠራጥራል።
ለሺህዎች ዘመናት እየሰፋችም እየጠበበች በተለያዩ የታሪክ፣የፖለቲካ ጠመዝማዛና የውጣ ውረድ ሂደት ዛሬ ላይ የደረሰችው ኢትዮጵያም የራሷ ብሄራዊ ፍላጎትና ጥቅም አላት።
የሀገር ብሄራዊ ፍላጎትና ጥቅም ሲባልም ከውስጥ አንስቶ ወደ ቀጠና፣አህጉርና ዓለማዊ እውነታዎች ላይ በተተነተነ የጥናት ውጤት በሆኑ ጭብጦች ላይ ተመስርቶ ሀገራዊ ህልውና አስጠባቂ ተግባራትን መከወን እንደማለት ነው።
በተለይ በተለይ ደግሞ ጂኦ-ፖለቲካዊ ከባቢያዊ እውነታና ስትራቴጂካዊ አቀማመጥ ለሀገራት ኢኮኖሚያዊያ የብሄራዊ ደህንነት ጉዳዮች የወሳኝነት ሚና እንዳለው ግልጽ ነው።
ታዲያ ለሀገራዊ ብሄራዊ ጥቅምና ፍላጎት መረጋገጥ ከወሳኝ ጥበብ የተሞላበት ዲፕሎማሲያዊ አቅም ፈጥሮ መገኘት ለአንድ ሀገር ይዋል ይደር የማይባል ጉዳይ ነው።
ግን ደግሞ ዲፕሎማሲያዊ አቅም ብቻውን የአንድን ሀገር ጥቅምና ፍላጎት ሊያሳካ አይችልም።
ስለዚህ አንድ ሀገር ከሁለንተናዊ ዘላቂ ኢኮኖሚያዊ አቅም ግንባታ ጋር የተጣመረ አስተማማኝ ወታደራዊ አቅም መገንባትም የቅድሚያ ቅድሚያ ስራ መሆኑን የዓለማችን ተጨባጭ እውነታ እያስመለከተን ይገኛል።
አሁን ላይ ዓለማችን በአስደንጋጭ ጦርነቶችና የጦርነት ስጋቶች እየተናጠች ያለችበት እውነታ ሲገለጥ የሀገራት ብሄራዊ ጥቅምና ፍላጎትን የማስጠበቅ ጉዳይ ፈጦ ይታያል።
አሁናዊው የዓለማችን ጦርነት የውክልና ጦርነት መልክ መያዙ ፈተናውን በእጅጉ የከበደ ያደርገዋል።
የኢራንና ሳዑዲ መራሽ ጎራ የመንን አውድ አድርገው ማውደማቸው፣
ለምዕራባዊያንና ሩሲያ ፍልሚያ ዩክሬን ዋጋ እየከፈለች መሆኗ
ለውክልና ጦርነት መስፋፋት ዓይነተኛ ማሳያዎች ናቸው።
ታዲያ በአሁናዊዋ ዓለማችን ሀገራት በራስ ተነሳሽነት ብቻ ሳይሆን በድንገቴ አስገዳጅ አሰላለፍ ሳያቅዱ ጦርነት ሊገጥማቸው የሚችልበት ሁኔታ እየሰፋ መጥቷል።
ታዲያ እኛ ወታደሮች በማያቋርጥ አቅም የመገንባት ሂደታችንና የዘውትር ዝግጁነት የማረጋገጥ ሞያዊ ግዴታችን ሁሌም ከኢትዮጵያችን ብሄራዊ ፍላጎትና ጥቅም መረጋገጥ አኳያ 'አሻግሮ ተመልካች' በሆነ እሳቤ ነው ተግባራችንን በመከወን ላይ የምንገኘው።
እንዳለመታደል ሆኖ አሁን ላይ የሀገራችንን ብሄራዊ ፍላጎትና ጥቅም ላይ አደጋ የጋረጠብን ታሪካዊ የውጭ ጠላቶቻችን በገዛ የራሳችን ሰዎች እንድንታወክ ማድረጋቸው ነው።
የእኛ ኢትዮጵያዊያን ተፈጥሯዊ እውነት የሆነውን ብዝሃ-ብሄር፣ቋንቋ፣እምነትን ልዩነቶችን መልካም ዕድላቸው አድርገው በእኛው ሰው ሰርገው እየገቡ በግጭት እያዳከሩን ይገኛሉ።
በስመ-ፖለቲካ በብሄር ጭንብል እየተከለሉና ወክለህናል ያሉትን ህዝብ ምሽግ እያደረጉ ከውጭ እስከ ሀገር ውስጥ በስውር በዘረጉት የጥላቻና የግጭት ሰበካ፣የሀሰት ፍብረካ ያለመታከት ቀን ከሌት እየሰሩ፤የገዛ ሀገራቸው ብሄራዊ ፍላጎትና ጥቅም ላይ አደጋ የጋረጡ ከሃዲዎች እንደ አሸን ፈልተውብናል።
የሀገር መከታ ጋሻ መከላከያ ተቋምን ማንኳሰስና እኛ ወታደሮችን በክብረ-ነክ አሉባልታ ማብጠልጠልም ስራዬ ብለው የተያያዙት አሳዛኝ አሳፋሪ ግብራቸው ሆኗል።
እኛ ግን ከራስ ክብር የሀገርን፤ከራስ ጥቅም የኢትዮጵያን አስቀድመናልና ሞራላችን በክብረ-ነኮች አሉባልታ ሳይነካ ጢም እንዳለ አለ።
በሀገር ውስጥ መዳከር ብቻ እንድንገደብ በዚያ አዙሪት አቅማችን እንዲላሽቅ ቢፈልጉም እኛ አሻግረን መመልከታችንን ላፍታም አላቆምንም።
የሀገር ብሄራዊ ፍላጎትና ጥቅምን የማረጋገጥ ተልዕኮ አንግበን ያለን ነንና በዚያ ልክ በሁለንተናዊ ብቃት ማረጋገጥ ላይ በኢትዮጵያችን ልክ የተለቀ የዘውትር ተግባራችን ቀጥሏል።
በአስቻለው ሌንጫ
