የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
الذهاب إلى القناة على Telegram
5 344
المشتركون
-22624 ساعات
-2 2007 أيام
-2 65830 أيام
أرشيف المشاركات
የሁለት ጊዜ የአንደኛ ደረጃ ጀግና ሜዳይ ተሸላሚው የብርጋዲየር ጄኔራል ለገሠ ተፈራ ታሪካዊ ቅርሶች ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ገቢ ተደረጉ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የካቲት 12 ቀን 2016 ዓ.ም
ቅርሶቹ ጀግናው ብርጋዲየር ጄኔራል ለገሠ 11 ዓመት እሥር ቤት ሆኖ የለበሰው ቱታ፣ እየተዋጋ የለበሰው የበረራ ልብስ፣ ሁለት የአንደኛ ደረጃ ሜዳዮችና ሌሎችም ናቸው።
ብርጋዲየር ጄኔራል ለገሠ ተፈራ አምስት የሚሆኑ የወራሪው ዚያድባሬን ጀቶች እያሳደደ ድንበራቸውንም ጭምር ጥሶ ገብቶ ከነሙሉ ፓይሌቶቻቸው አየር ላይ ያነደደ ጀግና ሲሆን በወቅቱ የሶማሊያን ወታደራዊ ማዕከላት በማጋየት ለኢትዮጵያ ድልን አስገኝቷል።
የቅርሶቹ ወደ ዩኒቨርስቲው መግባት ትውልዱ እንዲማርበት ትልቅ አስተዋፅኦ አለው ያሉት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶክተር) አሁን ላይ ለሀገር እየተዋደቁ ያሉትን ለመዘከርና ጀግናን ለማፍራት ያግዛልም ብለዋል።
የጀግና ሥራው ሕዝብ ወደሚያይበት መውጣት እንዳለበት የገለፁት የጄኔራል መኮንኑ ቤተሰቦችም አሁን ላይ የብርጋዲየር ጄኔራል ለገሠ ተፈራ ፋውንዴሽን በማቋቋም ለሀገር የተዋደቁትንና አሁንም እየተዋደቁ ያሉትን እያገዙ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የብርጋዲየር ጄኔራል ለገሠ ተፈራ አብሮ አደጎችና የሥራ ባልደረቦች፤ ጄኔራል መኮንኑ ለሐገር ታሪክ የማይረሳው ጀብድ ሰርተው ማለፋቸውንና ቅርሳቸውም ወደ ሙዚየም በመግባቱ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል።
ለብርጋዲየር ጄኔራል ለገሠ ተፈራ የሕብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ወደር የሌለው ሁለት የጀግንነት ሜዳይና የየካቲት 1966 ዓ.ም 1ኛ ደረጃ ኒሻን እስር ቤት ባሉበት የተሰጠ ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስትና ቤተሰቦቻቸው በሠሩት የዲፕሎማሲ ሥራ ከ11 ዓመት እሥር በኋላ ወደ ሐገራቸው ተመልሰው በመኖር በክብር ያረፉ ጀግና ናቸው።
በደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳና ሀርቡ ከተማ ለሚገኙ የጸጥታ ኃይሎች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የካቲት 08 ቀን 2016 ዓ.ም
"ሠላም ለሁሉም ፣ ሁሉም ለሠላም" በሚል መሪ ቃል በኮማንዶ ክፍለ ጦር ሬጅመንት የተሰጠው ስልጠና ምርቃት ላይ የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮነን፣ የቃሉ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ሙህዲን አህመድ፣ የዞኑ ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢ ብርጋዴር ጀኔራል ዘውዱ ሰጥአርጌ እና የደሴና ኮምቦልቻ ከተሞች ኮማንድ ፖስት አመራሮች ተገኝተዋል።
በምረቃ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮነን፣ ሥልጠናው የጸጥታ መዋቅሩን አቅም በማጎልበትና በማደራጀት የአካባቢውን ሰላም በራስ አቅም በማስጠበቅ ሁለንተናዊ ልማትን የማስቀጠል ዓላማ ያለው መሆኑን ተናግረዋል።
በክልሉ የጸጥታ ችግር ከተከሰተ ጀምሮ የሚሊሺያ አባላት ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በመሆን የአካባቢያቸውን ሰላም ለማስጠበቅ ከፍተኛ ተጋድሎ ማድረጋቸውን የገለፁት ዋና አስተዳዳሪው በዚህም ጽንፈኛ ኃይሉ እንዲዳከም በማድረግ አንጻራዊ ሰላም ተፈጥሮ ማኅበረሰቡ በነፃነት ለመንቀሳቀስ መቻሉን ገልጸዋል።
የደብብ ወሎ ዞን ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢ ብርጋዲየር ጀኔራል ዘውዱ ሰጥአርጌ ፣ የአቅም ግንባታ ሥልጠናው የአካባቢውንና የክልሉን ሰላምና ጸጥታ በመጠበቅና ለየትኛውም የጸጥታ ተልዕኮ ዘወትር ዝግጁ የሆነ የሚሊሺያ መዋቅር መፍጠር ላይ ያተኮረ መሆኑን ተናግረዋል።
የሚሊሻ አባሉ በሥልጠናው ያገኘውን አቅምና ልምድ ተጠቅሞ በቀጣይ የአካባቢውን ሰላም ማስጠበቅ እንደሚገባውም አሳስበዋል።
የሬጅሜንቷ ዋና አዛዥ ሻምበል ታሪኩ ሻሜቦ፣ ለሰልጣኞቹ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የተደገፈ ስልጠና የተሰጠ በመሆኑ ከስልጠናው ከፍተኛ የሆነ ልምድና ዕውቀት እንዲያገኙ መደረጉን ገልጸዋል ።
ተመራቂ መኮንኖች የወታደራዊ ሳይንስና ጥበብን ተከትለው ተልዕኳቸውን መፈፀም እንዳለባቸው ተገለፀ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የካቲት 04 ቀን 2016 ዓ.ም
በደብረዘይት አየር ወለድ ማስልጠኛ ትምህርት ቤት ከሁርሶ የዕጩ መኮነንነት ስልጠናቸዉን አጠናቀው ለተመለሱ ለኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ መኮንኖች አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን በዕዙ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ የቀጣይ ሥራን በተመለከተም አቅጣጫ ተሠጥቷቸዋል።
መከላከያ ሰራዊቱን ለመገንባት ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍተኛ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል ከዚህ ውስጥም ከዘመኑ ጋር የሚራመድ ወታደራዊ ብቃትና ችሎታ እንዲሁም ዲሲፕሊን ያለዉ መኮነንነት በስልጠና ማብቃት አንዱ ነው በዚህም ጥሩ ስራ እየተሠራ ነው ብለዋል።
ተመራቂ መኮንኖች የወታደራዊ ሳይንስና ጥበብን ተከትለው ተልዕኳቸውን መፈፀም እንዳለባቸው የገለፁት አዛዡ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች የኢትዮጵያን እድገት የማይመኙ ፅንፈኞችና የሸኔ ቡድኖችን በመጠቀም ልማታችንን በማደናቀፍ የሃገራችንን እድገት ወደኋላ ለመጎተት እንደሚፈልጉም ተናግረዋል፡፡
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ብርጋዲየር ጄኔራል አበባዉ ሰኢድ በተሰጠን የግዳጅ ቀጠና ሁሉ በተለይ የፅንፈኛዉንና የሸኔን አረመኔያዊ ድርጊቶችን በመከታተል የሰላም ጥሪ ያልተዋጠላቸዉን ፀረ-ሰላም ሃይሎች የማያዳግም እርምጃ በመዉሰድ በህዝቡ ዘንድም ሊፈጠር የነበረዉን አደጋ መታደግ መቻሉን አሥረድተዋል።
ተመራቂ መኮንኖች በበኩላቸው የእዙ አመራሮች ላደረገላቸው ድጋፍና አቀባበል አመሥግነው በሁርሶ ማሰልጠኛ ማእከል በነበራቸው ቆይታ የመሪነት ሚናን ሊያሳድግ የሚችል አቅም መፍጠራቸውን ተናግረዋል። ዘገባው የዕዙ የሠራዊት ስነ-ልቦና ግንባታ ክፍል ነዉ፡፡
የብሪክስ አባል ሀገራት 45 ትሪሊየን ዶላር ኢንቨስት ሊደረግ የሚችል ሃብት እንዳላቸው አንድ ሪፖርት አመላከተ
ቀደም ሲል ሩሲያ፣ ሕንድ፣ ቻይና፣ ደቡብ አፍሪካና ብራዚል አቅፎ የነበረው ብሪክስ ፥ በአሁኑ ወቅት ሳዑዲ ዓረቢያ፣ ኢራን፣ ኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና የተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች በመቀላቀል ቡድኑ መስፋፋቱ ተጠቁሟል።
በሪፖርቱ መሰረት አሥሩ ሀገራት በአሁኑ ወቅት 1 ነጥብ 6 ሚሊየን ግለሰቦች ከ1 ሚሊየን ዶላር በላይ ኢንቨስት ያደረጉ ግለሰቦች እንዳሏቸው ተጠቅሷል፡፡
በተጨማሪም ከ4 ሺህ 700 በላይ ግለሰቦች ከ100 ሚሊየን ዶላር በላይ ኢንቨስት ያደረጉ ሲሆኑ ፥ ከ500 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ቢሊየነሮች ናቸው ተብሏል፡፡
በአሁኑ ወቅት 45 በመቶውን የዓለም ሕዝብ የሚያጠቃልለው ህብረቱ፥ 36 በመቶው የሚሆነውን የዓለም አቀፍ የሀገር ውስጥ ምርት እንደሚይዝም ተገልጿል፡፡
ይህም ከቡድን-7 ሀገራት ጋር ሲነጻጸር በ30 በመቶ ድርሻ የሚልቅ መሆኑ ነው የተመላከተው።
ኢትዮጵያን ጨምሮ ሳዑዲ ዓረቢያና የተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች ባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የግል ሃብት እድገት ማሳየታቸው በሪፖርቱ ተብራርቷል፡፡
በዚህም የኢትዮጵያ ሚሊየነሮች ቁጥር በ30 በመቶ፣ ሳዑዲ ዓረብያ 35 በመቶ እንዲሁም የተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች በ77 በመቶ መጨመሩ ተጠቅሷል፡፡
ሪፖርቱ እንደሚያሳየው በአሁኑ ወቅት በህብረቱ በሚሊየነሮች ብዛት ቀዳሚ የሆነችው ቻይና 862 ሺህ 400 ሚሊየነሮች ያሏት ሲሆን ፥ ሕንድ 326 ሺህ 400 ሚሊየነሮች አሏት።
በሚቀጥሉት አሥር ዓመታት ቻይና 85 በመቶ እና ሕንድ 110 በመቶ በሚሊየነሮች ጠንካራ እድገት እንደሚያስመዘግቡ መገመቱንም አርቲ ዘግቧል።
አጫጭር መረጃዎች ስለ " ዓድዋ ድል መታሰቢያ " ፦
- በ5 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን ከምድር በታች ሁለት ደረጃዎችን ጨምሮ 5 ወለል እና 8 በሮች አሉት።
- 8ቱ በሮች ፦
* የምሥራቅ ጀግኖች በር፣
* የምዕራብ ጀግኖች በር፣
* የሰሜን ጀግኖች በር፣
* የደቡብ ጀግኖች በር፣
* የፈረሰኞች በር፣
* የአርበኞች በር፣
* የፓንአፍሪካኒዝም በር ተብለው ተሰይመዋል።
- በመታሰቢያው ነጋሪትን ጨምሮ የኢትዮጵያውያን የተለያዩ (ባህላዊዎችን ጨምሮ) የጦር መሳሪያዎች ተቀምጠዋል።
- በዓድዋ ድል መታሰቢያው የአፄ ምኒሊክና እቴጌ ጣይቱ ፣ የ12ቱን የጦር መሪዎች ሀውልት፤ በጦርነቱ የተሳተፉ ኢትዮጵያውያንና ፈረሶች መታሰቢያ የአርት ሥራዎችም ሰፍረዋል።
- አንድ መቶ ሃያ ሺህ ጀግኖችን የሚዘክር ማስታወሻ፣ የዓድዋ ድል ለፓንአፍሪካኒዝም ንቅናቄ ማሳያነቱንም ይዟል። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ፋውንቴንም ተሰርቶለታል።
- በአንድ ጊዜ 2 ሺህ 500 ሰዎችን መያዝ የሚችል የፓንአፍሪካኒዝም አዳራሽ አለው።
- በአንድ ጊዜ 2 ሺህ 300 ሰዎችን መያዝ የሚችል ዘመናዊ ሁለገብ አዳራሽ አለው።
- አራት ሺህ ሰዎችን መያዝ የሚችል የቤት ውስጥ የስፖርት ሜዳ እና አዳራሽ አለው።
- የህፃናት መጫወቻ፣ የንግድ ሱቆች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳ፣ ካፌና ሬስቶራንት፣ የባንክ አገልግሎት የሚሰጡ ቢሮዎችና የአርት ጋላሪ አለው።
- ከአንድ ሺህ በላይ የመኪና ማቆሚያ አለው።
- እያንዳንዳቸው 280 ሰዎችን መያዝ የሚችሉ 2 ሲኒማ ቤቶች አሉት።
- በቅርቡ ወደ ሀገር የገባችው " ፀሀይ አውሮፕላን " በዓድዋ ድል መታሰቢያ እንድትቀመጥ ተደርጓል።
- አጠቃላይ ስራው 4.6 ቢሊዮን ብር ወጪ ተደርጎበታል።
ℹ️ 00 ኪ.ሜ መነሻ ቦታ ፦ በዓድዋ ድል መታሰቢያ መሐከል ላይ የሚገኘው የኮምፓስ ምልክት በአዲስ አበባ እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ለሚገኙ ቦታዎች የርቀት መለኪያ መነሻ ነው።
ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች
🏴 በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ
09:30 | ማንችስተር ሲቲ ከ ኤቨርተን
12:00 | ፉልሃም ከ በርንማውዝ
12:00 | ሊቨርፑል ከ ብርንሌይ
12:00 | ሉተን ከ ሼፊልድ
12:00 | ቶተንሀም ከ ብራይተን
12:00 | ወልቭስ ከ ብሬንትፎርድ
02:30 | ኖቲንግሃም ከ ኒውካስትል
🌍በአፍሪካ ዋንጫ (የደረጃ ጨዋታ)
05:00 | ደቡብ አፍሪካ ከ DR ኮንጎ
🇪🇹 በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ
09:00 | አዳማ ከተማ ከ ፋሲል ከነማ
12:00 | ሻሸመኔ ከተማ ከ ድሬደዋ ከተማ
🇫🇷በፈረንሳይ ሊግ 1
01:00 | ሌንስ ከ ስታርስበርግ
05:00 | ፒኤስጂ ከ ሊል
🇩🇪በጀርመን ቡንደስሊጋ
11:30 | ኦግስበርግ ከ RB ሌብዚንግ
11:30 | ሞንቼግላድባህ ከ ዳርምስታድት
11:30 | ፍራንክፈርት ከ ቦቹም
11:30 | ዩኒየን በርሊን ከ ዎልቭስበርግ
11:30 | ቨርደር ብሬመን ከ ሃይደንሃይም
02:30 | ባየር ሌቨርኩሰን ከ ባየር ሙኒክ
🇪🇸 በስፔን ላሊጋ
10:00 | አለቬስ ከ ቪያሪያል
12:15 | ሪያል ሶሴዳድ ከ ኦሳሱና
02:30 | ሪያል ማድሪድ ከ ጅሮና
05:00 | ላስ ፓልማስ ከ ቫሌንሲያ
🇮🇹በጣልያን ሴሪ ኤ
11:00 | ካግላሪ ከ ላዚዮ
02:00 | ሮማ ከ ኢንተር
04:45 | ሳሱሎ ከ ቶሪኖ
🌏በኤዥያ ካፕ (የፍፃሜ ጨዋታ)
12:00 | ጆርዳን ከ ኳታር
በሬጅመንቷ የቀን ከሌት ክትትል በርካታ የቡድን መሳሪያዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋል ተችሏል።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የካቲት 02 ቀን 2016 ዓ.ም
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ አንድ ሬጅመንት በተሠማራችበት የግዳጅ ቀጠና የፅንፈኛውን ሀይል ሪዝራዦች በመቆጣጠር በአካባቢው የተረጋጋ ሠላም መፍጠሯን ሻምበል ታሪኩ ሻሜቦ ገልፀዋል፡፡
የሬጅመንቷ አባላት በተሰማሩበት የግዳጅ ቀጠና ለፅንፈኛው ቡድን ወደ በርሃ ሊላክ የነበረ በርካታ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር አውለዋል።
በተለይም የቡድን መሳሪያ ለመሻሻጥ ቀብድ የከፈሉ ነጋዴዎች ከነ መሳሪያው ተይዘዋል። ብሬን ፣ ስናይፐር ፤ ዲሽቃና ሞርታር ጭምር ለመግዛት ቀብድ የከፈሉትን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተካሄደ መሆኑም ተገልጿል።
በከተማዋ የፖለቲካ አመራሮች እንዲገደሉ ከፅንፈኛው ሃይል ተልዕኮ የተሰጣቸውን ፅንፈኞችም ጭምር ሬጅመንቷ በቁጥጥር ስር በማዋል በህዝቡ ዘንድ ሊፈጠር የነበረውን አደጋ መታደግ ተችሏል።
የመከላከያ ፣ የቀድሞ ልዩ ሃይልና የፌዴራል ፖሊስ አልባሳትንና ተተኳሾችን በመሰብሰብ ወደ በረሃ ለመላክ እየተዘጋጁ የነበሩ የሎጅስቲክስ ቡድን አባላትን በመያዝ የጠላትን የአቅርቦት ሰንሰለት መቁረጥ ተችሏል።
እስከአሁን የምስራቅ አማራ ፋኖ ምክትል አዛዥና የስልጠና ሃላፊ የነበረው አምሳ አለቃ ሲሳይ አሰፋን ጨምሮ በርካታ የፅንፈኛው ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር በማድረግ በጮሬሳ ተሃድሶ ማዕከል እንዲገቡ ተደርጓል።
ዘጋቢ አብዱራህማን ሀሰን
ፎቶግራፍ አብዱራህማን ሀሰን
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ክፍለጦር በቃሉ ወረዳና አካባቢው ከ2000 በላይ ሚሊሺያዎችን እያሠለጠነ ነው።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የካቲት 01 ቀን 2016 ዓ.ም
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ክፍለጦር በተሠማራባቸው ቃሉ ወረዳና አካባቢው ከ2000 በላይ ሠላምን ማረጋገጥ የሚችሉ ሚሊሺያዎችን እያሠለጠነ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ክፍለጦሩ አካባቢውን ከፅንፈኛ ሀይሉ ነፃ በማድረግ የፀጥታ ሀይል አሰልጥኖ ያሥመረቀና አሁንም ተጨማሪ ከ2000 በላይ የሚሊሺያ ሀይል በማሰልጠን ላይ እንደሚገኝ ሻምበል ታሪኩ ሻምቤቦ ገልፀዋል፡፡
ህዝቡ የራሱን ሰላም በራሱ እንዲጠብቅ ሰላም ወዳድ ከሆነውን ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ጋር በተደረገው ውይይት የተሰጠን አቅጣጫ በመሆኑ የአከባቢውን ወጣት በመመልመል እስከአሁን በ3 ዙሮች ሥልጠና መሠጠቱንና አሁንም ሥልጠና እየተሠጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ሠልጠኝ ሚሊሺያዎችና የአካባቢው ሠላም አሥከባሪዎች ተገቢውን ሥልጠና ከወሰዱ በኋላ ከሠራዊቱና ከህዝብ ጋር በመሆን ሠላም የማረጋገጥ ሥራ እንደሚሠሩ ታምኖባቸዋል።
የሀገሪቱ ኹለተኛው ብርቱ ሠው፥ ክቡር አቶ ተመሥገን ጥሩነህ (ተሜ) ያለፉት ሦስት ዓመታት የሀገሪቱ የብሔራዊ መረጃ ደኅንነት መስራቤትን በጄኔራል ዳይሬክተርነት የመሩት ጉምቱ የመረጃና የፖለቲካ ሠው አቶ ተመሰገን ጥሩነህ፣ የሀገሪቱ ኹለተኛው ብርቱ ሠው ኾኖ መሠየማቸውን ሰምተናል። ድንቅ ውሣኔ። ተገቢ መልሶ ማደራጀትና የአመራር ሥምሪት ኾኖ አግኝቸዋለኹ።
ክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፣ አቶ ተመስገን ጥሩነህ ማን ናቸው? እንኾ ምላሽ። አቶ ተመስገን ከክልል እስከ ፌደራል በተለያዩ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች በተለያየ የኃላፊነት ደረጃ አገልግለዋል። በቅርቡም በሚንስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚንስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ በመሆን ሲያገለግሉ ነበር።
በምስራቅ ጎጃም ብቸና የተወለዱት አቶ ተመስገን ጥሩነህ የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በትውልድ አካባቢያቸው ጎተራ እና ብቸና በላይ ዘለቀ ትምህርት ቤት አጠናቀዋል። የመጀመሪያ ድግሪያቸውን ከማይክሮ ሊንክ ኮሌጅ በኮምፒዩተር ሳይንስ፤ ሁለተኛ ድግሪያቸውን ደግሞ እንግሊዝ ሀገር ከሚገኘው ግሪንዊች ዩኒቨርሲቲ በአመራርና አስተዳደር ተከታትለዋል።
ከዚያም በአማራ ክልል የርዕሰ መስተዳድሩ የፀጥታ እና ቴክኖሎጂ አማካሪ፣ የአማራ ገጠር መንገዶች ባለሥልጣን ምክትል ሥራ አስኪያጅ፣ የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የምሥራቅ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ፤ የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር በመሆን አገልግለዋል፡፡
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር እና የኢትዮ-ቴሌኮም ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ በመሆንም ሠርተዋል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ መሥራች ከመሆን ባለፈ በዚሁ መስሪያ ቤት ከመምሪያ ኃላፊነት እስከ ዋና ዳይሬክተርነት አገልግለዋል፡፡
አቶ ተመስገን የሀገር መከላከያ ሠራዊት መረጃ ዋና መምሪያ፣ የኤሌክትሮኒክስ እና የቴክኒካል መረጃ መምሪያ ኃላፊም ነበሩ። በመከላከያ ሠራዊት ውስጥም እስከ ሻለቃነት ማዕረግ ደርሰዋል- አቶ ተመስገን ጥሩነህ። ከዚያ በመቀጠል የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኾኖም በትልቅ ድል የስራ ስምሪታቸውን ያጠናቀቁ ጥንቁቅ መሪ ናቸው።
በአማራ ክልል ፕሬዝደንትነት በነበሯቸው ግዝያት፣ የወሰንና የማንነት ጥያቄዎችን በሕግ እንዲመለሱ እና የሕግ የበላይነትን ለማስፈን እንደሚተጉ፣ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ የቱሪስት መስህቦች ላይ ከቀደመው በበለጠ ትኩረት እንደሚያደርጉ፣ ለሥራ እድል ፈጠራ፣ ለትምህርት ጥራት፣ ለመኖሪያ ቤቶች ግንባታ፣ ለኢንቨስትመንት እድገት፣ በሴቶች አቅም ማጎልበት ላይ እንዲሁም በሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ጠንክረው ሰርተው የተግባር መሪነት ለትውልድ ቅብብሎሽ ያስረከቡ መሪ ናቸው።
እንኾ ዛሬ ደግሞ፥ የሀገሪቱ ኹለተኛው የፖለቲካ መሪ በመኾን፣ ሀገርና ሕዝብን ዳግመኛ ለመታደግ ተሹሟል።
መልካም የሥራ ዘመን፥
