የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
الذهاب إلى القناة على Telegram
5 066
المشتركون
-25624 ساعات
-1 8217 أيام
-3 02830 أيام
أرشيف المشاركات
ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneCommand
You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
#ትፈለጋለች
በኦሮሚያ ክልል በሸገር ከተማ ቡራዩ ክፍለ ከተማ አንዲት እንጀራ እናት ሁለት ልጆችን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደሏ እየተፈለገች መሆኑን ፖሊስ ገልጿል።
ስለጉዳዩ የቡራዩ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምርያ የወንጀል ምርመራ ክፍል ባልደረባ የሆኑት ዋና ሳጅን ቀነኒሳ ታደሰ ምን አሉ ?
ዋና ሳጅን ቀነኒሳ ታደሰ ፦
" ወንጀሉ የተፈፀመው ቅዳሜ ሚያዝያ 28/2015 ዓ.ም. በከታ ወረዳ ልዩ ስሙ ሦስተኛ ቡራዩ በሚባል ስፍራ ነው።
ወንጀሉ የተፈፀመው ሌሊት ነው። ሁለት ሕጻናት በአሰቃቂ ሁኔታ በእንጀራ እናታቸው ተገድለዋል ተገኝተዋል።
ተጠርጣሪዋ ነጋሴ ከበደ ብሩ የምትባል ስትሆን፣ የባለቤቷን ሁለት ልጆች አንገታቸውን ቀልታ፣ በተኙበት ብርድ ልብስ አልብሳ እሳት ለኩሳባቸው አምልጣለች። "
የልጆቹ አባት የሆኑት አቶ ጌታሁን ባልቻ ምን አሉ ?
በአካባቢው የሚገኝ ቄራ የሚሰሩ ሲሆን ግድያው በተፈፀመበት ዕለት ማምሻውን ከባለቤታቸው ጋር በልጆቻቸው ጉዳይ ተነጋግረው እንደነበር ገልጸዋል።
አቶ ጌታሁን ባልቻ ፦
" በልጆቼ ጉዳይ ተነጋግረን ነበር። በዚህም ምክንያት እንለያይ ተባብለን፤ እርሷም ‘እኔ እሄዳለሁ፣ አንተ እዚህ ትኖራለህ’ አለችኝ።
ምሽት ላይ ስንነጋገር ዛቻም ሆነ ለእንደዚህ አይነት አሰቃቂ ድርጊት ያበቃል ብዬ የምጠረጥረው ጠቋሚ ነገር አላየሁም።
ሌሊት ከዘጠኝ ሰዓት በኋላ ወደ ቤት ስመለስ የቤቱ በር ክፍት ነበር። ወደ ውስጥ ስገባ እሳት ይነዳል። ልጆቼን አልጋ ላይ ሳያቸው ጭሱ አፈነብኝ ብዬ ሮጬ ወደ ውጪ አወጣኋቸው። በወቅቱ ትልቁ ልጄ ተቃጥሏል። ትናሿ ልጄንም አወጣኋት። ወደ ውጪ ካወጣኋቸው በኋላ እነርሱ ላይ ወድቄ ራሴን ሳትኩኝ።
ልጆቼን መጀመሪያ ሳያቸው በሕይወት ያሉ መስሎኝ ነበር ፤ ያሟሟታቸውን ሁኔታ ራሴን ከሳትኩበት አንድ ቀን በኋላ ነው ከአካባቢ ነዋሪዎች እና ከፖሊስ የሰማሁት።
ልጆቼን ማሳደግ እፈልጋለሁ እንለያይ አልኳት. . . እኔ እሄዳለሁ አንተ እዚህ ትኖራለህ አለችኝ። ይህንን ብቻ ነው የተናገረችኝ። እንደዚህ ዓይነት ድርጊት በልጆቼ ላይ፣ ቤተሰቤ ላይ፣ እንስሳትም ላይ ታደርጋለች ብዬ አላሰብኩም። "
በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉት የአቶ ጌታሁን ልጆች አንደኛው የ13 ዓመት ወንድ ሲሆን፣ ሌላኛዋ ደግሞ የ4 ዓመት ተኩል ሴት ናቸው።
ሁለቱም አንገታቸው ተቀልቶ ነው የተገደሉት።
አቶ ጌታሁን በ2013 ዓ.ም የልጆቻቸውን እናት በሞት ካጡ በኋላ ባለፈው ታኅሣሥ ነበር ከተጠርጣሪዋ ጋር የተጋቡት።
ሲጋቡም የልጆቻቸውን ሁኔታ ገልፀው፣ ተማምነው ነበር የተጋቡት።
ከዚያ በኋላ እዚያው ቡራዩ አካባቢ " ሽሮ ቤት " ከፍታ ስትሰራ ቆይታለች።
ነዋሪነቷም እዚያው ቡራዩ አካባቢ ኤጀርሳ ጎሮ የሚባል አካባቢ ነው።
ተጠርጣሪዋ እየተፈለገች ነው ...
ፖሊስ በአሰቃቂ ሁኔታ የሁለት ህፃናትን ነፍስ ያጠፋችውን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ለማዋል እያፈላለጋት ይገኛል።
በቁጥጥር ስር የዋሉ የቤተሰቦቿ አባላትም አሉ።
ከሰበታ እስከ አንቦ ድረስ ከተጠርጣሪዋ ጋር የሚመሳሰሉ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎችም አሉ።
መረጃው #የቢቢሲ_አማርኛ እና የቡራዩ ፖሊስ ነው።
የሪፐብሊኩ ጥበቃ ኃይል የተሰጠውን ሠላም የማስፈን ተልዕኮ በውጤት ማከናወኑን አስታወቀ
ባለፋት ጊዜያት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የፀረ ሠላም ድርጊት ሲፈፅሙ የነበሩ ኃይሎችን ተከታትሎ ለህግ በማቅረቡ ረገድ የተሳካ ተልዕኮ ማከናወኑን የሪፐብሊኩ ጥበቃ ኃይል ምክትል አዛዥ ሜጄር ጄኔራል አብዱሮ ከድር ገልፀዋል።
የጥበቃ ኃይሉ ከመንግሥት ፈጣን ትዕዛዝ ተቀብሎ ወደ ተለያዩ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ አካባቢውን የትርምስ ቀጣና ለማድረግ የሚጥሩ ኃይሎችን ተከታትሎ ለህግ በማቅረብ እና የህዝብን ሠላም በማረጋገጡ ረገድ ውጤታማ ሥራ እያከናወነ መሆኑንም ምክትል አዛዡ ተናግረዋል።
የሪፐብሊኩ ጥበቃ ኃይል አዲስ አበባ ከተማን ጨምሮ የመላው የሀገራችን ክፍል ተልዕኮውን እየፈፀመ እና ሠላም የማረጋገጥ ተግባሩን እያከናወነ እንደሚገኝ የገለፁት ሜጄር ጄኔራል አብድሮ፤ የክፍሉ የሠራዊት አባላት ማንኛውንም ጥቃት መመከት እና የሚሠጣቸውን ግዳጅ በአስተማማኝ ብቃት መፈፀም በሚችሉበት ሁኔታ ላይ እንደሚገኙም አክለው አስረድተዋል።
አብዮተኛውን ቼ ጉቬራ በቁጥጥር ስር ያዋሉት የቦሊቪያው ጄኔራል ጋሪ ፕራዶ ሳልሞን ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
የቦሊቪያ ጄኔራል የሆኑት ጋሪ ፕራዶ ሳልሞን የኩባውን አብዮተኛ ኤርኔስቶ "ቼ" ጉቬራን በቁጥጥር ስር ማዋላቸው የሚታወስ ሲሆን በ84 ዓመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል። እ.ኤ.አ. በ 1967 ጋሪ ፕራዶ ሳልሞን በቦሊቪያ ወታደራዊ ዘመቻን በመምራት ፣በአሜሪካ በሚስጥር አገልግሎት ወኪሎች በመታገዝ በቼ ጉቬራ የተደራጀውን የኮሚኒስት አመፅ ማክሸፋቸው አይዘነጋም።
በወቅቱ ቦሊቪያ የቀኝ ክንፍ ወታደራዊ መንግስት ስር ነበረች። አንድ የጦር መኮንን ቼ ጉቬራ በቁጥጥር ስር ከዋለ ከአንድ ቀን በኋላ መግደሉ ይታወሳል። በዩናይትድ ስቴትስ እና በሶቪየት ኅብረት መካከል የነበረው የቀዝቃዛ ጦርነት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሶ በነበረበት ወቅት ዋሽንግተን የቼ ጉቬራን እንቅስቃሴን ጨምሮ በላቲን አሜሪካ ስላለው የኮሚኒስት ተጽእኖ አሳስቧት ነበር።
ቼ ጉቬራ እ.ኤ.አ. በ1959 የኩባን አብዮት ካሸነፈ በኋላ ኩባን ለቆ ወደ ሌሎች ሀገራት የሽምቅ ውጊያ እንቅስቃሴዎችን ለመምራት መጓዙ ይታወሳል። የኩባ ኮሚኒስት መሪ ፊደል ካስትሮ ቁልፍ አጋር የነበረው ቼ በአለም አቀፍ ደረጃ ለኮሚኒስቶች ጀግና ተደርጎ ይወሰዳል። የጄኔራል ፕራዶ ልጅ ወላጅ አባቱን “የፍቅር፣ የታማኝነት እና የድፍረት ውርስ” ትቶ የሄደ “ያልተለመደ ሰው” ሲል ገልጿል።
ቼ ጉቬራን ተኩሶ የገደለው የቦሊቪያ የፖሊስ መኮንን ማሪዮ ቴራን ባለፈው ዓመት ህይወቱ አልፏል። የጉቬራን የሽምቅ ውጊያ በማፍረስ በእጁ ያስገባው ጄኔራል ፕራዶ የቦሊቪያን ወታደራዊ አገዛዝ በመከላከል ብሄራዊ ጀግና ተደርጎ ይጠራል።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
ሶሪያ ወደ አረብ ሊግ አባልነት ተመለሰች
የአረብ ሊግ አባል አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የሶሪያን ከሊጉ አባልት ያገደበትን ውሳኔ በመቀልበስ ወደ አባልነት መመለሱን አስታወቀ፡፡
ሶሪያ በፈረንጆቹ 2011 የአረብ የጸደይ አቢዮትን ተከትሎ በተነሳ አመጽ እና እሱን ተከትሎ በፈነዳው የእርስበርስ ጦርነት ምክንያት ሊጉ ከአባልነት አግዷት እንደነበር ይታወቃል፡፡
የሊጉ አባል አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ዛሬ ካይሮ ላይ ተሰብስበው የሶሪያን አባልነት መልሰው ያጸደቁ ሲሆን ይህም ከ12 ዓመታት እግድ በኋላ ወደ ሊጉ እንድትመለስ እስችሏታል፡፡
ወደ አባልነት እንድትመለስ የወሰነው ሊጉ ግንቦት 19/2023 በሳዑዲ አረቢያ ከሚያደርገው ስብሰባ ቀደም ብሎ ነው፡፡
የአረብ ሊግ ዋና ጸሓፊ አቡል ገይጥ የሶሪያን ወደ ሊጉ የመመለስን ውሳኔ ተከትሎ ከዛሬ ምሽት ጀምሮ ወደ አባልነቷ ስለተመለሰች ፕሬዝዳንቱ በሊጉ ስብሰባ መሳተፍ ይችላል ብለዋል፡፡
ወደ ሊጉ የመመለሱ ውሳኔ የተፋጠነው ሶሪያ ባለፈው የካቲት ወር በከባድ ርዕደ መሬት ከተመታች በኋላ እና በቻይና አደራዳሪነት ሳኡዲና ኢራን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ወደ ነበረበት ከመለሱ በኋላ እንደሆነ አልጀዚራ በዘገባው አመልክቷል፡፡
ሁለቱ አገራት በሶሪያ የእርስበርስ ጦርነት ውስጥ የተለያዩ ተዋጊ ቡድኖችን ሲደግፉ እንደነበርም ዘገባው አስታውሷል፡፡
ባለፈው ወር የሳኡዲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የኢራኑ ፕሬዝዳንት በደማስቆ ጉብኝት ማድረጋቸው የአገራቱ ግንኙነት ወደ ተሻለ ደረጃ ከፍ ማለቱን ያሳያል ነው የተባለው፡፡ የሶሪያ ጉዳይ በአረብ ሊግ ማዕቀፍ መፈታት አለበት የሚል አቋም መያዙንም መረጃው አመላክቷል፡፡
ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneCommand
You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
ሩሲያና አሜሪካ ወደ ቀጥታ ጦርነት ለመግት ከጫፍ ደርሰዋል ተባለ‼️
ሩሲያና አሜሪካ ወደ ቀጥታ ጦርነት ለመግባት ከጫፍ መድረሳቸውን በሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ሚኒስትር ሰርጌይ ራይባኮቭ አስታወቁ።
ፑቲንን ለመግደል አልሟል ከተባለው ጥቃት ጀርባ አሜሪካ አለች ሲል የሩሲያው ክሬምሊን ቤት መንግስት ከሷል። ይህንን ተከትሎም አሜሪካ እና ሩሲያ ቃታ ስበው እርስ በእርሳቸው ለመታኮስ ከጫፍ መድረሳቸውን ነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ሚኒስትር ሰርጌይ ራይባኮቭ የተናገሩት።
“አሁን ላይ ከአሜሪካ ጋር ወደ ቀጥታ ጦርነት ለመግበጣ ጫፍ ላይ ነን” ያሉት ሚኒስትር ደኤታው፤ “ከአሜሪካ ጋር ያለን ግንኙነት ወደ ወታደራዊ ግጭት እንዳይገባ የሚቻለንን ሁሉ እየሰራ ነው” ሲሉም ተናግረዋል። ሰርጌይ ራይባኮቭ አክለውም በሁለቱ ሀገራት መካከል አሁን ላይ ትክክለኛ ዲፕሎማሲ የለም ያሉ ሲሆን፤ ምክንያቱ ደግሞ አሜሪካ ጦርነቱን የማባባስ ስራ ላይ ስለተጠመደች ነው ሲሉም አስታውቀዋል።
አሜሪካ ሩሲያ ከዩክሬን ጋር እያደረገች ባለው ጦርነት ላይ በቀጥታ እየተሳተፈች ነው ያሉ ሲሆን፤ በሀገራን ላይ ሁሉን አቀፍ ጦርነት ለመቀስቀስ እየሰራች ነው ሲሉም ከሰዋል።በክሬምሊን ቤተ መንግስት ላይ የተፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ ሩሲያ፥ ዩክሬ በቀጥታ ጥቃቱን እንደፈጸመች እንዲሁም አሜሪካ ደግሞ ከጥቃቱ ጀርባ አለች ስትል መክሰሷ ይታወሳል።
ዩክሬንም ይሁን አሜሪካ በክሬምሊን ቤተ መንግስት ጥቃት ላይ እጃቸው አለበት መባሉን ባወጡት ግለጫ ውድቅ አድርገዋል።ይህንን ተከትሎ ክሬምሊን ቤት መንግስት ባወጣው መግለጫ፤ አሜሪካና ዩክሬን በክሬምሊን ላይ የተፈጸመውን የድሮን ጥቃት ውድቅ ማድረጋቸው "አስቂኝ ነው" ብሏል።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሚያዚያ 29 ቀን 2015 ዓ.ም
"የማያቆመው የሳቅና ደስታዋ ፍለጋዬ"
ማነው የፍቅር ጥግ ማሳያ እናቱ ጎስቁላና አዝና ማየት የማያመው?
የእምዬን በፈገግታዋ ምትክ ሀዘን ያቀጨመው ቁዘማን፣ከገጿ ፍካት ይልቅ ማድያት ያከሰለው እራሮት ያበለዘው ፊቷን አይቶ ልቡን የሚያደነድን ይኖር ይሆን? ካለ ጤንነቱ ያጠራጥራል።
ለኔ ለወቴው ኢትዮጵያችን ልክ እንደ እናቴ ናት ስላችሁ፤ ለእናት የሚኮነውን ሁሉ በመሆንና በዚህ እውነትና እምነት በተግባር በመኖር ነው።
የእናት ሀዘን ምንጭ እጦት ድህነት አይደለም።እናት የቱንም ዓይነት የኑሮ ጫና ችላ፤የህይወትን ከቋጥኝ የከበደ ፈተና ተቋቁማ፤የራሷን መኖር ከነአካቴው ትታ ለልጆቿ መኖር ቅንጣት አያዝላትም።በዚህም በፍጹም አታማርርም።የእናት አያልቄ ፍቅርና ጽናትን በደንብ አናውቀው የለ?
የእናት ቅስም የሚሰበረው፤በልጆቿ ላይ በሚያጋጥም አደጋ ነው።
ጠቃሚ ነገር ሲሆን "ከኔ በፊት ለልጆቼ" ጎጂ ነገር ሲሆን "ከልጆቼ በፊት ለኔ ያድርገው" ባይዋ እናት፣
የፍቅርን ጥግ ዳር የምታሳይ እንስፍስፍ ናት አይደል?
እናም ለኔ ለወቴው "እናቴና ኢትዮጵያዬ አንድ ናቸው" ስላችሁ፤መላው ህዝቦቿን እንደልጆቿ በፍቅር አቅፋ ማኖር የማይገዳት ኢትዮጵያችን በየትኛውም ስፍራና ሁኔታ የሚኖሩ ልጆቿ ላይ ተገቢ ያልሆነ ነገር ሲያጋጥም፤በእናትነት መንሰፍሰፍ ስትብከነከንና ሳቅ ርቋት በሃዘን ስታነባ በምናቤ እያየሁ ነው።
ለዛም ነው እኔ ወታደሯ ከማህጸኗ ወጥተው ልጆቿ ሆነው ሳለ፣ የገዛ እናታቸው ኢትዮጵያን ደስታ አጨልመው በሃዘን ለማብከንከን እዚህም እዚያም እሳት በጫሩ ቁጥር፤ጨርቄን ማቄን ሳልል የተለኮሰን እሳት ፈጥኜ ለማጥፋት ላይ ታች የምልላት።
እናት ኢትዮጵያዬ ክፉኛ ሆድ የሚብሳትና ከፍቷት በምሬት የምታነባው እኩያን በጭካኔ በሚፈጥሩት ግጭት ሳቢያ የልጆቿ ለሞት፣ስደትና ረሃብ መጋለጥ ነው።ይህ ለሷ ከሰቀቀንም በላይ ይሆንባታል።
አስቀድሜ ለሰላሟ እስከ ዕለተ - ሞቴ በማይሻር ቃል ኪዳን ዘብ የቆምኩላት እኔ ወታደሯ የሰላም እጦት በሚፈጥራቸው ቀውስ የእናት ኢትዮጵያዬን ሀዘን ያጠየመው ፊት ላለማየት፤ሰላም ነሺዋን በሙያዊ ብቃቴ እና በእናትነት ፍቅሯ ተሞልቼ ሁሌም ሳቋን ፍለጋ ላይ ነኝ።
ሰላሟ ሙሉ ሆኖ፣ግጭት ጥላቻ ተወግዶ፣የክፋትና የሴራ እሳቤዎች ከስመው፣ልጆቿ በአስተውሎትና በጥበብ የሚያድጉ የሚመነደጉላት፣እርሷም በልጆቿ የስኬት ጉዞ ደስታዋ በዝቶ በሳቋ ቁንጅናዋ የፈካ፣በደስታዋ ውበቷ ተገልጦ የምታስደንቅ ጠይም ወይዘሮ ኢትዮጵያዬን እንደማያት እርግጠኛ ነኝ።
ይህ እስኪሆን ግን "ሳቋን ፍለጋዬ አያቆምም" ህመሟን እየታመምኩ፣ስለ ደስታና ሳቋ እስከወዲያኛው የፀናሁ የእውነት ልጇ ወጥቶ - አደሯ ነኝና ፍለጋዬን ሊያሰናክል የሚዳዳን ሁላ በጀግንነት እየተፋለምኩላት እቀጥላለሁ።ለዚህ ልባዊ መሻቴ እራሴን ለእርሷ የሰጠሁ መናኟ ነኝና።
"አዎን ሳቅና ደስታዋ እውንና ዘላቂ ሆኖ ሀዘን ላይመለስ እስኪወገድላት እኔ ልጇ ዘብ እንደቆምኩ አለሁላት፡፡"
"ሁሌም የእናት ኢትዮጵያችን ሰላም ይብዛ"
አስቻለው ሌንጫ
ከፅንፈኛ ኃይሎች ጋር ተባብሮ በመሥራት የሽብር ተግባር ፈፅሟል በሚል ሲፈለግ የነበረው ጎበዜ ሲሳይ የተባለው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ
በአማራ ክልል ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለማፍረስ ከፅንፈኛ ኃይሎች ጋር ተባብሮ በመሥራት የሽብር ተግባር ፈፅሟል በሚል ሲፈለግ የነበረው ጎበዜ ሲሳይ የተባለው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሏል።
ግለሰቡ አምልጦ ጅቡቲ ከገባ በኋላ ወደሌላ አገር ሊሻገር ሲል ከዓለም አቀፉ ፖሊስ እና ከጅቡቲ መንግሥት ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር እንዲውል እና ተላልፎ ለኢትዮጵያ እንዲሰጥ ተደርጎ ዛሬ ምሽት አዲስ አበባ መግባቱን የፌዴራል ፖሊስ ገልጿል።
በአማራ ክልል ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን በማፍረስ ክልላዊ ሥልጣንን በኃይል ለመያዝ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት በህቡዕ ተደራጅተው እና ተቀናጅተው በሚንቀሳቀሱ ፅንፈኛ ኃይሎች ላይ የማያዳግም ሕጋዊ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል ሚያዚያ 22 ቀን 2015 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ማስታወቁ ይታወሳል።
በዚህ መሠረትም፦
1. ሀብታሙ አያሌው፣
2. ምንአላቸው ስማቸው
3. ብሩክ ይባስ እና
4. እየሩሳሌም ተ/ፃዲቅ
5. ዘመድኩን በቀለ
6. ልደቱ አያሌው
7. መሳይ መኮንን
8. ጎበዜ ሲሳይ
9. ምህረት ወዳጆ (ምሬ ወዳጆ)
10. በለጠ ጋሻው እና
11. ሙሉጌታ አንበርብር የተባሉት ተጠርጣሪዎች በፈፀሙት የሽብር ተግባር እንደሚፈለጉ እና ከዓለም አቀፉ የፖሊስ ድርጅት ኢንተርፖል ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር በማዋል ለሕግ እንደሚቀርቡ የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ማሳወቁ ይታወሳል።
ከነዚህ ተጠርጣሪዎች መካከልም ጎበዜ ሲሳይ ዘገየ የተባለው ግለሰብ፣ በአማራ ክልል ቆቦ አካባቢ የፅንፈኛ ታጣቂ ኃይሎችን በማደራጀት፣ በቅርቡም በጽንፈኞች ግድያ የተፈጸመበትን የአቶ ግርማ የሺጥላን ግድያ በማስተባበር ሚና እንደነበረው፣ በመከላከያ እና በሕዝቡ ላይ ፅንፈኞች ጥቃት እንዲያደርሱ በማደራጀት እና ቃል አቀባይ ሆኖ በማስተባበር የሽብር ተግባር ውስጥ በመሳተፍ ተጠርጣሪ በመሆን ሲፈለግ ቆይቷል።
ግለሰቡ አማራ ክልልን በማሸበር እና ሥልጣንን በኃይል በመቀማት በቀጣይም የፌዴራል መንግሥትን ለማፍረስ ሲንቀሳቀስ ከነበረ ፅንፈኛ አካል ጋር በመተባበር ሲሠራ እንደነበር በመጠርጠሩ፣ ግለሰቡን ጨምሮ ሌሎች በቁጥጥር ስር ያልዋሉ ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ የጋራ ግብረ ኃይሉ ከኢንተርፖል ጋር ባለ ስምምነት መሠረት ሲሠራ መቆየቱን ገልፆ ነበር።
በዚሁ መሠረትም አስፈላጊውን ፎርማሊቲ እና አግባብ ያላቸው መረጃዎችን በማደራጀት ጎበዜ ሲሳይ የተባለው ግለሰብ አምልጦ ጅቡቲ ከገባ በኋላ ወደሌላ አገር ሊሻገር ሲል ከዓለም አቀፉ ፖሊስ እና ከጅቡቲ መንግሥት ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር እንዲውል እና ተላልፎ ለኢትዮጵያ እንዲሰጥ ተደርጎ ዛሬ ምሽት አዲስ አበባ ገብቷል።
የፀጥታ እና የጋራ ግብረ ኃይል አሁንም ኢትዮጵያ ባላት ስምምነት መሠረት ሌሎች ያልተያዙ የሽብር ቡድኑ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል እየሠራ መሆኑን ለኢዜአ ገልጿል።
የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ ከሃያ ሺህ ጫማ ከፍታ በላይ መጓዝ የሚችል ሮኬት አስወነጨፈ
የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ "አፄ ቴዎድሮስ 2015" የሚል ስያሜ የተሰጣትን ሮኬት ከሃያ ሺህ ጫማ ከፍታ በላይ አስወንጭፎ ስኬታማ ሙከራ ማድረግ ችሏል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በህዋ ምርምር ላይ ትኩረት በማድረግ ጋፋት የህዋ ምህንድስና ልማት ማዕከልንም አቋቁሞ የተለያዩ የምርምር ሥራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል።
የማዕከሉ መሥራችና ሰብሳቢ አቶ በለጠ ጌታቸው፣ ሮኬት የማስወንጨፉ ሙከራ ከዚህ በፊት ከተሞከሩት የተሻለ ምርምር የተደረገበትና ለህዋ ሳይንስ የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን ተሸክሞ መሄድ የሚያስችል ቴክኖሎጅ የተገጠመለት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ በህዋ ሳይንስ ዘርፍ ትኩረት ሰጥታ እየሠራች ነው ያሉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር አነጋግረኝ ጋሻው በዩኒቨርሲቲው ተማሪና ተመራማሪዎች የተሠራው ሥራ ኢትዮጵያ እንደሰለጠኑት ሀገራት በህዋ ምርምር የበኩሏን ድርሻ እንደምትይዝ ጅምሩን ያሳየ ነው ብለዋል።
በኢትዮጵያ ከሚካሄዱት የህዋ ሳይንስ ምርምሮች ውስጥ በሮኬት ሳይንስ ዘርፍ ደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑንም ገልጸዋል።
የአማራ ሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሳሉ አያሌው (ዶ.ር) እንደዚህ አይነት ሙከራዎች ኢትዮጵያ ወደፊት በዘርፉ ለምታደርገው ምርምር አጋዥ ናቸው ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል።
⚽ ሃሙስ ምሽት የወጡ የስፖርት ዜናዎች፡ ሜሲ፣ ቤሊንግሃም፣ ሼክ ጃሲም፣ ኔይማር፣ ምባፔ፣ ሮናልዶ፣ ራይስ፣ ኬቨን ዴብሩይን፣ ኤርሊንግ ሃላንድ፣ ራፊንሃ፣ ጀምስ ሚልነር፣ ካልቪን ፊሊፕስ እና ሌሎችም ...
◾️የ35 አመቱ አርጀንቲናዊ የፊት መስመር ተጫዋች እንዲሁም የስምንት ባለንድኦር ባለቤት ሊዮኔል ሜሲ ወደ ሳኡዲ አረቢያው ክለብ አል ሂላል የሚያቀና ከሆነ 320 ሚሊየን ፓውንድ ክፍያ ቀርቦለታል በተጨማሪም ሊዮ በክረምቱ የፈረንሳዩን ሻምፕዮን ፒኤስጂን እንደሚለቅ ተረጋግጧል። (Telegraph )
◾️የሳውዲው ክለብ አል ሂላል የሜሲን ፊርማ ለማግኘት በሜጀር ሊጉ ሶከር ከሚገኘው ኢንተር ሚያሚ ጋር ትልቅ ፉክክር ይጠብቀዋል ፣ የሚጀር ሊግ ሶከሩ ክለብ ኢንተር ሚያሚ የቀድሞ ማንቸስተር ዩናይትድ እና እንግሊዝ ኮከብ ተጫዋች ዴቪድ ቤካም ንብረት እንደሆነ ይታወቃል ። ( The Guardian )
◾️ሪያል ማድሪድ የ19 አመቱን የቦርሺያ ዶርትመንዱን እንግሊዛዊ አማካኝ ጁድ ቤሊንግሃምን ለማስፈረም እየተነጋገረ ቢሆንም የጀርመኑ ክለብ ግን እስካሁን ከስፔኑ ሀያል ክለብ ሪያል ማድሪድ የቀረበለትን ጥያቄ አልተቀበለም ። ( Sky German )
◾️ሼክ ጃሲም የማንቸስተር ዩናይትድ ንብረትነት የግላቸው ማድረግ የሚችሉ ከሆነ እንደ መጀመሪያ ፈራሚነት እቅዳቸው ውስጥ ያስገቢትን ኔይማር ጁኒየር ቢሆንም አሁን ግን በምትኩ ፈረንሳዊውን የ24 አመቱን ኪሊያን ምባፔን ፣ የ26 አመቱ የባየር ሙኒክ እንዲሁም የፈረንሳይ የፊት መስመር ተጫዋች ኪንግስሊ ኮማን እና የሪያል ማድሪዱን ሁለገብ ተጫዋች ኤድዋርዶ ካማቪንጋን ለማስፈረም እንደ እቅድነት ይዘዋል። ( Bild's Christian Falk)
◾️የ24 አመቱ የዌስትሃም እና የእንግሊዝ አማካኝ ዴክላን ራይስ ፣ የ23 አመቱ የባየር ሊቨርኩሰን እና የፈረንሳይ የፊት መስመር አጥቂ ሙሳ ዲያቢ ፣ የ30 አመቱ የክሪስታል ፓላስ እና የአይቮሬኮስት የፊት መስመር አጥቂ ዊልፍሬድ ዛሃ ፣ የ22 አመቱ የፓላስ እና የእንግሊዝ ተከላካይ ማርክ ጉሂ በመድፈኞቹ አለቃ ሚኬል አርቴታ በክረምቱ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ተጫዋቾች ናቸው። ( Mail )
◾️ቼልሲዎች የዊልፍሬድ ዛሃን ፊርማ ለማግኘት የሚደረገው ፉክክርን ተቀላቅለዋል ይህ የሆነበት ምክንያት የቀድሞ የቶትንሀም አሰልጣኝ ማውሪዝዮ ፖቼቲኖ የቼልሲ አለቃ ለመሆን በመቃረባቸው ሲሆን ከዚህ ቀደም አርጀንቲናዊው አሰልጣኝ የስፐርስ ቤት እያሉ ሊያስፈርሙት የሚፈልጉት ተጫዋች ነበር። ( Mail )
◾️የቀድሞ የባየር ሙኒክ አለቃ ጁሊያን ናጌልስማን እንዲሁም በጀርመኑ ክለብ ባየርን ሊቨርኩሰን ጥሩ የሚባል ቡድንን መገንባት የቻለው ስፓንያርዱ አሰልጣኝ ዣቪ አሎንሶ የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶትንሀምን በአሰልጣኝነት እንደሚቀበሉት ይጠበቃል በተጨማሪ ቶተንሃም አሰልጣኝነት ሹመት ሚና ከስፖርቲንግ ሊዝበን አለቃ ሩበን አሞሪም ጋር የመጀመሪያ ግንኙነት ያደረጉ ሲሆን የ38 አመቱ አለቃ በውድድር አመቱ መጨረሻ ስራውን ለመቀበል ዝግጁ መሆኑን ነግሯቸዋል። ( Times )
◾️ኔዘርላንዳዊው አጥቂ ዉት ዌገርስት በማንቸስተር ዩናይትድ የመቆየት ፍላጎት አለው ነገርግን ቀያይ ሰይጣኖቹ የ30 አመቱ ተጫዋች ከበርንሌይ ያለው ውሰት ሲያልቅ በኦልድትራፎርድ ስለመቆየት ገና ድርድር አልጀመሩም። ( Telegraph )
◾️የጣሊያኑ ክለብ ሮማ ከእንግሊዞቹ ማንቸስተር ዩናይትድ እና ቶተንሃም እንዲሁም ከፈረንሳዩ ሀያል ክለብ ፓሪስ ሴንት ዠርሜይን በመቅደም የ25 አመቱን የእንግሊዝ ፊት መስመር ተጫዋች ታሚ አብረሀምን በክረምቱ የዝውውር መስኮት ከወደጣሊያን ለማስቀረት £35-40m አስቀምጠዋል። ( Calciomercato- in Italian )
◾️በዚህ የውድድር አመት በፈረሳይ ሊግ አ ጥሩ ጊዜን እያሳለፈ የሚገኘው ማርሴይ በክረምቱ ከኮንትራት ነፃ የሚሆነውን ዊልፍሬድ ዛሃን ለማስፈረም ጥረት ማድረግ የጀመሩ ሲሆን ልጁን በቻምፒየንስ ሊግ ተሳትፏቸው ሊያሳምኑት አቅደዋል ። ( Football Mercato-In French )
◾️ኒውካስትል የባርሴሎናውን እና ብራዚላዊውን ባለ ግራ እግር ጥበበኛ ራፊንሀን ለማስፈረም 70ሚ.ፓ ያዘጋጁ ሲሆን ልጁ ወደ ፕርሚየር ሊግ ለመመለስ ያለው ፍላጎት ልጁን የግላቸው ለማድረግ ይረዳቸዋል። ( The Sun )
◾️ቼልሲዎች የ33 አመቱን ጋቦናዊ የፊት መስመር ተጫዋች ፔር ኤሜሬክ ኦባምያንግን በክረምቱ ለመልቀቅ ዝግጁ ናቸው። ( telegraph )
◾️አስቶንቪላ በዚህ ክረምት የባርሴሎና የእግር ኳስ ዳይሬክተርነቱን ለመልቀቅ የወሰነውን ማትዮ አሊሚናን ለማምጣት ጥሩ ንግግር ላይ ናቸው። ( Times )
◾️የሊቨርፑሉ አማካይ ጀምስ ሚልነር በክረምቱ በነፃ ዝውውር ብራይተንን ይቀላቀላል ፣ እንግሊዛዊው የቀረበለትን የ12 ወራት ማራዘሚያ ከመፈረም ይልቅ በውድድር አመቱ መጨረሻ ላይ ከአንፊልድ የስምንት አመት ቆይታ በኃላ መልቀቅን መርጧል። ( Goal )
◾️ሊቨርፑል የብራይተን እና የአለም ሻምፕዮኖቹ አርጀንቲና አማካኝ አሌክሲስ ማክ አሊስታርን በክረምቱ የዝውውር መስኮት ለማስፈረም የሚጥሩ ከሆነ እስከ £70M ሊያወጡ ይችላሉ ፣ የአሜክስ ስታዲየም ምንጮች እንደተናገሩት ቡድኑ በሚቀጥሉት ወራቶች ውስጥ ማክ አሊስተር ወደ ሊቨርፑል የሚያደርገው ዝውውር አይቀሬ ይመስላል ሲሉ ተደምጠዋል። ( Mail )
◾️እንግሊዛዊው ካልቪን ፊሊፕስ በማንሲቲ መቆየት እና ለወደፊት በሲቲ ቤት ትልቅ ተጫዋቾች መሆንን ይመርጣል ፣ እንግሊዛዊው ኢንተርናሽናል ተጫዋች አሁንም በፔፕ ጋርዲዮላ ጥልቅ ፍቅር አለው። ( Alex_Crook )
◾️በሌላ ዜና ኬቨን ደብሩይን እና ኤርሊንግ ሃላንድ ለሚያዝያ ወር የፕርሚየር ሊግ የወሩ ምርጥ ተጫዋች እጩ ሆነዋል እንዲሁም የፓላሱ ( ኢዜ ) ፣ የኒውካስሉ ( ኢሳቅ ) ፣ የሊቨርፑሉ ( ዲዪጎ ጆታ ) ፣ የቦርንማውዙ ( ሶላንኬ ) ፣ የአስቶንቪላው ( ኦሊ ዋትኪንስ ) ፣ የኒውካስሉ ( ካሉም ዊልሰን ) በእጩነት የቀረቡ ተጫዋቾች ናቸው።
#Update
" ውይይቱ በአብዛኛው በአዎንታዊ መልኩ የተከናወነ ቢሆንም በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ በዚህኛው የውይይት ስምምነት ላይ አልተደረሰም " - መንግሥት
በታንዛኒያ ሲካሄድ የቆየው የሰላም ውይይት የመጀመሪያ ምዕራፍ ዛሬ ተጠናቀቀ።
በኦሮሚያ ክልል ያለውን ግጭት በማስወገድ ሰላምን ለማምጣት ያለመውና በታንዛኒያ ሲካሄድ የቆየው የሰላም ውይይት የመጀመሪያ ምዕራፍ ዛሬ መጠናቀቁን መንግሥት አሳውቋል።
ውይይቱ በአብዛኛው በአዎንታዊ መልኩ የተከናወነ ቢሆንም በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ግን በዚህኛው የውይይት ምዕራፍ ስምምነት ላይ ለመድረስ አልተቻለም ብሏል፡፡
ግጭቱን በዘላቂነትና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለማስቆም እንዲቻል ሁለቱም አካላት የሰላም ውይይቱን መቀጠል አስፈላጊ መሆኑ ላይ ተግባብተዋል ተብሏል።
መንግሥት በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥትና እስካሁን ሲመራባቸው በነበሩ መሠረታዊ መርሖች መሠረት ግጭቱን በሰላማዊ መልኩ ለመፍታት መንግስት የጸና አቋም እንዳለው አሳውቋል።
መንግሥት " ኦነግ ሸኔ " እያለ የሚጠራው ታጣቂው የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት የሰላም ውይይቱን በተመለከተ የሚሰጠውን ማብራሪያ ተከታትለን እናሳውቃለን።
ጃዊ ወረዳ‼
በአዊ ብሔረሰብ አስተዳድር በጃዊ ወረዳ ከመንግሥት ጋር ቅሬታ በመፍጠር ጫካ ገብተው የነበሩ የታጠቁ ኃይሎች በአገር ሽማግሌዎች አወያይነት እርቅ ፈፅመው ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ መደረጉን ዞኑ አስታውቋል ።
በዕለቱ 118 አባላት በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ዳግም ወንጀል ላለመሥራት የስምምነት ሰነድ ላይ የፈርሙ ሲሆኑ የያዙትን የነፍስ ወከፍ መሣሪያ አስመዝግባው ሕጋዊ ማድረግ መቻሉን ከአዊ ብሔረሰብ አስተዳድር ኮሙኒኬሽ መምሪያ መረጃ ያመለክታል።
ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇
"ተንፈላስሼባት አይደለም"
" እወዳታለሁ ስላችሁ ተንፈላስሼባት ሳይሆን ያለኝን ሁሉ ሰጥቺያት እስክሞትላት ድረስ ነው።
ሰንደቋን በልቤም በክንዴም አትሜ፤ሰላም ነሺዋን ልፋለምላት ስወስንም የመውደዴን እውነት በተግባር አረጋግጬላት ነው።
ሰው እንደመሆኔ ደስታ፣ምቾት፣ቤተሰባዊ ፍቅርና የህይወት መልካም ገጸ-በረከቶች ሁሉ ሳያምሩኝ ቀርተው አይደለም።እሷን መውደዴ ከምንም በላይ በልጦብኝ ነው።
ለኢትዮጵያዬ አፍላ ወጣትነቴን ሸልሚያት፣በሙሉ ጊዜዬ በእውቀትና በጉልበቴ ያለ አንዳች ስስት ሳገለግላት፤ትርጉም ያለው ዜግነታዊ ሚናን የመወጣት ክብር ይሰማኛልና፤ልቤ ሃሴት ታደርጋለች።
የውትድርና ህይወቴ ሀገሬን በስሚ ስሚ አሊያም በንባብ ሳይሆን በተግባር ተዘዋውሬ እንዳውቃት አስችሎኛል መሬቷን ብቻ ሳይሆን የቆምኩለት ህዝቤን ባህል፣ወግ፣የአኗኗር ዘይቤና አይጠገቤ ፍቅር ኖሬው እንዳውቅ ሆኛለሁ።
የኢትዮጵያዊነት እምነትና ፍቅሬ የሚቀዳው ከህዝቤ ወሰን አልባ ተዝቆ የማያልቅ ልባዊ ፍቅር ነውና መቼም የማይናወጽ እንደሆነ እስከ ነፍሴ ህቅታ አብሮኝ ይዘልቃል።
ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ከምስራቅ እስከ ምዕራብ መላው የውድ ሀገሬ ህዝብ መልከ ብዙ ውብ ባህላዊ እሴት፣ቋንቋና ሁለንተናዊ መስተጋብር የመንፈስ እርካታ አጎናጻፊ ውብ ቀለሜ ነውና የማበላለልጠው መንደርም ሆነ ሌላ የለኝም።
ይህ ጽኑ እምነቴ፣ከኢትዮጵያችን ጥልቅ ፍቅርና መውደድ ጋር ተጣምረው ለሀገሬና ህዝቤ ሙሉ እኔነቴን የሰጠሁ ወጥቶ-አደሯ መሆኔ ክብርና ኩራቴ እንደሆነ በተሟላ ሞያዊ ብቃት ንቁ የሰላም ዘብ የመሆኔ እውነት በህይወቴ እስካለሁ ይቀጥላል።
እናም እኔ ወታደሩ ሀገሬን እወዳታለሁ ስላችሁ ተንፈላስሼባት ሳይሆን እስክሞትላት ነው!!!!
"ክብር ለሠላማችን ዘብ ጀግናው ወታደር"
መንግስት በዕውቀቱ ህዝብ ገንዘቡ ተባብረው ሰሩት። ይህ ውብ ምድር ለኛ ብቻ የተሰጠ ምድር ነው። የዚች ለምለም አገር ልጆች ነን። ድንግል መሬት የዘን የሚለውን ቃል ስንሰማ ግር የሚለን ሰዎች አለን። ወገኖቸ በሀብት ብዛት ጆሯቸውን የደፈኑት የአረብ ባህረ ሰላጤው አገሮች አሸዋ መሬታቸውን እንዲህ ውብ ለማድረግ ቢሊዮን ዶላር ያፈሳሉ። ዶላሩ ፈሶም ሰው ሰራሽ እንጅ የተፈጥሮን ውበት መሆን አይችልም። እኛ ግን አይናችን ተጋረደ እንጅ ሀያሉ ፈጣሪ በራሱ ጥበብ እንዲህ ውብ አድርጎ ትንሽ ብቻ የናተን ጥበብ ተጠቅማችሁ ተጠቀሙበት ብሎ መርጦ የሰጠን ምድር አለችን። በምድር ላይ ገነት የለም እንጅ የምድራችን ገነት ኢትዮዽያ ናት። የሰው ልጅ ተወለደ፣ አደገ ጥሩ ስራ ሰራ የሚባለው እራሱን ሲለውጥ ብቻ አይደለም እንዲህ ያለ የለውጥ አዕምሮን ይዞ ለህዝብ ሰርቶ ሲያሳይ ነው። የቀረን መተማመንና መስማማት ነው። ከተማመን ከተስማማን፣ ከተከባበርን ከሁሉም በላይ የሰውን ልጅ የፍቅርን አሸናፊነት ከተረዳን ይች 24 ሰአት የምንገዳደልባት ኢትዮዽያ እንዲህ ውብና ለሰው ልጆች ሁሉ ምቹ ሆና የተሰጠችን መሆኗን አምነን ከመሰዳደብ መነጋገር፣ ና ግጠመኝ ከማለት የሰላም እጆችን ካስቀደምን፣ ሰላም ካወረድን በቅርብ አመት የአፍሪካን የባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤትነትን ተቀብለን አንገታችንን ቀና አድርገን እንራመዳለን።
በለው ቁረጠው አፍረሰው ቀማው አፈናቅለው ወደመጣበት መልሰው፣ የሚለውን ዘፈን ከደጋገምነው ግን ደማስቆም ውብ ነበረች ለማፍረስ ግን የ12 ቀን ጦርነት ነው የበቃት። ከስህተታችን ተምረን እንዲህ ያለ የልማት ልዕልናን ተመኝተን ተግተን ከሰራን ግን ልክ እንደ ሀላላ ያለ ውብ ስራ እየሰራን አለምን ሁሉ ወደኛ እንዲመጣ እናስገድደዋለን። ቅን እንጅ የሀገር ቅንቅን አታድርገን ( አሜን )
#ሱሌማን_አብደላ
⚽ ሰኞ አመሻሽ የወጡ የቅድመ ዝውውር ወሬዎች: ሃላንድ፣ ዛሃ፣ ተራራ፣ ቭላሆቪች፣ ማዲሰን፣ አብርሀም፣ ዲባላ፣ ዚነዲን ዚዳን፣ አክራፍ ሃኪሚ፣ ሳዲዮ ማኔ, ቻርሊ ፓቲኖ..
🆕➥ ማንቸስተር ሲቲ ከ 22 አመቱ ኖርዊዊው አጥቂ ኤርሊንግ ሃላንድ ጋር በአዲስ ኮንትራት ለመነጋገር በዝግጅት ላይ ናቸው። (Football Insider)
🆕➥ የ30 አመቱ የክሪስታል ፓላስ እና አይቮሪኮስት አጥቂ ዊልፍሬድ ዛሃ የአርሰናል፣ ጁቬንቱስ፣ ቼልሲ እና ባርሴሎና ለዝውውር የሚፈለግ ተጭዋች ሆኗል። (Telegraph)
🆕➥ ቼልሲዎች የ24 አመቱ እንግሊዛዊ አማካኝ ሜሰን ማውንት ዝውውር ከባየር ሙኒክ እና ሊቨርፑል የሚቀርብላቸውን ጥያቄ ውድቅ እንደሚያደርጉ ታውቋል። ሰማያዊዎቹ ያቀረቡለትን አዲስ ኮንትራት እንደሚፈራረም ተማምነዋል። (Football Insider)
🆕➥ የ23 አመቱ የጁቬንቱስ ሰርቢያዊ አጥቂ ዱሳን ቭላሆቪች ለአርሰናል እና ባየር ሙኒክ እንዲያስፈርሙት ቀርቦላቸዋል። (Tutto Mercato Web - in Italian)
🆕➥ ቻርሊ ፓቲኖ አርሰናልን በዚህ ክረምት በቋሚነት ሊለቅ ነው። የ19 አመቱ አማካይ መደበኛነት የሚጫወትበትን ቡድን መቀላቀል ይፈልጋል። ይሄንን ለአሁን በአርሰናል የሚያሳካ አይመስልም። በድጋሚ ደሞ ከአርሰናል በውሰት መሰጠት አይፈልግም ከዛ ይልቅ በቋሚነት መውጣትን ይመርጣል። (TheAthleticFC)
🆕➥ ሌስተር ሲቲዎች ከሊጉ ከመውረድ ለግዜው ቢርቁም የ26 አመቱን እንግሊዛዊ ኢንተርናሽናል ጀምስ ማዲሰንን በዚህ ክረምት ይሸጡታል። ማንችስተር ዩናይትድ፣ ቶትንሀም እና ኒውካስል የተጭዋቹ ፈላጊ ናቸው። (Telegraph - subscription)
🆕➥ ማንቸስተር ዩናይትድ እና ፓሪስ ሴንት ዠርሜይን የ25 አመቱ እንግሊዛዊ አጥቂ ታሚ አብርሀም ቅዳሜ ከኤሲ ሚላን ጋር ለሮማ ሲጫወት እንቅስቃሴውን ለመከታተል መልማዮቻቸውን ልከዋል። (Gazzetta dello Sport - in Italian)
🆕➥ ሮማዎች የ25 አመቱን ቤልጄማዊ አማካኝ ዩሪ ቲሌማንስን ለማዛወር እያሰቡ ሲሆን የሌስተር ኮንትራቱ በውድድር አመቱ መጨረሻ ሲያልቅ በነፃ ዝውውር ሊያስፈርሙ ከሚፈልጉት ክለቦች ጋር ፉክክሩን ተቀላቅለዋል። (Calcio Mercato Web - in Italian)
🆕➥ የቀድሞ የሪያል ማድሪድ አሰልጣኝ ዚነዲን ዚዳን በዚህ ክረምት ወደ ቀድሞ ስራው አሰልጣኝነት ማኔጅመንት የመመለስ ፍላጎት አለው። ጁቬንቱስ፣ ፓሪስ ሴንት ዠርሜይን እና ማርሴይን ሊቀጥሩት ፈልገዋል። አንቼሎቲ ከለቀቁም ወደ ማድሪድ ሊመለስ ይችላል። (Calciomercato - in Italian)
🆕➥ የ16 አመቱ እንግሊዛዊ አጥቂ ማኪሴ ኢቫንስን ከሚከታተሉት የፕሪምየር ሊግ ቡድኖች መካከል ቼልሲ ይጠቀሳል። (Marca - in Spanish)
🆕➥ ኒውካስል ዩናይትዶች የ29 አመቱን የሮማውን አርጀንቲናዊ የፊት መስመር ተጫዋች ፓውሎ ዲባላን ለማስፈረም እያጤኑ ነው። (Sun)
🆕➥ ሼፊልድ ዩናይትድ የ26 አመቱን ስኮትላንዳዊ አጥቂ ኦሊ ማክበርኒን ወደ ፕሪምየር ሊግ ማደጉን ካረጋገጠ በኋላ ኮንትራቱን ሊያራዝሙለት ከውሳኔ ላይ ደርሰዋል። (Sun)
🆕➥ ማንቸስተር ዩናይትዶች የፓሪስ ሴንት ዠርሜይን የ24 አመቱን ሞሮኮ ተከላካይ ሃችራፍፍ ሃኪሚን ለማስፈረም ይፈልጋሉ። (Football Insider)
🆕➥ ቼልሲዎች ከባየር ሙኒኩ የ31 አመቱ ሴኔጋላዊ የፊት መስመር ተጫዋች ሳዲዮ ማኔ ጋር ስማቸው ተያይዟል። ባቫሪያኖቹ ሴኔጋላዊውን አጥቂ ለገዢ ክለቦች በማቅረብ ላይ ናቸው። (Football London)
🆕➥ የሳውዲ አረቢያው ክለብ አል ናስር በሲቪያ በውሰት የሚገኘውን የማንቸስተር ዩናይትድን የ30 አመቱ ብራዚላዊ ተከላካይ አሌክስ ቴልስን እየተከታተለ ነው። (AS)
📌 ከተመቻችሁ LIKE ማድረጋችሁን አትርሱ !
📌 ጓደኞቻችሁ እንዲያነቡት SHARE ያድርጉላቸው !
📌 አስተያየት ካላችሁም ከታች COMMENT አድርጉ !
ከፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል የተሰጠ መግለጫ
በአማራ ክልል ሕገ-መንግስታዊ ሥርዓቱን በማፍረስ ክልላዊ ስልጣንን በኃይል ለመያዝ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት በህቡዕ ተደራጅተውና ተቀናጅተው በሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ ኃይሎች ላይ የማያዳግም ህጋዊ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል ሚያዚያ 20 ቀን 2015 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ማስታወቁ ይታወሳል።
በመሆኑም የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይል እየወሰደ ባለው እርምጃ በዚህ ህቡዕ አደረጃጀት ውስጥ ሲንቀሳቀሱና የሽብር ተግባር ሲፈጽሙ የተገኙ 47 ተጠርጣሪዎችን ከበርካታ የነፍስ ወከፍና የቡድን መሣሪያዎች፣ ቦንቦችና ተቀጣጣይ ፈንጂዎች እንዲሁም ከሳተላይት መገናኛ መሣሪያዎች እና የተለያዩ መረጃዎችን ከያዙ ላፕቶፖች ጋር በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ለመገናኛ ብዙኃን በላከው መግለጫ አመልክቷል።
ተጠርጣሪዎቹ የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮችን የግድያ ዒላማ በማድረግ፤ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል በመናድ የክልሉን መንግሥታዊ መዋቅር በመቆጣጠር የፌደራል መንግሥትን ለመጣል በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ተደራጅተው እና ተቀናጅተው በህቡዕ ሲንቀሳቀሱ እንደተደረሰባቸው አስታውቋል።
ግብረ-ኃይሉ ለመገናኛ ብዙኃን በላከው መግለጫ፤ መንግስት የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት እና ለሐሳብ ትግል ሰፊ ዕድል በመስጠቱ እንዲሁም ችግሮች በውይይት እንዲፈቱ ባደረገው ጥረት ብዙዎች ይሄንን ዕድል መጠቀማቸውን አስታውሷል።
ይሁንና የአማራን ህዝብ የማይወክሉ እነዚህ ጽንፈኛ ኃይሎች የመንግሥትን ሰላማዊ አማራጭ በመግፋት በውጭ ከሚገኙ ግብረ-አባሮቻቸው ጋር በህቡዕ በመገናኘት የፖለቲካ፣ የወታደራዊ፣ የኢንተለጀንስ፣ የሚዲያ እና የፋይናንስ ክንፍ ማቋቋምቸው እንደተደረሰበት መግለጫው አመልክቷል።
የጋራ ግብረ-ኃይሉ መግለጫ እንዳመለከተው፤ የጽንፈኛ ኃይሎችን የፖለቲካ፣ የወታደራዊ፣ የኢንተለጀንስ፣ የፋይናንስ እና የሚዲያ ክንፍ የሚመራው ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ የተባለ ግለሰብ ሲሆን፤ ይህ ክንፍ በተለያዩ የውጭ ሀገራት ከሚገኙ 16 ጽንፈኛ የዲያስፖራ አባላት ጋር ትስስር በመፍጠር በሚያገኛቸው የሎጀስቲክስ እና የፋይናንስ ድጋፎች በአማራ ክልል ከባህርዳር ከተማ ጀምሮ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ታጣቂዎችን የመመልመል፣ የማሰልጠን፣ የማስታጠቅና የማሠማራት ተግባር በማከናወን በክልልና በፌደራል ደረጃ ሽብር እና ግድያ እንዲፈጽሙ ተልዕኮ ሲሰጥ እንደነበር በተደረገ ክትትል እና ምርመራ ተደርሶበታል ብሏል መግለጫው።
ለዚህም በለጠ ሸጋው እና ምሕረት ወዳጆ ወይም በቅጽል ስሙ ምሬ ወዳጆ በተባሉት የጽንፈኛ ኃይሉ ታጣቂ መሪዎች እና ግብረ-አባሮቻቸው ሰሞኑን በትውልድ በቀኤአቸው ግፍና ጭካኔ በተሞለበት አኳሃን የተገደሉት የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባልና የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ የሺጥላ እና የጥቃት ሰለባ የሆኑ የሥራ ባልደረቦቻቸው ማሳያ ናቸው ብሏል የጋራ ግብረ-ኃይሉ መግለጫ።
የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል መግለጫ አክሎም፤ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የሚገኙ እነዚህ ጽንፈኛ ኃይሎች በፈጠሩት ህቡዕ አደረጃጀት እኩይ ዓላማቸውን ለማስፈጸም በአማራና በሌሎች አካባቢዎች በሚገኙ 130 ወረዳዎች የመለመላቸውንና በህቡዕ ያዘጋጇቸውን 450 ግለሰቦች የአማራ ክልል ህዝብ የመረጣቸውንና በተለያዩ የአመራር እርከኖች ላይ ያስቀመጣቸውን በኃይል በማስወገድ በራሳቸው መዋቅር የመተካት ሥራ ሲሰሩ እንደነበር በክትትል እና በምርመራ የተደረሰባቸው መሆኑን አስታውቋል።
በተጨማሪም ጽንፈኛ ኃይሎች የክልሉን የፀጥታ ኃይልንም በራሳቸው ታጣቂዎች ለመቀየር ተዘጋጅተው እንደነበር የተገኛው መረጃ ማመላከቱን ገልጿል።
ዶ/ር መሥፍን ኃ/ማርያም፣ ዶ/ር ግሩም ላቀውና ሌሎችም በተለያዩ የውጭ ሀገራት የሚኖሩ የጽንፈኛ ኃይሉ ተባባሪዎች ከውጭ ሆነው የፖለቲካ ክንፉን እንደሚያስተባብሩ፤ አንተነህ ብርሃን፣ ወርቁ ጓዴና ሌሎችም ከሀገር ውስጥና ከውጭ የሚላከውን ገንዘብ እንዲቀበሉና ለሽብር ተልዕኮ ማስፈፀሚያ እንዲያውሉ የባንክ አካውንት እንደተከፈተላቸው በክትትልና በተደረገው ምርመራ መረጋገጡን የገለፀው የጋራ ግብረ-ኃይሉ መግለጫ፤ ቴዎድሮስ አስፋውን ጨምሮ ሌሎችም በዚሁ የሽብር እንቅስቃሴ ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን መግለጫው አስታውቋል።
መግለጫው አያይዞም የእነዚህ ጽንፈኛ ኃይሎችን የሚዲያና ፕሮፓጋንዳ ክንፍ የሚመራው መስከርም አበራ በተባለች ግለሰብ መሆኑን ጠቅሶ፤ በዚህ ህቡዕ አደረጃጀት ውስጥ ከሀገር ውስጥ ዳዊት በጋሻው የተባለ ግለሰብ እንዲሁም ከተለያዩ የውጭ ሀገራት ደግሞ ከኢትዮ 360 እና መረጃ ቲቪ ሀብታሙ አያሌው፣ ምንአላቸው ስማቸው፣ ብሩክ ይባስ እና እየሩሳሌም ተ/ፃዲቅ በተጨማሪም ዘመድኩን በቀለ እና ልደቱ አያሌው ከአንከር ሚዲያ መሳይ መኮንን እንዲሁም ሌሎች ግለሰቦች የዚህ እኩይ ዓላማ አስፈፃሚ አባላት መሆናቸውን በምርመራ መረጋገጡን ገልጿል።
እነዚህ ጽንፈኛ ኃይሎች የሀሰት ወሬዎችን በመፍጠር እና ከፍተኛ የሽብር ፕሮፓጋንዳ በመንዛት ህዝቡን በብሄር እና በሀይማኖት በመከፋፈልና በማጋጨት የክልል እና የፌደራል መንግሥትን በኃይል ለመጣል እንዲሁም ሀገሪቱ ከጀመረችው የለውጥና የልማት መንገድ ወጥታ ወደ ለየለት ሁከትና ትርምስ እንድትገባ በህቡዕ ተደራጅተው እየሠሩ መሆናቸውን የገለፀው የጋራ ግብረ ኃይሉ፤ በሀገር ውስጥና በውጭ ሆነው በሀሰት ሀገር ለማፍረስ የሚሰሩ እነዚህን ጨምሮ ሌሎችም በህቡዕ አደረጃጀቱ ውስጥ ያሉ ግለሰቦችም ጭምር በሽብርተኝነት ምርመራ እየተጣራባቸው መሆኑን መግለጫው አመልክቷል።
እነዚህ የሽብር ኃይሎች ከሚኖሩባቸው ሀገራት በአለም አቀፍ የፖሊስ ድርጅት (ኢንተርፖል) እንዲሁም እነሱ ከሚኖሩባቸው ሀገራት መንግሥት የፀጥታ እና የደኅንነት ተቋማት ጋር በተመሠረቱ የትብብር ማዕቀፎች አማካኝነት ወደ ሀገር ቤት ተላልፈው እንዲሰጡ በህግም እንዲጠየቁ እየሰራ መሆኑን እና ይህንኑ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።
የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል መግለጫ አክሎም፤ እነዚህ ውጭ ሀገር የሚኖሩ ተፈላጊዎች ከውጭ ሀገር በሚያገኙት እና በሀገር ውስጥ ያላቸውን ሀብት ተጠቅመው ለዚህ እኩይ ተግባር እያዋሉ መሆኑን በምርመራ የተደረሰበት ስለሆነ በሀገር ውስጥ ያላቸውን ሀብት የመለየት እና በህግ የመቆጣጠር ስራ እየተሰራ መሆኑንም ጭምር አስታውቋል።
ሕገ-መንግሥቱንና ሕገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለማፍረስ እየተንቀሳቀሱ የነበሩ እነዚህ ጽንፈኛ ኃይሎች የኢትዮጵያን አንድነት ከማይፈልጉ የውጭ ፀረ ሰላም ኃይሎች ጋር ተቀናጅተው መንግሥትን በኃይል ለማስወገድ ሲሰሩ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው የሚገኝ መሆኑን ያመለከተው የጋራ ግብረኃይሉ መግለጫ፤ ኅብረተሰቡ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የሚወሰደውን እርምጃ ከትጥቅ ማስፈታት ጋር በማያያዝ ውዥንብር ለመፍጠርና የተሳሳተ መረጃ ለማሰራጨት ከሚጥሩ አካላት ራሱን እንዲጠብቅ በጋራ እንዲታገል ጥሪ አቅርቧል።
በመጨረሻም የተጀመረው ህጋዊ ኦፕሬሽን ከግቡ እንዲደርስ ህብረተሰቡ እያደረገ ላለው ከፍተኛ ተሳትፎ የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ምስጋና እያቀረበ፤ በህግ ቁጥጥር ሥር እንዲውሉ ጥብቅ ክትትል እየተደረገባቸው ያሉ ተፈላጊዎችን ካሉበት ጠቁሞ እንዲያሲዝ በዚህ አጋጣሚ ጥሪውን እያቀረበ በቀጣይ የምንደርስበትን ውጤት ለህዝብ እየገለፀ እንደሚሄድ ያስታውቃል።
የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል
