የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
الذهاب إلى القناة على Telegram
5 204
المشتركون
-11024 ساعات
-1 9137 أيام
-2 77030 أيام
أرشيف المشاركات
ዛሬ ከለሊቱ 8:00 ሰዓት ጀምሮ ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ለጊዜው ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ፡፡
በመስቀል አደባባይ የሚካሄደው ፕሮግራም ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ስለሚሆኑ አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል። በመሆኑም፡-
• ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚጓዙ ተሽከርካሪዎች ኡራኤል አደባባይ ላይ
• ከቦሌ ጌቱ ኮሜርሻል አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ በታች እና በላይ እንዲሁም ግራና ቀኝ
• ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ ጋዜቦ አደባባይ ላይ
• ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና
ሲኒማ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ የቀድሞው አራተኛ ክፍለጦር (ጥላሁን አደባባይ ላይ ዝግ )
• ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለሚጓዙ ለገሀር መብራት ላይ
• ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ ላይ
• ከራስ ሆቴል ወደ ስታድዮም ራስ ሆቴል ላይ
• ከሃያሁለት አደባባይ ወደ ኡራኤል የታችኛው መንገድ ሙሉ ለሙሉ
• መስቀል አደባባይ፣ ሜክሲኮ አደባባይ፣ አፍሪካ ህብረት ትራፊክ መብራት ፣ልደታ ፀበል እና የመከላከያ ግቢ ድረስ በመምጫና በመመለሻ ወቅት
• ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት ላይ
• ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ
• ከካዛንቺስ ሼል ወደ ባንቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ እንዲሁም
• ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወስደው መንገድ ECA ጫፍ ላይ
ለጥቅምት 15 /2016 ዓ.ም አጥቢያ ረቡዕ ከለሊቱ 8:00 ሰዓት ጀምሮ ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ለጊዜው ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ፡፡ ፕሮግራሙ በሚከበርበት ዙሪያ እና በአካባቢው በግራና በቀኝ ለረጅምም ሆነ ለአጭር ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ፍፁም የተከለከለ መሆኑን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ ገልጾ ለመላው የመከላከያ ሰራዊት አመራሮችና አባላት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃሙስ ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም
"በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት " በሚል መሪ ቃል ለሚከበረው ለዘንድሮ ለ116ኛው የሠራዊት ቀን እንኳን በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን ።
እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ የረዥም ዓመታት ሀገርን ከጠላት የመከላከል የተጋድሎ ታሪክ ካላቸው ሀገራት መካከል በጀግኖች ልጆቿ የአይበገሬነት ፊት የምትሠለፍ ታሪካዊት ሀገር ናት።
ከቀደመው ዘመን ጀምረን አሁን ላይ ያለውን እውነታ እንኳ ብንቃኝ ኢትዮጵያ በርካታ የውጪ ወራሪ ሀገራት ያሠፈሠፉባት ጥቂት የማይባሉ የውስጥ እርስ በርስ ግጭቶች የተከሰቱባት በባንዳዎች የተፈተነችበትና በየትኛውም ዘመን ያልተንበረከከች የወራሪዎችን ፈተና አልፋ ዛሬ ላይ የደረሠች ሥለመሆኗ የታሪክ ድርሳናት መዝግቧል።
በሀገራችን የጀግንነት የታሪክ መዝገብ ያልሠፈሩ ግን ደግሞ አለም ያወቃቸው ቱባ ባህሎችና ድንቅ ታሪኮች ያላት ኢትዮጵያ በታሪክ በሠራዊቷ ኮርታ እንጅ አንድም ጊዜ አፍራ እንደማታውቅ ታሪክ ህያው ምስክር ነው ።
ዛሬ ላይም በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ሀገረ ጠል በሆኑ ባንዳዎችና የፀረ ሠላም ሀይሎች ችግሮች ቢከሠቱም ጀግንነት ባህል ልምዱ እና የዘወትር ተግባሩ ባደረገው ሠራዊታችንና ህዝባችን የሠላም እንቅፋቶችን ፈተና ተቋቁማ ሀገራችን በልማት ጎዳና ላይ ትገኛለች።
በመሆኑም በየትኛውም ጊዜ እና በማንኛውም ቦታ ለሠራዊታችን ብርታት ሞራልና የጀርባ አጥንት ከሆነው ህዝባችን ጋር ሆነን ሠላማችንን እያሥቀጠልን እንገኛለን።
116ኛው የመከላከያ ሠራዊት ቀንም ይበልጥ ቃላችንን የምናደስበት በየዘመናቱ ለሀገራችን ሉዓላዊነት ሲሉ መስዋዕት የከፈሉ ጀግኖችን የምንዘክርበትና ከመላው ህዝባችን ጋር ሆነን ለሀገራችን ሠላምና ልማት ማበብ በጋራ የምንቆምበት ዕለት ጭምር ነው።
እናም እንደ መሪ ቃላችን በተፈተን ጊዜ ሁሉ ፀንተን የድል ሠራዊት ሆነን ዛሬ ላይ እንደደረሥነው ቀጣይም ከመላው ህዝባችን ጋር ለሀገራችን መክፈል ያለብንን ሁሉ ዋጋ በመክፈል የኢትዮጵያን ሠላም እና ዕድገት አፅንተን እናሥቀጥላለን ።
"በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት"
ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
#ሰበር_ዜና #ኢትዮ_ቻይና
የኢትዮጵያን የቆዳ ስፋት 80 በመቶ የሚሸፍን የሳተላይት መረጃ በነፃ ቀረበ።
የኢትዮጵያን ሙሉ የቆዳ ስፋት የሚሸፍን የሳተላይት መረጃ በነፃ ለማቅረብ ከቻይና መንግሥት ጋር ስምምነት በተደረሰ ስምምነት የቻይና መንግሥት የኢትዮጵያን 80 በመቶ የቆዳ ስፋት የሚሸፍን ሁለት ሜትር ‹‹ሪዞሊውሽን›› (የምስል ጥራት) ያለው የሳተላይት መረጃ በነጻ አቅርቧል ተብሏል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርን ጠቅሶ #ሪፖርተር እንደዘገበው የኢትዮጵያን ሙሉ የቆዳ ስፋት የሚሸፍን የሳተላይት መረጃ በየዓመቱ ለማግኘት ሥምምነት ያለ ሲሆን በስምምነቱ መሰረት ኢትዮጵያ መረጃውን ሌላ ወገን መሸጥ አትችልም።
በበጀቱ ዓመቱ የመጀመሪያ ሦስት ወራት ከቻይና መንግስት የተገኘው ይኸው የሳተላይት መረጃ አሁን ባለው ዓለም አቀፍ የገበያ ዋጋ 2.8 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያወጣ ዘገባው ያመላክታል።
ከጥቂት ዓመታት በፊት ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር በመተባበር ወደ ጠፈር የላከቻቸው ሁለት የመረጃ ሳተላይቶች የአገልግሎት ጊዜያቸውን በማጠናቀቃቸው ሥራ እንዳቆሙና በቀጣይ ሁለት ዓመታት ኢትዮጵያ የመሬት ምልከታ ሳተላይት ለማምጠቅ ማቀዷን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጆኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩትን ጠቅሶ ቢቢሲ መዘገቡ ይታወሳል።
ሪፖርተር በዚህ ዘገባው፥ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ዋቢ አድርጎ አዲስ የመሬት ምልከታ ሳተላይት ለማልማትና ለማምጠቅ በ2015 ዓ.ም. ጨረታ ወጥቶ በቂ ተጫራች ባለመገኘቱ መሰረዙን አንስቶ፤ በቀጣዮቹ ወራት ጨረታውን በድጋሚ ለማውጣት ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጿል።
