የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
الذهاب إلى القناة على Telegram
4 770
المشتركون
-23224 ساعات
-1 7917 أيام
-3 26430 أيام
أرشيف المشاركات
ነሐሴ 22 ቀን 2014 ዓ.ም
የኢፌዲሪ መከላከያ ሠራዊት የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጠባቂ በመሆኑ ሀገራዊና ህዝባዊ ኃላፊነቱን በከፍተኛ ጥንቃቄ እየፈፀመ ነው!!
አሸባሪው ኃይል የትግራይን ወጣት እየማገደ በሕዝብ ማዕበል ማጥቃቱ እኔ እየመራሁ የማልዘርፋት ሀገር ትፍረስ እኩይ ተግባሩና ፀረ ህዝብ ባህሪው አንፃር የሚጠበቅ ነው። በተቃራኒው እኛ ግን የመላው አንድ መቶ ሃያ ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵዊያን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነት ተቀብለን የምንፈፅም ህዝባዊና ፕሮፌሽናል ብሔራዊ ኃይል ስለሆንን መላውን ህዝባችንና የትግራይን ጨቅላ ህፃናት ከከንቱ እልቂት የመታደግ ሞራላዊና ህጋዊ ግዴታ አለብን፡፡
ህወኃት ያኔ ጥንት በአንደኛው የዓለም ጦርነት ስልጣኔና የዘመነ ጦር መሳሪያ ባልነበረበት ጊዜ ጦርነትን በሰው ማዕበል ገጥመህ ማሸነፍ ወረት በነረበት ወቅት እንደሚደረገው ከግብረ-ገብ፣ ከሞራልና ህጋዊነት በእጅጉ በተጣረሰ አኳሃን ገና በሰውነታቸው ያልጠነከሩ ጨቅላና ለጋ ህፃናት ከኋላ በሃይል እየገፋ በሚገባ ሰልጥኖ እስከ አፍንጫው ከታጠቀ የመከላከያና ጥምር ኃይል ፊት እያሰለፈ የእሳት እራት አድርጎ በማስፈጀት የሞት ቀኑን ለማዘግየት ታሪክ ይቅር የማይለውን ጭካኔ በገዛ ወገኑ፤ ወገናችን የትግራይ ህዝብ ላይ እየፈፀመ ነው፡፡
ስለዚህም ሰራዊታችን በህግ የተቋቋመ፣ በህግ የሚመራና በህዝብ በተመረጠ መንግስት የሚታዘዝ ሲያለማ እደሚሞገስና እንደሚሸለም ሁሉ የተሰጠው ህገ-መንግስታዊ ተልዕኮ በሚገባ ሳይፈፅም ሲቀርና ሲያበላሽ በሀገሪቱና ዓለም አቀፍ ህጎች የሚጠየቅና የሚዳኝ ሀገራዊ ኃይል ነው፡፡ ስለሆነም ህግን ተከትሎ ወገኑን ከሰቆቃና እልቂት ለመታደግ አስፈላጊውን ሁሉ መስዋእትነት በጀግንነት በመክፈል የኢትዮጵያን የግዛት አንድነትና ብሔራዊ ጥቅም ያስከብራል፡፡
የሽብር ቡድኑ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ተከፋይ፤ ጉዳይ አስፈፃሚና በወንጀል የሚፈለግ ህገ-ወጥ ሽፍታ ስለሆነ የኃላፊነትና የተጠያቂነት መንፈስ አይሰማውም፡፡ በባህሪው ምክንያት ሊሰማውም አይችልም፤ ስለዚህም ነው እንደፈለገ የሚዋሸውና የግፎች ሁሉ ጥግ የሆነ ተግባር በገዛ ወገኑ ላይ የሚፈጽመው፡፡ ስለሆነም ህዝባችንን ከዚህ አሬመኔ ቡድን ቀንበር ለማላቀቅና ከከንቱ ጭፍጨፋ ለማዳን ህዝባችንና ለሀገራችን ይጠቅማል የተባለውን ሁሉ በመስዋዕትነታችን እውን ለማድረግ በከፍተኛ ብቃትና የላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ነን፡፡
ህዝባችን ከፍጅት ለመታደግ ሲባል መሆን የሚገባውን ሁሉ አጠቃላይ ሁኔታን በማያበላሽ አግባብ ቀጣይም ሊኖር እንደሚችል መታወቅ ይኖርበታል፡፡
እኛ ታላቅና ታሪካዊ ኃላፊነት ካለበት የመከላከያ ኃይል በሚጠበቅ አግባብ፣ ሁለተናዊ በሆነና ነገን አሻግሮ በሚመለከት እሳቤ እንዲሁም በወታራዊ ሳይንስና ጥበብ የምናደርገው እና እናንተ በጋለ ጥልቅ የሀገር ፍቅር ስሜት ዛሬ፣ አሁን፣ እዚችው እዲሆን የምትፈልጉትን ሁሉ "አፍ በእጅ በሚያስይዝ" አስተማማኝና ዘላቂ በሆነ ድል ይታረቃል፡፡
ዛሬም ሆነ እስከ ወዲያኛው የኢትዮጵያን ክብርና ጥቅም ለመጉዳት የሚደረግ ከሰማይ በታች ያለ ፈተና ሁሉ እንደማንፈተን ታውቃላችሁ! ታምኑናላችሁም! ለኢትዮጵያ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦች፤ ህዝቦች ደህንነት፣ የግዛት አንድነትና ለሀገረ መንግስቱ ቀጣይነት በመቆም የምንከፍለው መስዋእትነት ክብርና ኩራታችን ነው፡፡
#ኢትዮጵያዊነት ማለት ፅናት ነው! በፅናታችን ሀገራችንን እንታደጋለን!!
ሰበር ዜና ‼️
ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት፣ ኮማንዶ፣ ልዩ ኃይልና ፋኖ በጥምረት ደቡብ ቆቦን መልሶ ተቆጣጠረ። የአራቱንም ጥምር ምት መቋቋም የተሳነው የህወሓት ጀሌ ቆቦን ለቆ ወደ አላማጣ ጉዞ ጀምሯል። እንደገና ዛሬ 4 ሰዓት አካባቢ በግዳን በኩል ለመግባት ሞክሮ አከርካሪውን ተመትቶ ተመልሷል።
ማሳሰቢያ‼️
ታጠቃለህ
ትጠቃለህ
ቦታ ትለቃለህ
ቦታ ትይዛለህ... ይህ የጦርነት ባህሪ ነው ቤትህ ሶፋ ላይ ቁጭ ብለህ ለምን ብለህ አትጠይቅ እሳቱ ላይ አንተ የለህምና ከቻልክ ለሰራዊቱ ሞራል ስጥ ካልቻልክ ዝም በል ምኑንም ስታውቅ እሳት ውስጥ ሳትሆን ሸሹ አትበል! ትዕዛዝ ሰጪ ልሁን አትበል!
መረጃ‼️
መከላከያ ሠራዊት ሀገራዊና ህዝባዊ ኃላፊነቱን በከፍተኛ ጥንቃቄ እየፈፀመ መሆኑን ገለጸ!!
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጠባቂ በመሆኑ ሀገራዊና ህዝባዊ ኃላፊነቱን በከፍተኛ ጥንቃቄ እየፈፀመ እንደሚገኝ ገለጸ፡፡
መከላከያ ሠራዊት ባወጣው መግለጫ እንደገለጸው አሸባሪው ህወሓት የትግራይን ወጣት እየማገደ በሕዝብ ማዕበል ማጥቃቱ፣ እኔ እየመራሁ የማልዘርፋት ሀገር ትፍረስ እኩይ ተግባሩና ፀረ ህዝብ ባህሪው አንፃር የሚጠበቅ ነው።
በተቃራኒው እኛ ግን የመላው 120 ሚሊየን በላይ ኢትዮጵውያን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነት ተቀብለን የምንፈፅም ህዝባዊና ፕሮፌሽናል ብሔራዊ ኃይል ስለሆንን መላውን ህዝባችንና የትግራይን ጨቅላ ህፃናት ከከንቱ እልቂት የመታደግ ሞራላዊና ህጋዊ ግዴታ አለብን ነው ያለው፡፡
ህወሓት ያኔ ጥንት በአንደኛው የዓለም ጦርነት ስልጣኔና የዘመነ ጦር መሳሪያ ባልነበረበት ጊዜ ጦርነትን በሰው ማዕበል ገጥመህ ማሸነፍ ወረት በነረበት ወቅት እንደሚደረገው ከግብረ-ገብ፣ ከሞራልና ህጋዊነት በእጅጉ በተጣረሰ አኳኋን ገና በሰውነታቸው ያልጠነከሩ ጨቅላና ለጋ ህፃናት ከኋላ በሃይል እየገፋ በሚገባ ሰልጥኖ እስከ አፍንጫው ከታጠቀ የመከላከያና ጥምር ኃይል ፊት እያሰለፈ የእሳት እራት አድርጎ በማስፈጀት የሞት ቀኑን ለማዘግየት ታሪክ ይቅር የማይለውን ጭካኔ በገዛ ወገኑ፤ ወገናችን የትግራይ ህዝብ ላይ እየፈፀመ መሆኑንም ጠቁሟል፡፡
ስለዚህም ሰራዊታችን በህግ የተቋቋመ፣ በህግ የሚመራና በህዝብ በተመረጠ መንግስት የሚታዘዝ፤ ሲያለማ እደሚሞገስና እንደሚሸለም ሁሉ የተሰጠው ህገ-መንግስታዊ ተልዕኮ በሚገባ ሳይፈፅም ሲቀርና ሲያበላሽ በሀገሪቱና ዓለም አቀፍ ህጎች የሚጠየቅና የሚዳኝ ሀገራዊ ኃይል እንደሆነም አውስቷል፡፡
ስለሆነም መከላከያ ሰራዊት ህግን ተከትሎ ወገኑን ከሰቆቃና እልቂት ለመታደግ አስፈላጊውን ሁሉ መስዋዕትነት በጀግንነት በመክፈል የኢትዮጵያን የግዛት አንድነትና ብሔራዊ ጥቅም ያስከብራል ነው ያለው፡፡
የሽብር ቡድኑ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ተከፋይ፤ ጉዳይ አስፈፃሚና በወንጀል የሚፈለግ ህገ-ወጥ ሽፍታ መሆኑን ያመላከተው ሰራዊቱ ቡድኑ የኃላፊነትና የተጠያቂነት መንፈስ አይሰማውም፤ በባህሪው ምክንያት ሊሰማውም እንደማይችል አስረድተዋል፡፡
በዚህ ሳቢያም የሽብር ቡድኑ እንደፈለገው የሚዋሽ እና የግፎች ሁሉ ጥግ የሆነ ተግባር በገዛ ወገኑ ላይ የሚፈጽም መሆኑን አንስቷል፡፡
ስለሆነም መከላከያ ሰራዊት ህዝባችንን ከዚህ አሬመኔ ቡድን ቀንበር ለማላቀቅና ከከንቱ ጭፍጨፋ ለማዳን ህዝባችንና ለሀገራችን ይጠቅማል የተባለውን ሁሉ በመስዋዕትነታችን እውን ለማድረግ በከፍተኛ ብቃትና የላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡
ህዝባችን ከፍጅት ለመታደግ ሲባል መሆን የሚገባውን ሁሉ አጠቃላይ ሁኔታን በማያበላሽ አግባብ ቀጣይም ሊኖር እንደሚችል መታወቅ ይኖርበታልም ነው ያለው ፡፡
እኛ ታላቅና ታሪካዊ ኃላፊነት ካለበት የመከላከያ ኃይል በሚጠበቅ አግባብ፣ ሁለተናዊ በሆነና ነገን አሻግሮ በሚመለከት እሳቤ እንዲሁም በወታደራዊ ሳይንስና ጥበብ የምናደርገው እና እናንተ በጋለ ጥልቅ የሀገር ፍቅር ስሜት ዛሬ፣ አሁን፣ እዚችው እዲሆን የምትፈልጉትን ሁሉ "አፍ በእጅ በሚያስይዝ" አስተማማኝና ዘላቂ በሆነ ድል ይታረቃል ሲልም አረጋግጧል፡፡
ዛሬም ሆነ እስከ ወዲያኛው የኢትዮጵያን ክብርና ጥቅም ለመጉዳት የሚደረግ ከሰማይ በታች ያለ ፈተና ሁሉ እንደማንፈተን ታውቃላችሁ! ታምኑናላችሁም! ለኢትዮጵያ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦች፤ ህዝቦች ደህንነት፣ የግዛት አንድነትና ለሀገረ መንግስቱ ቀጣይነት በመቆም የምንከፍለው መስዋእትነት ክብርና ኩራታችን ነው ሲል በመግለጫው መግለጹን ከመከላከያ ሰራዊት ማኅበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
ነሐሴ 22 ቀን 2014 ዓ.ም
ወታደራዊ የሆኑ ዒላማዎችን አነፍንኖ የሚመታ የጦር አውሮፕላን ቴክኖሎጂን ታጥቆ በብቃት የሚጠቀመው አየር ኃይላችን የተሳካ ተልዕኮና የጠላት የሀሰት ድራማ……
አሸባሪው ህወሓት ከዓለም የምግብ ድርጅት የመቀሌ መጋዘን በዘረፈው 570 ሺህ ሊትር/12 ታንከር/ ነዳጅ ምክንያት ከየአቅጣጫው እየደረሰበት ያለውን ውግዘት ለማርገብ የተካነበትን ሌላ የሀሰት ድራማ እየተወነ ነው፡፡
የኢፌዴሪ አየር ኃይል ልምድና ብቃት ባላቸው ፖይለቶቻችን ኢላማን ለይተው በሚመለከቱና በሚመቱ ዘመናዊ ትጥቆቻችን ታግዘው የጠላትን ወታደራዊ ኢላማዎች ማውደም የሚችሉ ናቸው።
አየር ኃይላችን የታጠቃቸው የዘመኑ የረቀቀ ቴክኖሎጂ ትሩፋት የሆኑ ተዋጊ የጦር አውሮፕላኖች የታዘዙትን ብቻ የሚከውኑ ሳይሆኑ ከሰው ልጅ የላቁ እንዲሆኑ በመጠቀ ጥበብ የተሰሩ ስለሆነ ወታደራዊ የሆኑ ዒላማዎችን አነፍንፈው በመለየት ቁልጭ አድርገው በማሳየት የማደባየት አቅም ያላቸው ናቸው፡፡ ስለዚህም ዜሮ ስህተት ይሰኛሉ!
መንግስት ያለአንዳች ቅድሜ ሁኔታ የሰላም እጁን ዘርግቶ እያለ በእብሪት የተወጠረው የሽብር ቡድን አሻፈረኝ ብሎ ዳግም ለ3ኛ ጊዜ ጦርነት ከፍቶብን እያለ እንኳን ለሰላም ባለን ፅኑ አቋም ምክንያት እስካሁን በሙሉ አቅማችን ወደ ጦርነት ሳንገባ በመከላከል ውጊያ ጀግናው አየር ኃይላችን ወደ ጠላት ደጀን በጥልቀት ገብቶ እብሪቱን ለማስተንፈስ የተመረጡ ወታደራዊ አቅሞች ላይ ስኬታማ ተልዕኮ እየፈፀመ ነው፡፡
"ሌባ ላመሉ…" እንዲሉ አሸባሪው ህወሀት የሀገረ ሰው ለእብሪት እብደቱ ማካሄጃ በእሱ መያዣነት በርሃብ እየተለበለቡ ላሉት የትግራይ ህዝብ ወገናችን መድረሻ የሆነውን ነዳጅ በጭካኔ መንጠቁን የተመለከቱ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ውግዘቶችን አቅጣጫ ለማስቀየር ህፃናት በአየር ተደበደበብኝ የሀሰት ውንጀላ ከጦር ሜዳ ያጋዘውን ሬሳ በጥቁር ፌስታል ጠቅልሎ በመቅረጽ፣ ተደበደበ የሚለውን ቦታ የህፃናት መጫወቻ ለማስመሰል የቢራቢሮ ስዕል ስሎ በማሳየት፣ የህፃናት መጫወቻ ቁሳቁስ ሰብስቦ በመናፈሻ በረንዳ በቀላል ፈንጂ አስነሺ ፈረካክሶ የተካነበትን ቅጥፈት እየተወነ ነው፡፡
ሆኖም የሽብር ቡድኑ በአውሮፕላን ተመታ በሚል እያሰራጨ ያለው አጸደ ህፃናት ማስመሰያው የውሸት ድርሰት እና ቀድሞ ለዚሁ የሃሰት ውንጀላ ተዘጋጅቶ የነበረ ነው፡፡ ውሸትና ጦርነትን ህልውና ያደረገው አሸባሪ ቡድን በሀሰት ድርና ማግ የሸመነው ጥቁር ፕሮፖጋንዳ ነው፡፡ ለማንኛውም ዘ-ህወሀታዊ የቅጥፈት ትራጄዲ አልተሳክቶም፡፡
እድሜ ለዘመኑ የረቀቀ ቴክኖሎጂና ለጀግናው አየር ኃይላችን ብቃት ኦ! ዜሮ ስህተት!!
#ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ አኩሪ ተጋድሎ ሁለም አሸናፊ ነች!!
ነሐሴ 22 ቀን 2014 ዓ.ም
ጀግናው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የአንድ መቶ ሃያ ሚሊዮን ህዝብ ኃላፊነት ያለበት ፤ በህገ-መንግስት የተመሠረተ በመንግስት የሚመራ፣ በማንኛውም ጊዜ እና ሁኔታ የሚሰጠውን ትዕዛዝ አክባሪ እና ፈፃሚ ፕሮፌሽናል ብሔራዊ ኃይል ነው።
ሠራዊታችን የኢትዮጵያን የግዛት አንድነትና የዜጎቿን ደህንነት የማረጋገጥ ታላቅና ታሪካዊ ኃላፊነት የተሸከመ ጀግና ነው።
ሠራዊታችን በማንኛውም ጊዜ፣ ቦታና ሁኔታ በመንግስት የሚሰጡ ትዕዛዞችን በህዝባዊነት፣ በጀግንነት እና በፅናት መከፈል የሚገባውን መስዋዕትነት ሁሉ ከፍሎ ተግባራዊ የሚያደርግ የድል ሠራዊት ነው።
አሜሪካ ከቻይና ወደ ሀገሯ የሚደረጉ በረራዎችን አገደች
የበረራ እገዳው ለአንድ ወር ገደማ ይቆያል ተብሏል
አሜሪካ ከቻይና ወደ ሀገሯ የሚደረጉ በረራዎችን ላይ እገዳ መጣሏ ተሰምቷል።
ከዚህ በፊት በንግድ አሁን ደግሞ በታይዋን ጉዳይ መካረር ውስጥ የገቡት አሜሪካ እና ቻይና ሌላ ውዝግብ ውስጥ ገብተዋል።
ቻይና በኮሮና ቫይረስ ምክንያት በተወሰኑ የአሜሪካ አየር መንገዶች ላይ የጉዞ እገዳዎች አስተላልፋ ነበር። አሜሪካም ለዚህ እገዳ የአጸፋ እርምጃ የወሰደች ሲሆን 26 በረራዎች ከቻይና ወደ አሜሪካ እንዳይደረጉ እገዳ ጥላለች።
እገዳ ከተጣለባቸው አየር መንገዶች መካከልም ሺያሜን፣ ኤየር ቻይና፣ ሳውዘርን ቻይና እና ቻይና ኢስተርን ዋነኞቹ ናቸው ሲል ቪኦኤ ዘግቧል።
ሰባቱ በረራዎች ከቻይና ወደ ኒዮርክ፣ 19ኙ በረራዎች ደግሞ ወደ ሎስ አንጀለስ ሊደረጉ ታስበው እንደነበርም ተጠቅሷል።
ቻይና ከአንድ ወር በፊት የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በሚል በአሜሪካዊያኖቹ ዴልታ እና ዩናይትድ አየር መንገዶች ላይ 26 በረራዎችን እንዳያደርጉ እገዳ ጥላ ነበር።
'ቻይና በአሜሪካ አየር መንገዶች ላይ እገዳውን ያስተላለፈችው ከአሜሪካ ወደ ሀገሯ ከገቡ መንገደኞች ውስጥ አራት በመቶ ያህሉ ኮሮና ቫይረሱ ስለተገኘባቸው ነበር።
የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ታይዋንን መጎብኘታቸውን ተከትሎ የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት በከፋ ደረጃ ላይ ይገኛል።
የወቅታዊ ሁኔታ መረጃ !!
አሸባሪው ሕወሐት በአንድ በኩል የተለመደውን የሰው ኃይል ማዕበልን በመጠቀም የቆቦ ከተማ ከውጭ በብዙ አቅጣጫ እያጠቃ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ በከተማ ውስጥ ሠርጎ ገቦችን በማሥረግ የሕዝቡን ደኅንነት አደጋ ውስጥ በሚያስገባ መልኩ የከተማ ውስጥ ውጊያ ለማድረግ የሚያስችል ሁኔታ እየፈጠረ ይገኛል።
የሕዝብን ከፍተኛ ፍጅት ለማስወገድ ሲባል የመከላከያ ኃይል የቆቦ ከተማን በመልቀቅ እና ወደ ኋላ መጥቶ ለመከላከል የሚስችለውን ወታደራዊ ይዞታዎችን ለመያዝ ተገዷል።
አሸባሪው ኃይል የትግራይን ወጣት እየማገደ በሕዝብ ማዕበል ማጥቃቱን ካላቆመ መከላከያ ሕጋዊ ፣ ሞራላዊና ታሪካዊ ግዴታውን ለመወጣት የሚገደድ ይሆናል።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት፤
ነሃሴ 21 ቀን 2014 ዓም አዲስ አበባ
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
ነሐሴ 21 ቀን 2014 ዓ.ም
"ጠላትን አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ለትውልድ የሚተላለፍ ታሪክ መስራታችንን እንቀጥላለን።" ፦ ሌ/ጀኔራል ይልማ መርዳሳ
በኢፌዴሪ አየር ኃይል የሰራዊት ቤተሰብ ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል።
የሰራዊት አባላትና ቤተሰቦቻቸው በጋራ በመሆን የአየር ኃይልን የዝግጁነት አቅምና በተቋሙ ውስጥ እየተሰሩ የሚገኙ መሰረተ ልማቶችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የኢፌዲሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጀኔራል ይልማ መርዳሳ እንደተናገሩት ወታደር የቤተሰብ ድጋፍ ሲኖር ይጀግናል፣ ለድልም ይበቃል፣ ለቀጣይ ግዳጅም መነሳሳትን ይፈጥራል።
አየር ኃይላችንም ላስመዘገበው ውጤታማ የግዳጅ አፈፃፀም ስኬት የእናንተ የቤተሰቦቻችን ድርሻ የላቀ በመሆኑ ልትኮሩም ፤ ልትመሰገኑም ይገባችኋል ብለዋል።
ዋና አዛዡ አክለውም እኛ የአየር ኃይል አባላቶች ጠላትን አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ለትውልድ የሚተላለፍ ታሪክ መስራታችንን እንቀጥላለን ብለዋል።
በቀጣይም የሰራዊቱንና የቤተሰቦቹን ኑሮ ለመደጎም በትኩረት እንደሚሰራ የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌ/ጀኔራል ይልማ መርዳሳ ተናግረዋል።
ከሰራዊት ቤተሰቦች መካከል አንዳንዶች በሰጡት አስተያየት የኢትዮጵያን ጠላቶች ድባቅ በመምታት ለህዝባችን አኩሪ ድል እያበሰረ የሚገኘው አየር ኃይል የእኛ ቤተሰቦች የሚሰሩበት ተቋም በመሆኑ ደስተኞች ነን።
አየር ኃይልን መጎብኘት በመቻላችን ኩራት እንደተሰማቸው የገለፁት ቤተሠቦች ከሰራዊቱ ጎን በመቆም የሚጠበቅባቸውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል።
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
ነሐሴ 21 ቀን 2014 ዓ.ም
አሸባሪው ህወሓት በሞት አፋፍ ላይ ካሉ ትግራዋይ ጉሮሮ ንጥቂያ እስከ ኢትዮጵያን ማራቆት ፈፅሟል!
ከሰሞኑ የሽብር ቡድኑ ህወሓት በመቀሌ ከተማ ውስጥ የሚገኘውን የዓለም የምግብ ድርጅት መጋዘን በኃይል ሰብሮ በመግባት ነዳጅ እና ሌሎች ለሰብዓዊ ድጋፍ አገልግሎት የሚውሉ ቁሳቁሶችን መዝረፉ ዓለም አቀፉን ማሕበረሰብ እያነጋገረ ይገኛል፡፡ ምንም እንኳን ድርጊቱ የዓለም አቀፉን ማሕበረሰብ ቀልብ የሳበ እና ያሳዘነ ድርጊት ቢሆንም መሰል ድርጊቶች ህወሐት ጥርሱን የነቀለበትና አድጎ ያረጀበት ባህሪው ነው፡፡
ወቅቱ 1970ዎቹ አጋማሽ ነው፡፡ የሰሜኑ ኢትዮጵያ በተለይም የትግራይ እና አዋሳኝ አካባቢዎች ህዝብ ህወሀትን እና ድርቅን ጥሎባቸው የከፋ የርሃብ ቸነፈር ተከስቶ እየረገፉ ነበር፡፡ እናቶች የልጆቻቸውን የርሃብ ጣር ውጭ ነፍስ ግቢ ትንቅንቅ መመልከት ተስኗቸው ቀድመው ወድቀዋል፡፡ ሕይወታቸው ያለፉ እናቶችን ጡት እንደጎረሱ ተዘቅዝቀው ሞታቸውን የሚጠባበቁ፤ መናገር እና ማልቀስ የተሳናቸው ህጻናት ቁጥር ቀላል የሚባል አልነበረም፡፡ ክስተቱን ለመስማት እና ለማየት እድል ያገኙ ሁሉ ልባቸው ተሰብሯል፡፡
የዓለም ማህበረሰብ በወቅቱ ተደጋጋሚ ጦርነት እና ድርቅ ተባብረው በሰሜን ኢትዮጵያ በፈጠሩት የርሃብ አደጋ ልባቸው ክፉኛ ተነክቷል፡፡ እንደ ቦብ ጌልዶፍ ያሉ ከያንያን የተለያዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ሁነቶችን እየፈጠሩ በርሃብ አደጋ ለተጠቁ ወገኖች ገቢ የሚያሰባስቡ በጎ አድራጊዎች ከዚህም ከዚያም ቢራወጡም የተፈለገው ድጋፍ ግን ለተባለለት ዓላማ በተገቢው መንገድ መድረስ አልቻለም፡፡
ለነፍስ አድኑ ርብርቡ ዋና እንቅፋት ደግሞ ህወሓት ነበር፡፡ መንገድ እየዘጋ፣ ለድጋፍ የሚሄዱ ተሽከርካሪዎችን እየዘረፈ እና እያጠቃ፤ እንደምንም የደረሰውን ድጋፍም በድብቅ እየከዘነ ለተቸገሩት እንዳይደርስ አደረገ፡፡ ትግራይ ውስጥ በርሃብ አለንጋ የሚቀጣው ሕዝብ በየጎዳናው ወድቆ የተላከ የእርዳታ ቁሳቁስ ግን ሱዳን ውስጥ በሱዳናዊ ደላሎች አማካኝነት በግልጽ ይቸበችቡ ነበር፡፡ ይህ አስነዋሪ እና አሳፋሪ ድርጊት በአሜሪካው የስለላ ድርጅት (ሲ አይ ኤ) እና መሰል ድርጅቶች ዘግይቶም ቢሆን ቢጋለጥም ቅሌት ለህወሐት ብርቁ አልነበረምና አልደነቀውም፡፡
ህወሐት በሱዳን ድንበር አካባቢ እንቅስቃሴ እንዲያደርግ ሕቡዕ ተልዕኮ የተሰጠው እና ማሌሊት በሚል መጠሪያ የተቋቋመው ቡድን ዋና ተግባራትም በርሃብ አለንጋ የሚቀጡ የኢትዮጵያ ትግራይ ዜጎቻችን ወደ ሱዳን ማስወጣት እና በስማቸው የሚሰጡትን የእርዳታ ቁታቁስ ሽጦ የጦር መሳሪያ መግዛት ነበር፡፡ በዚህም እርዳታ ድርጅቶች ለትግራይ ህዝብ ርሃብ ማስታገሻ የዕለት ደራሽ እህል መግዣ ከውጭ የመጣውን 100 ሚሊዮን ዶላር ወደ ህወሀት ካዝና እንዲገባ አድርጓል፡፡
ህወሐት ከወታደራዊ መንግስት ደርግ ጋር በነበረው ጦርነት የመሳሪያ ችግር እንዳይኖርበት ካደረጉት መንገዶች አንዱ ይህው የእርዳታ ምግብን ሽጦ የጦር መሳሪያ የመግዛት አስነዋሪ ስትራቴጂው ነበር፡፡ በወቅቱ በአይነትና በገንዘብ ከውጪ ረጅዎች በድርቅ ለተጎሳቆለው የትግራይ ህዝብ የሚላከውን ከ95% (ከዘጠና አምስት ፐርሰንት በላዩን) በሞት አፋፍ ላይ ካሉ ትግራዋይ ጎሮሮ ነጥቆ ለጦር መሳሪያ ግዥ አውሎታል፡፡
በጦርነቱ ሕይዎታቸውን ካጡት የትግራይ ልጆች ባልተናነሰ መልኩ በህወሐት ሴራ በርሃብ ተቀጥቶ የረገፈው የትግራይ ህዝብ በርካታ ነበር፡፡ በዚህ መልኩ ወደ ስልጣን የመጣው ህወሐት ሀገር የመምራት እድል አግኝቶም “ሌባ ላመሉ ዳቦ ይልሳል” እንዲሉ የኢትዮጵያን ሀብትና ንብረት ከመስረቅ እና ከመልከስከስ የቦዘነበት ወቅት እንዳልነበር ለኢትዮጵያዊያን ድብቅ አይደለም፡፡ ሠራዊታችንም በግልፅ የሚያውቀው እውነታ ነው፡፡ የህወሓት ባለስልጣናት በዘመናቸው ሀገር እየመሩ ባሉበት ወቅት መርከብ ሰርቀው በመሸጥ ኪሳቸውን አደልበዋል፡፡
ህወሀት ሕዝብ እያሥተዳደረ በቱባ ባለስልጣኖቹ አማካኝነት መሬት ዘርፏል፡፡ በእርዳታ እና በብድር ስም ከውጭ የሚመጣ ድጋፍ ከሹማምንቶቹ መቀራመት በኋላ አየር ባየር ተመልሶ ማረፊያው ከአበዳሪዎቹ ኪስ እና ካዝና ውስጥ ነበር፡፡ በህወሐት ዘመን የሚኒስተሮቹ ተቀዳሚ ተግባር ድለላ እና ኮሚሽን ማሰባሰብ ነው ብለው የሚተቹት በርካቶች ነበሩ፡፡ ታዲያ ከሰሞኑ መቀሌ ውስጥ የሚገኘውን የዓለም ምግብ ድርጅት መጋዘን ሰብሮ በመግባት ነዳጅ እና ሌሎች የሰብዓዊ ድጋፍ ቁሳቁሶችን መዝረፉ ዓለምን ስለምን እንደ አዲስ አነጋገረ ብሎ የሚጠይቅ አይጠፋ ይሆናል፡፡
የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ሳማንታ ፓዎር ትናንት በትዊተር ገጻቸው ባጋሩት መልዕክት ህወሐት በመቀሌ የሚገኘውን የዓለም ምግብ ድርጅት 570 ሺህ ሊትር ነዳጅ መዝረፉ አሳፋሪ እና የሚወገዝ ነው ብለውታል፡፡
የሰብዓዊ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች አገልግሎት የሚውል 150 ሺህ ጋሎን ነዳጅ መዝረፍ በትግራይ ንጹሃን ላይ በጭካኔ መፍረድ ነው ብለውታል፡፡ ምንም እንኳን ዳይሬክተሯ በህወሐት ዘረፋ ልቤ ተነክቷል ቢሉም ትግራዋያን ግን ይህንን ከተላመዱት ከስድስት አስርት ዓመታት በላይ ተቆጥሯል፡፡
ስለሆነም የተከበርከው የትግራይ ህዝብ ወገናችን ሆይ ኧረ ሰቆቃው፣ ከምትወዳት ኢትዮጵያ ሀገርህና እህትና ወንድም ከሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በደም ተቃብትህ መራራቅህ ይቅር በቃኝ! አሸባሪውን ህወሓትንም በቃህ በለው! ምክር ዝክርህን ካልሰማ የቻልከውን ሁሉ አድርገህ ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ተላላኪ የሆነውን አሸባሪ ከጫንቃህ ላይ አሽቀንጥረህ በመጣል ኢትዮጵያዊ አንድነትህን አስከብር፤ መላው የኢትዮጵያ ህዝብንና ጀግናው ሠራዊታችን ከጎንህ ነን፡፡
ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ አኩር ተጋድሎ ታሸንፋለች!!
ሩሲያ እና ህንድ በዶላርን በመተው በራሳቸው ገንዘብ ለመገበያየት ተስማመሉ
የሩሲያ፣ ቻይና፣ ህንድ፣ ብራዚል እና ደቡብ አፍሪካ ህብረት የሆነው ብሪክስ ፕሬዝዳንት ፑርኒማ አናንድ እንደገለጹት በአባል ሀገራቱ መካከል የዶላር ግብይት አያስፈልግም ብለዋል።
እንደ ሩሲያ ቱዴይ ዘገባ ከሆነ ሩሲያ እና ህንድ ለሚያደርጓቸው የእርስ በርስ ንግድ ልውውጥ ሩብል እና ሩፒን ለመጠቀም መስማማታቸውን ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል።
ሁለቱ ሀገራት ከዚህ ውሳኔ ላይ የደረሱት ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ጦርነት መክፈቷን ተከትሎ በአሜሪካ እና አውሮፓ ህብረት ማዕቀብ በመጣሉ ነው።
ቻይና የእስራኤልና ፍልስጤም ግጭት እልባት እንዲያገኝ ጠየቀች፡፡
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የቻይና ቋሚ ተወካይ ዣንግ ጁን ሃዉስ፣ አለም አቀፉ ማህበረሰብ የእስራኤልና የፍልስጤም ግጭት እልባት እንዲያገኝ ተጨባጭ እርምጃዎችን ሊወስድ ይገባል ብለዋል፡፡
ዣንግ ግጭቱን ለመፍታት ቀዳሚዉ ጉዳይ ሁለቱም ወገኖች በዲፕማሲያዊ አቅጣጫዎች የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲያከብሩ፣እንዲረጋጉ እና እነዚህ ጥረቶች እንዲቀጥሉ ማድረግ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶች ወደ ጋዛ እንዲገቡ እና በተቻለ ፍጥነት በእስራኤል የጋዛ እገዳ ሙሉ በሙሉ እንዲቆምም ማሳሰባቸዉን ሲጂ ቲኤን አስነብቧል፡፡
ፍልስጤም አሁን የተወረረችበት ግዛት ዘላቂ እንደማይሆንና አለም አቀፉ ማህበረሰብ ጉዳዩን ትኩረት ሰጥቶት የጉዳዩን መነሻ ሊጋፈጥ ይገባዋል፤ በሁለቱ አገራት መካከል ያለዉ አሉታዊ ግንኙነት እንዲስተካከልም የሁለት ሀገራት የጋራ መፍትሄ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡
የፍልስጤማዉያን የማይገረሰሱ መብቶች ወደቦታቸዉ ከተመለሱ በእስራኤልና ፍልስጤም መካከል ያለዉን የተቀናጀ አብሮመኖርና ሰላም መመለስ እንደሚቻል አንስተዋል፡፡
አሜሪካን ያሰጋውና ለሁለተኛ ቀን የቀጠለው የኢራን የድሮኖች ልምምድ
ቴህራን ለሞስኮ ልታግዝ ትችላለች በሚል አሜሪካን ስጋት ውስጥ የከተተው የኢራን የድሮኖች ልምምድ አሁንም እንደቀጠለ ነው፡፡
በልምምዱ የተለያዩ አይነት ሰው አልባ አውሮፕላኖች በበረሃማ ስፍራዎች ቦምቦችን ሲጥሉ የሚያሳዩ ምስሎችም ይታያሉ፡፡
ልምምዱ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን 150 ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ያሳተፈ ፣ የኢራንን የባህረ ሰላጤ ጠረፍ እና አብዛኛውን ግዛቷን የሚሸፍን እንደሆነም ነው የተዘገበው።
https://www.youtube.com/watch?v=FQfU_SX0Vvg
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
