ar
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

الذهاب إلى القناة على Telegram

Addis abeba Ethiopia

إظهار المزيد
5 756
المشتركون
-27824 ساعات
-2 5467 أيام
-1 99730 أيام
أرشيف المشاركات
ዩክሬን 40 የሩሲያ ቦምበሮችን አወደመች 📌ዩክሬይን ይህን ኦፕሬሽን ለማዘጋጀት አንድ አመት ከስድት ወር ከዘጠኝ ቀን ተዘጋጅታለች። ዝግጅቷን ያደረገቺው ደግሞ ከዚያው ሩሲያ ውስጥ ነው። 📌 ዩክሬይን ይህንን ዝግጅት ስታደርግ ምስጢር እንዳይወጣ ለማድረግ ለየትኛውም አጋሮቿ አላሳወቀችም። 📌ድሮኖቹን የማምረት የመገጣጠም እና ለጥቃት የማዘጋጀት ስራ ሲሰራ የነበረው ከሩሲያ ጦር ማዘዣዎች አካባቢ ነው። 📌 ድሮኖቹ ለጥቃት ተዘጋጅተው እንዳለቁ ያንን ሲያዘጋጁ የነበሩ ዩክሬይናዊያን ሩሲያን ለቀው ወደ ዩክሬይን ተመለሱ። 📌ከዚያ ድሮኖቹን የያዙ ኮንቴይነር መኪኖች ወደ ዘጠኝ የሩሲያ ግዛቶች ተሰማሩ። 📌 ከዚያ በዘጠኙም የአየር ማረፊያዎች ውስጥ ያሉ 40 ስትራቴጂክ ቦምበሮችን በሪሞት ኮንትሮል እንዳልነበሩ አደረጓቸው። ድሮኖቹ AI ተገጥሞላቸው ስለነበር ኢላማቸውን በራሳቸው ያሳኩ ነበር። 📌በየጦር ጣቢያው ከተቀመጠው የሩሲያ ሚሳኤሎች ውስጥ 34%ቱ ወደሙ። ሩሲያ 140 ቦምበሮች የነበሯት ቢሆንም አሁን የቀሯት 100 ብቻ ሆነዋል። 📌ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዜሌንስኪ ክስተቱን በታሪክ ተፅፎ ይቀመጣል ሲል በጀብዱ ተሞልቶ ገልፆታል። ሩሲያ ጦርነቱን ካላቆመች ገና የምትከፍለው ዋጋ ውድ ነውም ብሏል። 📌ራሺያ በዚህ ጥቃት ብቻ በግምት ከ2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ከስራለች ተብሏል። ራሺያ ለአፀፋዊ ምላሹ ከላይ በምስል የሚታየውን Oreshnik RS26 የተባለውን ስትራቴጂክ ሚሳኤል ልትጠቀም እንደምትችል እየተነገረ ነው። 📌ይህ ሚሳይል የመታበትን ኢላማ በ 4000 ዲግሪ ሴልሺየስ ሙቀት የሚቃጥል አደገኛ መሳሪያ ነው። 📹 #BREAKING 📹📹 https://www.youtube.com/@habeshamedianetwork6156 Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለቢልጌትስ የክብር ሽልማት አበረከቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ምሽት በብሔራዊ ቤተመንግሥት በተካሄደ ሥነሥርዓት የኢትዮጵያን ታላቁን የክብ
+4
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለቢልጌትስ የክብር ሽልማት አበረከቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ምሽት በብሔራዊ ቤተመንግሥት በተካሄደ ሥነሥርዓት የኢትዮጵያን ታላቁን የክብር ኒሻን ለቢል ጌትስ ሸልመዋል። ይኽ የከበረ ሽልማት የጌትስ ፋውንዴሽን ባለፉት 25 አመታት በኢትዮጵያ ላበረከታቸው አሻጋሪ ሥራዎች እና ታላላቅ ዘመን ተሻጋሪ በጎ ተፅዕኖዎችን ያከበረ ነዉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በንግግራቸው ለቢል ጌትስ ፋውንዴሽን የ25 አመታት አሸጋጋሪ ሥራዎችን ምስጋና አቅርበዋል። ቢል ጌትስ ከቴክኖሎጂ ፈር ቀዳጅነት ወደ በጎ አድራጊነት ያደረጉትን ጉዞ በማውሳትም  ዝቅ ብሎ በማገልገል፣ በአክብሮት እና በእኩልነት እምነት ላይ የተመሠረተውን አገልግሎታቸውን አድንቀዋል። ፋውንዴሽኑ በጤና፣ ግብርና፣ ዲጂታል መታወቂያ የሚያደርገው ጥረት ብሎም ጠንካራው በመከባበር ላይ የተመሠረተ ትብብር በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተወስቷል።

ኢትዮጵያ 2ኛ ወጣች!🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹👌 ኢትዮጵያ በሕንድ ሃይድራባድ በተዘጋጀው አለም አቀፍ የቁንጅና ውድድር 2ኛ ወጣች። 130 ሃገራት በተሳተፉበት 72ኛው አለም አቀፍ የቁንጅና ውድድር
+1
ኢትዮጵያ 2ኛ ወጣች!🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹👌 ኢትዮጵያ በሕንድ ሃይድራባድ በተዘጋጀው አለም አቀፍ የቁንጅና ውድድር 2ኛ ወጣች። 130 ሃገራት በተሳተፉበት 72ኛው አለም አቀፍ የቁንጅና ውድድር ታይላንድ 1ኛ ሆናለች። በሜካኒካል ኢንጂነሪንግ ሁለተኛ አመት የአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ተማሪዋ ሞዴል ሃሴት ደረጀ የ2ኛ ደረጃን አግኝታሌች ‹‹ሚስ ኢትዮጵያ›› ከአፍሪካ 1ኛ ወጣች፡፡

ሀገርና ህዝብ የሚመካበት ዘመናዊ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ተገንብቷል ኢንጂነር አይሻ መሐመድ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 23 ቀን 2017 ዓ.ም ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታጠቀ ሀገርና ህዝብ የሚመካ
ሀገርና ህዝብ የሚመካበት ዘመናዊ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ተገንብቷል      ኢንጂነር አይሻ መሐመድ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 23 ቀን 2017 ዓ.ም ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታጠቀ ሀገርና ህዝብ የሚመካበት ጠንካራ የመከላከያ ሠራዊት መገንባቱን የመከላከያ ማኒስቴር ሚኒስትር ኢንጂነር  አይሻ መሐመድ  ገለጹ። ሚኒስትሯ በመከላከያ ሠራዊት የተከናወኑ ተግባራትን፣ የተገኙ ስኬቶችንና ቀጣይ ተልዕኮዎችን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ከሀገራዊ ለውጡ ማግስት መከላከያ ሠራዊትን ጨምሮ በፀጥታና ደህንነት ተቋማት ስኬታማ ሪፎርም መደረጉን አንስተው፤ ውትድርና ጀግኖች የሚመርጡት ለሀገር ሉዓላዊ አንድነት ዋጋ የሚከፈልበት የተከበረ ሙያ መሆኑን ተናግረዋል። በዘመናዊ ቴክኖሎጂና በሥነ-ምግባር የታነጸ ሀገርና ህዝብ የሚመካበት ፕሮፌሽናል የሀገር መከላከያ ሠራዊት መገንባቱንም አንስተዋል። የዓለም አቀፍ የጦርነት ስልቶች መለወጣቸውን የጠቀሱት ሚኒስትሯ፤ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትንም ዘመናዊ ትጥቅን በማሟላት የሀገርን ተጋላጭነት ማስቀረት የሚችል አስተማማኝ ኃይል ማድረግ ተችሏል ብለዋል። ሠራዊቱ በህበረብሔራዊ አንድነት የተዋቀረና ለሀገር ሉዓላዊነት ዘብ የቆመ የመጨረሻው ጠንካራ ምሽግ መሆኑን አብራርተዋል። ባለፉት ዓመታት በነበሩ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ መልከ ብዙ ግዳጆችን በብቃት በመወጣት በአደረጃጀት፣ በትጥቅ፣ በአስተሳስብና ስልጠና ነጥሮ የወጣ ዘመናዊ ሠራዊት ሆኗልም ነው ያሉት። በኢትዮጵያ ላይ ከየትኛውም አቅጣጫ የሚቃጣ ጥቃትን ከሩቅ የሚያስቀርና የሚመክት የምድር ኃይል፣ የአየር ኃይል፣ የሜካናይዝድ፣ የባሕር ኃይል፣ የልዩ ዘመቻ እና የሳይበር ኃይል መገንባቱን አንስተዋል። ሠራዊቱ ህገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለማፍረስ የሚሞክሩ አካላት ላይ የማያዳግም እርምጃ በመውሰድ የሀገርን ሰላምና ደኅንነት ማፅናቱንም ገልጸዋል። በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሰላም ችግር የሚፈጥሩ የታጠቁ አካላት ላይ እርምጃ በመውሰድና በሰላማዊ መንገድ እጃቸውን እንዲሰጡ በማድረግ የዜጎችን ሰላም እያስጠበቀ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የጽንፈኞችና የሽብር ቡድኖችን የስጋት አቅም በማክሰም ስኬታማ የህግ ማስከበር ስራ መሰራቱንም ሚኒስትሯ ማብራራታቸውን ኢዜአ ዘግቧል። ሠራዊቱ ከሌሎች የጸጥታ ተቋማት ጋር በመተባበር በሰዎች እና በሸቀጦች እንቅስቃሴ ላይ መስተጓጎል በሚፈጥሩ ጥቂት የጥፋት ኃይሎች ላይ ቀጣይነት ያለው እርምጃ  በመውሰድ ሰላማዊ የትራንስፖርት ፍሰት እንዲኖር በማድረግ ላይ መሆኑንም ገልጸዋል። ለህዝብ ሰላምና ለሀገር ሉዓላዊ አንድነት የህይወት መስዋዕትነት የሚከፍለውን ሰራዊት በማህበራዊ ሚዲያ በሀሰት ስሙን የሚያጠፉ አካላት መኖራቸውን በማንሳት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስበዋል። ኢትዮጵያ የጀመረችው ሁለንተናዊ የዕድገት ጉዞ እንዳይሳካ የሚፈልጉ ታሪካዊ ጠላቶቿ ከውስጥ ባንዳዎች ጋር ጥምረት በመፍጠር እየሰሩ መሆኑንም አንስተዋል። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/

#viral | ቻይና 'ሃይ ስካይ' ብላ የሰየመችውን ሰው አልባ አውሮፕላኖች ተሸካሚ ይፋ ልታደርግ ነው የመጀመሪያዋ የቻይና የድሮን ተሸካሚ ጂዩቲያን ኤስኤስ-ዩኤቪ በሰኔ ወር እንድትበር ፕሮግራም ወጥቶላታል። ጂዩቲያን እስከ 15 ሺህ ሜትር ከፍታ ላይ መብረር እና 1 ሺህ ኪሎ ግራም የሚሳኤል መሳሪያዎችን ወይም ከ100 በላይ ትናንሽ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መሸከም ትችላለች። 7 ሺህ ኪሎ ሜትር የማካለል አቅም አላት። የበረራውን የ3-ዲ ሲሙሌሽን ይመልከቱ https://youtube.com/shorts/dt1Iz9xzJi0?si=GjDqRTN0TCby9zA9

ትራዎሬ ከሩስያ ተመልሶ፤ ዋጋዶጉ የገባ ዕለት በርካታ ሺህዎች አደባባይ በመውጣት የእንኳን ደህና መጣህ አቀባበል አድርገውለታል። በዕለቱ ግን በርካቶችን ያስደነገጠና የቡርኪናውያንን ልብ የሰበረ ክስተ
ትራዎሬ ከሩስያ ተመልሶ፤ ዋጋዶጉ የገባ ዕለት በርካታ ሺህዎች አደባባይ በመውጣት የእንኳን ደህና መጣህ አቀባበል አድርገውለታል። በዕለቱ ግን በርካቶችን ያስደነገጠና የቡርኪናውያንን ልብ የሰበረ ክስተት ተከስቷል። ድንገተኛው ጥቃት እንዴትና በነማን ተፈጸመ ?የሞት ሽረት ትንቅንቅ ያደረጉት የቡርኪናቤ ሰራዊት አባላት መጨረሻስ? ዋጋዱጉን ያመሰውና የምዕራባውያኑ ሚዲያዎች እልል በቅምጤ የሆነላቸው የትራዎሬን መግባት ተከትሎ የተፈጠረው ትክክለኛው ነገር ምን ነበር? #በተከታዩ_ሊንክ_ይመልከቱት 👇👇 https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos

🇷🇺🇪🇹 ሩሲያ የአጋሮቿን የዲጂታል ሉዓላዊነት ለማጠናከር ቁርጠኝነቷን ገለፀች የሩሲያ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት የዓለም አቀፍ የመረጃ ደህንነት ጉዳዮች ልዩ ተወካይ አርተር ሉክማኖቭ ከኢትዮጵያ የመረ
🇷🇺🇪🇹 ሩሲያ የአጋሮቿን የዲጂታል ሉዓላዊነት ለማጠናከር ቁርጠኝነቷን ገለፀች የሩሲያ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት የዓለም አቀፍ የመረጃ ደህንነት ጉዳዮች ልዩ ተወካይ አርተር ሉክማኖቭ ከኢትዮጵያ የመረጃ መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሐሚድ ጋር ከኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 ግን ለጎን ውይይት አካሂደዋል። ሁለቱ ባለሥልጣናት በውይይታቸው ባደጉ እና እያደጉ ባሉ ሀገራት መካከል ያለውን የቴክኖሎጂ ክፍተት ለማጥበብ በጋራ መሥራት እንደሚገባ አንስተዋል። 👉 ሉክማኖቭ ሩሲያ የእውቀት ልውውጥ እና የቴክኒክ ትብብር በማድረግ አጋር ሀገራት የዲጂታል ሉዓላዊነታቸውን እና የመረጃ ደህንነት አቅማቸውን እንዲያዳብሩ ለመደገፍ ቁርጠኛ ነች ብለዋል። #Ethiopia #BREAKING 📹📹 https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command https://t.me/Commando_And_Airborne_Command

#አሰብ_የኢትዮጵያ_ነው! 🇪🇹 አሰብ ምኞት አይደለም፤ ተጨባጭ እውነት ነው፤ የኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ማንነት ነው፤ ቱባ ታሪክ ነው። ፖለቲካዊ ክንድ ነው፤ ኢኮኖሚያዊ አቅም ነው። አመክንዮአዊ (log
#አሰብ_የኢትዮጵያ_ነው! 🇪🇹 አሰብ ምኞት አይደለም፤ ተጨባጭ እውነት ነው፤ የኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ማንነት ነው፤ ቱባ ታሪክ ነው። ፖለቲካዊ ክንድ ነው፤ ኢኮኖሚያዊ አቅም ነው። አመክንዮአዊ (logical) ጥያቄ ነው፤ ዓለም የሚደግፈው ጥያቄ ነው። ኢትዮጵያዊ ነኝ፤ አሰብም የኢትዮጵያ ነው፤ አሰብ የቀደምት አያቶቻችንና አባቶቻችን ታሪክ አካል ነው፤ የእኔም ነው! ስለአሰብ ደጋግሜ የምጽፈው የኢትዮጵያ ሀቅ ስለሆነ ነው፤ የሚገባን ውርስና ንብረታችን በመሆኑ ነው፤ እዳ ስላለብን ነው፤ ያለአሰብ የተሟላ ህልውናና ብልጽግና ስለማይኖረን ነው። የባለቤትነት መብታችን፣ ሀቃችን፣ ነፃነታችን እና ንብረታችንም አካል በመሆኑ ነው። . . . . . . የኢትዮጵያዊነት ማንነታችን በታሪክ፣ በባህል እና በጋራ ትግል የተገነባ ነው። የዚህ ግንባታ ድንበሩም በሩም አሰብ ነው፤ የስትራቴጂክ ሉዓላዊነት እና ነፃነት ዓርማ ነው። የአገርና የህዝብ ታሪካዊ፣ ባህላዊ እና ጂኦፖለቲካዊ ቅርስና ውርስ ነው። አሰብ ማንም በሸፍጥ ሊቀማንና ሊወስድብን የማይገባ፣ ማንም ከታሪክ ሊሰርዘው የማይችል. . . ወደባችን ነው። ዓለም አቀፍ፣ ቀጣናዊ እና ክልላዊ ጫናዎች የማይበግሩትና የማያስቀሩት ዳር ድንበር ነው። . . . በጉንደት፣ በጉራዕ፣ በኩፊት፣ በዶጋሊ፣ በዓድዋ . . . ጠላትን በማርበድበድ የሚታወቁት ቆራጥ፣ ታማኝ፣ ጀግና፣ የጦር መሪና ተዋጊ አሉላ አባነጋ፦ "#ራሱ_ቀይ_ባህር_የኢትዮጵያ_የተፈጥሮ_ወሰን_ሆኖ_ኖሯል፤ ይኖራልም!” ማለታቸውም #ቃል ነው። ለዛሬው ትውልድ የተላለፈ፣ በወርቅ ቀለም የታተመ ነጎድጓዳማ ቃል ነው። በኢትዮጵያዊ ማንነት፣ ሉዓላዊነት እና ባለቤትነት ላይ የተዋቀረ ዘመን አይሽሬ ቃል ነው። ቃሉም የትውልድ አደራ ነው፤ አደራም እዳ ነው፤ ይህ የእኔ ትውልድ ከነወለዱ የሚከፍለው እዳ ነው። ይህ ትውልድ እዳውን ከነወለዱ የሚከፍለው አሰብን ተረክቦና ጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ ሲያወርስ ብቻና ብቻ ነው። Via Betty Gullele

Update "ከፑቲን ጋር ሐሙስ በቱርክ ለመገናኘት ዝግጁ ነኝ" ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ከሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በቱርክ ኢስታንቡል ተገናኝተው ለመ
+1
Update "ከፑቲን ጋር ሐሙስ በቱርክ ለመገናኘት ዝግጁ ነኝ"  ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ከሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በቱርክ ኢስታንቡል ተገናኝተው ለመነጋገር ፈቃደኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። ፕሬዝዳንቱ በኤክስ ገጻቸው ሩስያ ለቀጥታ የሰላም ንግግሮች ያቀረበችውን ሀሳብ በደስታ በመቀበል ነገር ግን ድርድር ከመጀመሩ በፊት የተኩስ አቁም መኖር እንዳለበት አሳስበዋል። የሩስያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የቀጥታ ውይይት ለመጀመር ያቀረቡትን ጥሪ በጎ ምልክት መሆኑንም ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ጠቅሰዋል። ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ሐሙስ ዕለት በቱርክ ኢስታንቡል ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲንን እጠብቃለሁ ብለዋል። መላው ዓለም ይህን ለረጅም ጊዜ ሲጠብቀው ቆይቷል ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ ሆኖም ግን ማንኛውንም ግጭት ለማስቆም የመጀመሪያው እርምጃ መሆን ያለበት የተኩስ አቁም ስምምነት ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡(ቢታንያ ሲሳይ) #Ethiopia #BREAKING 📹📹 https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command https://t.me/Commando_And_Airborne_Command

የሩሲያ ፕሬዘዳንት ቭላድሚር ፑቲን የቡርኪናፋሶን ሰራዊት ለማሰልጠን ቃል ገቡ !! በ2023 በሁለቱ ሀገራት በጋራ ለመስራት በገቡት በወታደራዊ በንግድ በኢንቨስትመንት አብረዉ ለመስራት ስምምነት መሰረ
+3
የሩሲያ ፕሬዘዳንት ቭላድሚር ፑቲን የቡርኪናፋሶን ሰራዊት ለማሰልጠን ቃል ገቡ !! በ2023 በሁለቱ ሀገራት በጋራ ለመስራት በገቡት በወታደራዊ በንግድ በኢንቨስትመንት አብረዉ ለመስራት ስምምነት መሰረት ለሩሲያ የድል በዓል በሞስኮ የሚገኙት የቡርኪናፋሶ ፕሬዘዳንት ኢብራሂም ትራኦሬ አማካኝነት 50,000 የቡርኪናፋሶ ወታደሮችን እንዲያሰለጡኑላቸዉ የቀረበላቸውን ጥያቄ መቀበላቸው ተገልጿል ። በዚህ ከዘመኑ ጋር የዘመነ ስልጠና ሩሲያ የምትታወቅባቸዉን የጦርነት ስልቶች በሳይንስ የተደገፉ ቴክኒካዊና የቴክኖሎጂ መሳርያዎች አጠቃቀም ግጭት አፈታትና መከላከል ስልጠናዎች እንደምትሰጥና በቡርኪናፋሶ ለሚደረግ የምዕራባውያን ጣልቃ ገብነት ማንኛውም ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን ገልፀዋል ።ሲል ያስነበበዉ faso 7 tv ነዉ ። #Ethiopia #BREAKING 📹📹 https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command https://t.me/Commando_And_Airborne_Command

🇧🇫 አደገኛ የፈረንሳይ ሰላይ በቡርኪናፋሶ ተተያዘች፤ በ NGO የእርዳታ ድርጅት ስም ለፈረንሳይ ስትሰልል የተደረሰባት ክሌሪ ዱቦይስ Hope Forward የተባለ የዕርዳታ ድርጅት ዳይሬክተር በመሆ
🇧🇫 አደገኛ የፈረንሳይ ሰላይ በቡርኪናፋሶ ተተያዘች፤ በ NGO የእርዳታ ድርጅት ስም ለፈረንሳይ ስትሰልል የተደረሰባት ክሌሪ ዱቦይስ Hope Forward የተባለ የዕርዳታ ድርጅት ዳይሬክተር በመሆን ነበር ወደ ቡርኪናፋሶ የገባችው ዓላማውም በሴቶችና ህፃናት ጤንነት ላይ ለመስራት በሚል ሽፋን ነበር። ራሷን የበጎ አድራጊ በማድረግ የተለያዩ የገጠር መንደሮች ትምህርትቤቶች በገበያዎች እየዞረች ጉብኝት ከማድረጓም በላይ አዲሱን የትራዖሬን መንግስትም በሀገሪቱ ቴሌቪዥን ስታወድስ ታይታለች። ይሁን እንጂ ከዚህ ሁሉ ጀርባ የስለላ ስራዋን በብቃት እያቀላጠፈች ነበር፣የሀገሪቱን የመከላከያና ወታደራዊ ተቋማት ፣የነዳጅና የሀይል መስጫ አካባቢዎች፣ የኮሙኒኬሽንና የመገናኛ ሲስተሞችን በድሮን ጭምር ፎቶ ስታነሳ ነበር። በተጨማሪ የሀገሪቱን ማፕና ጂኦግራፊ አቀማመጥ በማጥናት ለናቶና ለአውሮፓውያን የስለላ ተቋማት ታቀብል እንደነበር የቡርኪናፋሶው የኢንተለጀንስ ተቋም ደርሶበታል። ፕሬዚዳንት ትራዖሬ በተገኙበት የሰላይዋ ጉዳይ እየተጠና መሆኑንም ዘገባው ጠቁሟል፣የፈረንሳይ መንግስትና አሜሪካ በትራዖሬ ወደ ስልጣን መምጣትና አዲሱ ፖሊሲያቸው ስላልተደሰቱ ግለሰቡን ለማጥፋት የተለያዩ ሙከራዎችን እያደረጉ ሲሆን እስካሁን ግቡን አልመታላቸውም ትራዖሬ ሰሞኑን ለጉብኝት ሩሲያ ነበሩ። ከሩሲያ ጋር እጅና ጓንት መሆናቸው ያበሳጫቸው ምዕራባውያን ነገ ሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች የነሱን ፈለግ ከተከተሉ በሚል ከፍተኛ ስጋት ላይ ወድቀዋል። አቡ ሙስዓብ ከሜይፌር #Ethiopia #BREAKING 📹📹 https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command https://t.me/Commando_And_Airborne_Command

ሞስኮ‼ የቡርኪናፋሶ ፕሬዘዳንት ኢብራሂም ትራኦሬ ጋር የፎቶግራፍ ማስታወሻ ለማግኘት በሞስኮ የነበረው ድባብ በከፊል😳 #Ethiopia #BREAKING 📹📹 https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command https://t.me/Commando_And_Airborne_Command

❗️ሩሲያ እና ዩክሬን የጦር እስረኞች ልውውጥ አደረጉ ሁለቱም ሀገራት በአጠቃላይ 205 ወታደሮችን እንደተለዋወጡ የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል። የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የሩሲያ ወታደሮችን በማስመለሱ ሂደት አሸማጋይ እንደነበረች ሚኒስቴሩ ጨምሮ ገልጿል።