cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ትንሳኤሽን ያሳየን ውዲቷ ኢትዮጵያ

ሀገር ማለት ምንድነው? እውን ሰው ነው አልያም መልክዓ ምድር? ማንነትስ ማንንና ምንን ይመለክታል ~ኢትዮጵያ ማነች? ~ሰብዓዊነትስ የምንለው በምን መልኩ ነው እነዚህን አይነት ጥያቄዎች እየተነተንን ወደ እናንተ የምናደርስበት ቻናል ሀሳብ አስተያየቶቻችሁንበ @M162608 ያድርሱን

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدلم يتم تحديد اللغةالفئة غير محددة
مشاركات الإعلانات
266
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

ሰላም ለእናንተ ይሁን ቤተሰቦቼ በድጋሜ በመጥፋቴ ይቅር በሉኝ የተፈጥሮን ገፀበረከቶች እንደ አዲስ እየተመለከትኩ ኢትዮጵያዊ ትሩፋቶቻችን ምን ላይ ደርሰዋል የሚለው በመመልከት ላይ ስለነበርኩኝ መሆኑን ከወገቤ ዝቅ ብዬ ከጉልበቴ ሸብረክ ብዬ አሳስባለው🙏🙏🙏🙏🙏
إظهار الكل...
https://youtu.be/iaUHfxibYgk ጎብዝ እዚህ ግሩፕ ውስጥ 1132 ሰዎች አለን እርስ በራሳችን ሰብስክራይብ እንደራረግ አንዳችን ለአንዳንችን ተደጋግፈን እንደግ በተንኮል ሳይሆን በስራ ለማሸነፍ ከልባችን እንጣር
إظهار الكل...
የአርቲስት ዋና ሳጅን መኮንን ንጉሴ ጉዞ

ክፍል አንድ

መነበብ ያለበት መፅሐፍ #ማዕበሉ_ይፈጥናል!!!!!
إظهار الكل...
ኤሎሄ ወይ ውረድ ወይ ፍረድ ፈረደህ እንደ ሰዶም በቃ አጥፋን በንዳድ አልያም ውረድና አሰናብተን ከዚ በብርሀን ረአድ ከፊትህ የሚያቆም ግብር ስለሌለን ከፍርድህም ሚያድን ፅድቅ ስላልሰራን ከእንስሳነት መንደር ሰው ሲለምን ከማይ ከአናብስቶች ቀዬ ገድሎ ጀግና ነኝ ባይ ባየለበት ሀገር ባየለበት ሰማይ ሰውነት ሸቀጥ ነው የትም ይሰፈራል በማነሳቸው ልክ የእንስሳ ዛራቸው ልብን ይሸልታል እንጨት ፈልጦ ሲልክ በዓል ለሚቆጥር ፍየል በግ ለማረድ ውለታ ለሚያጥር ያረስኩትን በሬ ከሆዴ አላኖርም ብሎ ለሚለምን ለዚህ ሰዋዊ ሰው ካራ ለምኑ ነው ባንገቱ ሚዘምን ግና በእንስሳነት ዓለም ሺ በረከሰበት መፈናቀል መክተም በሆነበት ቀዬ በሆነበት ቀለም ጩኸት ዳባ ልበስ የምን ሰልፍ መውጣት የምን እግዚኦ አቤቱ ጨቋኝ ሲበዛ ነው የሚገለጥልን መሠልጠን ውበቱ ህግ ምን ማለት ነው ሰዶ ማሳደድ ነው የስልጣን እውነቱ ለመከተል እንባ😢😢😢😢 #አምላክ_ይፈርዳል_እባካችሁ_እንደ_ህዳር_አህያ_ማንም_አይጫነን!! @derto1234
إظهار الكل...
+በዙፋን ላይ የኢትዮዽያ ንጉሥ ሆኖ ቢቀመጥም እርሱስ አኗኗሩ ገዳማዊ ነበር: +ከተባረከች ሚስቱ ቅድስት መስቀል ክብራ ጋር አንዲት ማዕድ ብቻ በቀን ይቀምሱ ነበር:: ለዛውም ለምለሙን ለነዳያን ሰጥተው እነርሱ የሚበሉት የእንጀራውን ቅርፍት (ጠርዝ) ብቻ ነበር:: +በአካለ ሥጋ ወደ ሰማያት ተነጥቆ ብዙ ምሥጢራትን አይቷል: +በምሳሌውም ሃገረ ሮሃን (ላስታን) ገንብቷል: +ዛሬም ድረስ ምስጢር የሆኑት ፍልፍል አብያተ መቃድስ የእጆቹ ሥራዎች ናቸው:: +ሥራውን ከፈጸመ በሁዋላ መንግሥቱን ለቅዱስ ነአኩቶ ለአብ አውርሶ: በመንኖ ጥሪትና በቅድስና ኑሮ አርፏል:: ጌታችን ስምህን ያከበረ: ዝክርህን የዘከረ: ከቤትህ ያደረውን: ከርስተ መንግስተ ሰማያት አካፍለዋለሁ ሲል ቃል ኪዳን ገብቶለታል:: ይህቺ ዕለት ቅዱሱ ንጉሥ የተወለደባት ናት:: =>እኛን ስለ ወደደ ሰው የሆነ ጌታ ፍቅሩን ይሳልብን:: ከድንግል እናቱና ከልደቱ በረከትም ያሣትፈን:: =>ታሕሳስ 29 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት= 1.ልደተ ክርስቶስ ስቡሕ 2.ታኦዶኮስ (ድንግል ማርያም) 3.ቅዱስ ኢያሱ ነቢይ (ልደቱ) 4.ቅዱስ ላሊበላ (ልደቱ) 5.አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (ልደታቸው) 6.ጻድቅ አቃርዮስ (ንጉሠ ሮሃ) 7.ቅዱስ ቆሪል ገመላዊ 8.ሰብአ ሰገል 9.ዮሴፍና ሰሎሜ 10.ቅዱሳን ሰማዕታተ አክሚም =>ወርኀዊ በዓላት 1.ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት 2.ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ 3.ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ኢትዮዽያዊት 4.ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ 5.ቅድስት አርሴማ ድንግል =>"+"+" እነሆ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራቹሃለሁና አትፍሩ:: ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት: እርሱም ክርስቶስ: ጌታ የሆነ ተወልዶላቹሃልና:: "+"+" (ሉቃ. 2:10) <<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
إظهار الكل...
✝✞✝ እንኳን ለዓለም ሁሉ ጌታ #ኢየሱስ #ክርስቶስ" ዓመታዊ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✝✞✝ ✝"+" ልደተ ክርስቶስ "+"✝ =>ዓለማትን: ዘመናትን: ፍጥረታትን ሁሉ የፈጠረ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ: ወልደ አምላክ ነው:: የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጁ ሲሆን ራሱም እግዚአብሔር ነው:: በባሕርየ ሥላሴ መበላለጥ የለምና ወልድ ክርስቶስ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ትክክል ነው እንጂ አይበልጥምም: አያንስምም:: +እርሱ ቅድመ ዓለም የነበረ: ማዕከለ ዓለም ያለና ዓለምን አሳልፎ የሚኖር ጌታ ነው:: ቀዳማዊና ደኃራዊው: አልፋና ኦሜጋ እርሱ ነው:: (ዮሐ. 1:1, ራዕ. 1) ሁሉ በእጁ የተያዘ ነው:: +እርሱ እውነተኛ አምላክ (ሮሜ. 9:5): የዘለዓለም አባት: የሰላምም አለቃ ነው:: (ኢሳ. 9:6) ቅድመ ዓለም ሲሠለስ: ሲቀደስ ኑሮ ይህንን ዓለም ፈጠረ:: እርሱ ሁሉን ያስገኛል እንጂ ለእርሱ አስገኝ የለውም:: < አንድ ክርስቲያን ከሁሉ አስቀድሞ ሊያውቀው የሚገባ መሠረተ እምነት ይሔው ነው !! > +መድኃኒታችን ክርስቶስን በዚህ መንገድ የማያምንና የማያመልክ ሁሉ እርሱ ክርስቲያን አይደለም:: ምንም ሥጋችንን ተዋሕዶ ብዙ የትሕትና ሥራዎችን ቢሠራም: ቢሰቀል: ቢሞትም እርሱ እግዚአብሔር ነውና ፍጹም አምላክ ፍጹምም ሰው ብለን ልናመልከው ይገባል:: +እንደ አርዮስ: ንስጥሮስና ልዮን የማይገቡ ነገሮችን መናገር ጐዳናው የሞት: መዳረሻውም ገሃነመ እሳት ነው:: እንኩዋን የክብር ባለቤት መድኅን ክርስቶስ ላይ በፍጡር ላይ እንኩዋ የማይገባ ነገርን የተናገረ ሁሉ የገሃነም ፍርድ አለበት:: << ለእርሱ የዓለም ፈጣሪ: ጌታና ቤዛ ለሆነው መድኅን ኢየሱስ ክርስቶስ ለዘለዓለም ምስጋና: ጌትነት: ውዳሴና አምልኮ ይሁን !! >> +እግዚአብሔር አዳምን በ7 ሃብታት አክብሮ በገነት ቢያኖረው "አትብላ" የተባለውን ዕፀ በለስ በላ:: በዚህም ከፈጣሪው ተጣልቶ: በሞተ ሥጋ ሞተ ነፍስ: በርደተ መቃብር ርደተ ገሃነም ተፈረደበት:: በሁዋላ ግን ንስሃ ስለ ገባ "ከ5 ቀን ተኩል (5,500 ዘመን) በሁዋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ቃል ኪዳንን ሰጠው:: +ከዚህ በሁዋላ ለ5,500 ዘመናት ጊዜ ወደ ታች ይቆጠር ጀመር:: ስለ እግዚአብሔር ሰው መሆንና ዓለምን ማዳንም ትንቢት ይነገር: ሱባኤ ይቆጠር: ምሳሌም ይመሰል ገባ:: +ከአዳም እስከ ሙሴ (ዘመነ አበው) ምሳሌያት ይበዛሉ:: ከሙሴ እስከ ዳዊት (ዘመነ መሣፍንት) ምሳሌያቱ እየጐሉ መጥተዋል:: ከልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እስከ ቅዱስ ሚልክያስ ድረስ (በዘመነ ነቢያት / ነገሥት) ግን ትንቢቶች ስለ ክርስቶስና ስለ ማደሪያ እናቱ እንደ ጐርፍ ፈሰዋል:: +ነቢያትም የመሲህን መምጣት እየጠበቁ በጾም: በጸሎትና በትሕርምት ኑረዋል:: እንባቸውንም አፍሰው ቅድመ እግዚአብሔር ደርሶላቸዋል:: *"+" ልደተ ክርስቶስ እምድንግል "+"* =>"ጊዜው ሲደርስ አንባ ይፈርስ" እንዲሉ አበው መደኃኒታችን የጥልን ግድግዳ ያፈርስ ዘንድ: ከኃጢአትና ከሞት ቁራኝነት ይፈታን ዘንድ: ለሰዎች ቤዛ ይሆን ዘንድ: ትንቢተ ነቢያትን ይፈጽም ዘንድ: በቀጠሮ (በ5 ቀን ተኩል) ወደዚህ ዓለም መጣ:: +የሰማይና የምድር ጌታ በእንግድነት በመጣ ጊዜም እርሱን ለመቀበል በተገባ የተገኘች ንጽሕት ሙሽራ ድንግል ማርያም ሆነች:: ከእርሷ በቀር ለዚህ ክብር ሊበቃ የሚቻለው ፍጥረት: እንኩዋን ኃጢአት ካደከመው የሰው ልጅ ከንጹሐን መላእክት ወገን አልተገኘም:: +በጊዜውም መልአከ ትፍሥሕት ቅዱስ ገብርኤል መጋቢት 29 ቀን ወደ ድንግል ወርዶ የአምላክን ሰው የመሆን ዜና ከውዳሴና ከክብር ጋር ነገራት:: (ሉቃ. 1:26) ድንግልም ለ9 ወራት ከ5 ቀናት ሰማይና ምድር የማይችሉትን መለኮትን ተሸከመች:: +ልክ ሙሴ በደብረ ሲና እንዳያት ዕጽ ድንግል ማርያምንም ባሕርየ መለኮቱ አላቃጠላትም:: ስለዚህም ነገር "ወላዲተ አምላክ: ታኦዶኮስ: ንጽሕተ ንጹሐን: ቅድስተ ቅዱሳን: ንግሥተ አርያም: የባሕርያችን መመኪያ . . ." እያልን እንጠራታለን:: +ግሩም ድንቅ ጌታን ጸንሳ ዘጠኝ ወራት እስኪፈጸሙ ድረስ ብዙ ተአምራትን ሠራች:: መላእክተ ብርሃን እየታጠቁ አገለገሏት: አመሰገኗት:: ልጇን አምላክ: እርሷን እመ አምላክ እያሉ ተገዙላት:: +ከዚያም በሮሙ ቄሣር በአውግስጦስ ዘመን ሰው ሁሉ ይቆጠር ዘንድ አዋጅ ወጥቷልና እመ ብርሃን ማርያም ከቅዱሳኑ ዘመዶቿ ዮሴፍና ሰሎሜ ጋር ወደ አባቷ ዳዊት ከተማ ወደ ቤተ ልሔም ሔደች:: +በዚያም ሳሉ የምትወልድበት ጊዜ ቢደርስ በፍጹም ድንግልና እንደ ጸነሰችው ሁሉ በፍጹም ድንግልና ወለደችው:: (ኢሳ. 7:14, ሕዝ. 44:1) ተፈትሖም አላገኛትም:: ልማደ አንስትም አልጐበኛትም:: ምጥም አልነበረባትም:: +ድንግል ማርያም ክርስቶስን በወለደች ጊዜ ልጇ አምላክ: እርሷም የአምላክ እናት መሆኗ ይታወቅ ዘንድ:- 1.የብርሃን ጐርፍ ፈሰሰ: 2.99ኙ ነገደ መላእክት ወርደው "ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም" እያሉ ዘመሩ: 3.ትጉሐን እረኞች በቅዱስ ገብርኤል መሪነት መጥተው ክብሩን ተካፈሉ: 4.በሰማይም ልዩ ኮከብ ድንግልና ልጇ ተስለውበት ዝቅ ብሎ ታየ: 5.ቅድስት ሰሎሜም በድፍረት የድንግልን ሆድ ዳስሳ እጇ ቢቃጠል እንደ ገና በተአምራት ድኖላታል:: +በጊዜውም በምሥራቅ የፋርስ: የባቢሎንና የሳባ ነገሥት አስቀድሞ ከበለዓም: በሁዋላም ከዠረደሸት በተረዱት መሠረት ኮከቡን በማየታቸው ታጥቀው ተነሱ:: +ከምሥራቅ አፍሪቃና ከእስያም በተመሳሳይ ኮከቡን በማየታቸው 12 ነገሥታት በየግላቸው 10 10 ሺህ ሠራዊትን እየያዙ ድንግልንና ንጉሥ ልጇን ፍለጋ ወጡ:: +12ቱ ነገሥታት ከነ ሠራዊታቸው ሲሔዱ ስንቃቸው በማለቁ 9 ነገሥታት ተስፋ ቆርጠው ተመለሱ:: 3ቱ ግን በፍጹም ጥብዓት ከ30ሺ ሠራዊት ጋር በኮከብ እየተመሩ ኢየሩሳሌም ደረሱ:: +እነዚህም መሊኩ የኢትዮዽያ (የሳባ ንጉሥ ተወራጅ): በዲዳስፋና መኑሲያ (ማንቱሲማር) ደግሞ የፋርስና የባቢሎን ነገሥታት ናቸው:: ወደ ኢየሩሳሌም ሲደርሱም ሔሮድስና ሠራዊቱ ታወኩ:: +እነርሱ ግን የቤተ ልሔምን ዜና ከጠየቁ በሁዋላ በጐል ድንግል ማርያምን: ክርስቶስን: ዮሴፍና ሰሎሜን አገኙ:: ለ2 ዓመታት እነርሱን ፍለጋ ደክመዋል: ተንከራተዋልና ደስታቸው ወሰን አጣ:: +በእመቤታችንና በልጇ ፊት በደስታ ዘለሉ:: "አንፈርዓጹ ሰብአ ሰገል" እንዲል:: ወርቁን: እጣኑንና ከርቤውንም ገብረው: በግንባራቸው በፊቱ ሰገዱ:: 3 ጊዜም እየወጡ እየገቡ ቢመለከቱት በኪነ ጥበቡ አንዴ እንደ ሕጻን: በ2ኛው እንደ ወጣት: በ3ኛው እንደ አረጋዊ ሆኖ ታይቷቸው ፈጽመው አድንቀዋል:: +ወደ ሃገራቸው ሲመለሱም "ወአስነቀቶሙ ሕብስተ ሰገም" እንዲል የገብስ ዳቦ ጋግራ ድንግል ለሰብአ ሰገል ሰጠቻቸው:: እነርሱም ይህንን እየተመገቡ የ2 ዓመቱን መንገድ በ40 ቀን ሲጨርሱት ዳቦው ግን ያ ሁሉ ሺህ ሰው ተመግቦት አላለቀም:: ተአምራትንም ሠርቷል:: << የልደቱ ነገር እንዲሁ ተተርኮ የሚያልቅ አይደለምና ይቆየን:: የከርሞ ሰውም ይበለን:: >> +*" ቅዱስ ላል-ይበላ ንጉሥ "*+ =>በ12ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ ላይ በሃገራችን የነገሠው ቅዱስ ላሊበላ:- +በብሥራተ መልአክ ተወልዷል: +ቅዱሳት መጻሕፍትን ገና በልጅነቱ አጥንቷል: +የንጉሥ ዘር ቢሆንም በጾምና ጸሎት: በትሕርምት አድጉዋል:: +በወንድሙ ቢገረፍም ቂም አልነበረውም: +ስለ ወዳጆቹ ፍቅር መርዝ ጠጥቷል:
إظهار الكل...
ከወደድኩት ላካፍላቹ
إظهار الكل...
#ሕፃን ተወልዶልናል ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል ስሙም ድንቅ መካር፣ኃያል አምላክ፣የዘላለም አባት፣ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል 🙏🙏🙏ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችን ለመድሀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በጤና አደረሳችሁ ሀገራችን ሀገር ሰላም ዘመናችንን ዘመነ ፍስሀ ያድርግልን አሜን!!!!! @derto1234
إظهار الكل...
ክፍል ፩ ሰላም ለእናንተ ይሁን የቻናሌ ቤተሰቦች እንደምን አረፈዳችሁ ሁሌም እንደምንለው #ምርጥ ምርጡን ለእናንተ ብለን ይዘን መተናል ለዛሬ የኢትዮጵያን የስም አመጣጥ የታሪክ ምሁራን እንዳስቀመጡት እናመላልስ #ኢትዮጵያ የሚለው ቃል አመጣጥ በተለያዩ የታሪክ ምሁራን የተለያየ ገለፃ ሲኖረው በጣም ተአማኒነህ ካገኙት አንዱ አይቲዮፒያ የሚለው የግሪክ ቃል ነው። ኢትዮጵያ ድሮ ለውጭ ሀገራት አቢሲኒያ በሚል መጠሪያ ትታወቅ ነበር ይህም ስያሜ የመጣው ከሀበሻ ነበር። ኢትዮጵያ የሚለውን ስም ጥንታዊነት የሚታወቅ ከግሪክ ጸሐፍት ነው። ከሁሉ ቀድሞ የሆነው ሪሩክ ባለቅኖ ሆሜር ይጠቅሰዋል።በግሪክ አጠቃቀም ከሰሀራ በረሃ በስተደቡብ ላለው የአፍሪካ አህጉር ክፍል በሙሉ ሲገለፅ በተለይም ለኩሽ በሚነካ ትርጉሞች ይገኛል።ፕሊኒ እንደሚለው በኢትዮጵያ መጽሐፍት ልማድ የሀገሩ ስም የኩሽ ልጅ ኢትዮጲስ ማክሼ ነው። ሆኖም በአቅራቢያው እንደ መንግሥት ስም መጀመሪያ የተመዘገበው ዘመን የአክሱም ንጉሥ ኢዛና ዘመነ መንግሥት አራተኛው ክፍለ ዘመን ነበር። ይህ እንደ መግለቢያ እንየው ይቀጥላል......... #ኑ ሰው እንሁን @derto1234 @derto1234 ሀሳብ አስተያየቶቻችሁን በ @M162608 ያድርሱን
إظهار الكل...
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.