ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ
الذهاب إلى القناة على Telegram
ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።
إظهار المزيد636
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-47 أيام
-1230 أيام
أرشيف المشاركات
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ሚያዝያ ፳፱ (29) ቀን።
❤ እንኳን #ከሰባ_ሁለቱ_አርድእት ለአንዱ መራራ የሆኑ ውኃዎችን ለውጦ ጣፋጮች ላደረጋቸው፤ የደረቁ ዕንጨቶችንም ላለመለመና በደዌ የተጨነቁ ብዙ በሽተኞችንም ላዳነ #ለሐዋርያ_ለቅዱስ_አርስጦስ ዕረፍት በዓልና ለንጹሕ ደግ ቅን ለሆነ ለኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ #ለአባ_አካክዮስ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ ከክብር ባለቤት #ከጌታችን_ከኢየሱስ_ክርስቶስ_ከልደቱ (በዓለ ወልድ) ከወራዊ መታሰቢያ በዓል፣ #ከአባ_ገምሶና ከእርሱ ጋራ ከሆኑ ከብዙ ሰማዕታት ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_አርስጦስ፦ ይህም ቅዱስ ከሐዋርያት ጋራ በጽርሐ ጽዮን የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ከተቀበለ በኋላ ከአገሩ ሁሉ ቋንቋ ተናገረ። ሐዋርያትንም እያገለገለ ከእሳቸው ጋራ ሲሰብክ ብዙ ጊዜ መከራ ተቀበለ።
❤ ከዚህም በኋላ ሐዋርያት መርጠው ለኢየሩሳሌም ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ሾሙት። በዚችም አገልግሎት ጥቂት ቆይቶ ብስጥስ በሚባል አገር ላይ ሁለተኛ ኤጲስቆሰነት ሾሙት። በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም በውስጥዋ አስተምሮ አንድነትንና ሦስትነትን በማሳወቅ የሰዎቿን ልቡና ብሩህ አደረገ። የጣዖታትንም ቤቶች አፍርሶ አብያተ ክርስቲያንን ሠራ በክብር ባለቤት በጌታችንም ስም አጸናቸው።
❤ ታላላቅ አስደናቂ ተአምራትን በማድረግ መራራ የሆኑ ውኃዎችን ለውጦ ጣፋጮች አደረጋቸው፣ የደረቁ ዕንጨቶችንም እንዲያለመለመልሙና እንዲአፈሩ አደረጋቸው፣ በደዌ የተጨነቁ ብዙ በሽተኞችንም አዳነ ወደ በጎ እርጅና ደርሶ እግዚአብሔር አገልግሎ ሚያዝያ29 በሰላም ዐረፈ። እንሆ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በመልክቱ አስታውሶታል። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ሐዋርያ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_አካክዮስ፦ ይህ አባት ንጹሕ ደግ ቅን የሆነ የኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ ነው። ይህንንም ቅዱስ ከሀድያን ብዙ ቀኖች አሠቃዩት እግዚአብሔር በእጆቹ ብዙ ተአምራትን አደረገ ከዚህም በኋላ ሚያዝያ29 በፍቅር አንድነት ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዠላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ 29 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ዕብል_አርስጦስሃ_ፍጹም። ኤጲስቆጶስና በእደ ሐዋርያት ተሠይመ። ለሀገረ ብናጥስ ሕዝብ እንዘ ያርኢ መድምመ። ገብረ በጸሎቱ ይቡስ ዕፅ ልምሉመ። ወምረረ ማይ ረሰየ ጥዑመ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_29።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "አልቦ ነገር ወአልቦ ነቢብ ዘኢተሰምዐ ቃሎሙ። ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ። ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ"። መዝ 18፥3-4። የሚነበቡት መልዕክታት ቈላ 4፥10-14፣ 1ኛ ዮሐ 4፥918 እና የሐዋ ሥራ 13፥4-16። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 10፥1-12። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም በዓልና የበዓለ ሃምሳ ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
Repost from የግ/ደ/ቅ/አርሴማ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ቤት መዝሙር ክፍል
በግራር ደብረዓባይ ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን አካባቢ የምትገኙ ፣
መኖርያችሁን
📍በአለምባንክ ፣
📍በአየርጤና ፣
📍በካራ፣
📍በቤቴል ያደረጋችሁ::
በቅርብም በሩቅም ያላችሁ የክርስቶስ ቤተሰቦች ተጋብዛችኋል::
ወጣቶች፣
በአቅራቢያ የምትገኙ በሰንበት ት/ቤት ያደጋችሁ፣
በመንፈሳዊ ማኅበራት ያደጋችሁ፣
የጽዋ ማኅበራትም ጭምር፣
ጥሪው ሁሉንም ኦርቶዶክሳዊ ይመለከታልና አዳርሱ::
Forward
❤ "በአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ሚያዝያ ፳፰ (28) ቀን።
❤ እንኳን በኮራሳት ተራራ በገድል ተጠምዶ ለሚኖር በሐሰት ሰው ገድለሃል ብለውት የሞተውን ሰው አስነስቶ ላስመሰከረ #ለቅዱስ_አባት_ለአባ_ሜልዮስና መቅሱር ለሚባል አገር ለሆነ #ለቅዱስ_ብስጣውሮስ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ #ከዋሲሊኮስና ከብዙ ሰማዕታት ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_ሜልዮስ፦ ይህም አባት ኮራሳት በሚባል አገር በተራራ ባሉ ዋሻዎች ከሁለት አርድእቱ ጋራ ይኖር ነበር። የኮራሳት ንጉሥ ሁለት ልጆቹ ወደዚያ ወጡ ከእርሳቸውም ጋራ አገልጋዮች አሉ አራዊትን አጥምደው በፍላፃዎች ይገሉ ዘንድ መረባቸውን ተክለው አርባ ምዕራፍ ያህል ሔዱ። መረቡን በጠቀለሉት ጊዜ ይህን ቅዱስ አባት ማቅ ለብሶ ጠጉሩም የረዘመ ሁኖ አገኙት።
❤ የንጉሥ ልጆችም በአዩት ጊዜ ፈሩ አንተ ሰው ነህን ወይም መንፈስ ብለው ጠየቁት እርሱም "በዚህ ተራራ ውስጥ የምኖር ለሕያው እግዚአብሔር ልጅ ለጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ የምሰግድ ሰው ነኝ" ብሎ መለሰላቸው። እነርሱም "ከእሳትና ከፀሐይ በቀር አምላክ የለም እንዳንገድልህ ሠዋላቸው" አሉት። እርሱም "እሳትና ፀሐይ የተፈጠሩ ናቸው እናንተም ተሳስታችኋል ፍጥረቶችን በፈጠረ በእውነተኛ አምላክ ታምኑ ዘንድ እኔ እለምናችኋለሁ" ብሎ መለሰላቸው። በዚያን ጊዜ ይህን አባት ሁለቱን አርድእትም ይዘው ጽኑ ሥቃይ አሠቃዩአቸው በዚህ ወር በዐሥራ ሦስት የሁለቱን አርድእት ራሳቸውን ቆረጡአቸው የሰማዕትነት አክሊል ተቀበሉ።
❤ አረጋዊ ቅዱስ ሜልዮስን ግን ዐሥራ አምስት ቀን ያህል ሲአሠቃዩት ኖሩ ከዚህ በኋላ በመካከላቸው አቆሙት አንዱ በፊት አንዱ በኋላ ሁነው በፍላፃ ይነድፉት ጀመር። እርሱም "በእናንተ ላይ ክፉ ያልሠራውን ለመግደል ሁለታችሁ ስለተስማማችሁ እንዲሁ እንደሥራችሁ በፍላፃችሁ ነገ ትሞታላችሁ" አላቸው። ሰምተውም አልፈሩም ነፍሱን እስከሚአሳልፍና ምስክርም ሆኖ የሰማዕትነት አክሊል እስከሚቀበል ነደፉት እንጂ። በማግሥቱም እንደልማቸው ለአደን ወጡ የዱር አህያም አገኙ ተከትለውም ቀስታቸውን አስፈነጠሩ እግዚአብሔር ፍላፃቸውን ወደልባቸው መለሰ ቅዱስ ሜልዮስም እንደተናገረባቸው ሞቱ።
❤ በዚህ ቅዱስም እጅ ጌታችን ተአምራትን ገለጠ በአንዲት ዕለትም አልፎ ሲሔድ በመንገድ ላይ የሞተ ሰው አገኘ የአገር ሰዎች ግን አንዱን መነኰስ አንተ ነህ የገደልከው ብለው ያዙት። ቅዱስ ሜልዮስም ጸለየ "የሞተውም በውኑ የገደለህ ይህ መነኵሴ ነውን?" አለው ያን ጊዜ የሞተው ተነሥቶ "እርሱስ አልገደለኝም ነገር ግን ብዙ ገንዘቤን ከአንድ ቄስ ዘንድ አደራ አስጠበቅሁ ስለዚህ ገደለኝ ከዚህም ጣለኝ" አለ ደግሞ እንዲህ ብሎ ለመነው "ዕገሌ ወደሚባል ወደዚያ ቄስ ሒደህ ገንዘቤን ከርሱ ተቀብለህ ለልጆቼ ስጥ" አለው። ቅዱስ ሜልዮስም "እስከ ትንሣኤ ቀን በሰላም ዐርፈህ ተኛ እኔ ገንዘብ አከፋፋይ ዳኛ አይደለሁም" አለው ያንጊዜም ተኛ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ በቅዱስ ሜልዮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_ብስጣውሮስ፦ የዚህም ቅዱስ አባቱ ጻድቅ ሰው ነው እናቱን ግን ሰይጣን አስቷት ወደ እስልምና ገባች እርሱም ፈሪሀ እግዚአብሔርን እየተማረ እስከሚጐለምስ አደገ አካለ መጠንም አድርሶ ሚስት አገባ ከርሷም ልጆችን ወለደ።
❤ ብዙ ዘመናትም በአለፉ ጊዜ አንገተ ደንዳና በቀለኛ ሰው በእርሱ ላይ ተነሥቶበት ወደ እስላሞች መኳንንት ሒዶ ሰው ወደ እኛ ሕግ ቢገባ ልጆቹም ሃይማኖቱን ይከተላሉ ይህ ብስጣውሮስ ግን ከሕጋችን የተለየ ነው ብሎ ነገር ሠራበት። የእስላሞች ዳኞችም በሰሙ ጊዜ መልክተኞች ልከው ወደርሳቸው ወደ ሸንጎ አቀረቡት ስለ ሃይማኖቱም ጠየቁት ክርስቲያን እንደሆነ ያለ ፍርሀት ክርስቲያን ነኝ ብሎ ታመነ። ዳኛው ግን ይሸነግረው ዘንድ በፍቅር ይናገረው ጀመር ከከበረችና ከቀናች ሃይማኖቱ ይመለሰው ዘንድ ብዙ ስጦታዎችን እንደሚሰጠው ቃል ገባለት ቅዱሱ ግን ከቶ አልተመለሰም ወደ ስጦታውም ከቶ ልቡ አላዘነበለም።
❤ ከዚህ በኋላ ወደ ግዞት ቤት ወስደው በእግረሙቅ እንዲአሥሩት በአንገቱም የተበሳ ታላቅ ግንድ አሥረው በግንባሩ ደፍተው በኵስ ላይ እንዲጥሉት መኰንኑ አዘዘ። እንዲሁም አደረጉበት እስከ ሦስት ቀን በእሥር ቤትም ሳለ ፀዐዳ ርግብ መጥቶ ጋረደው ስለዚህም የእሥር ቤቱ ጠባቂ ምስክር ሆነ።
❤ ከዚህም በኋላ ዳኞች ወደ ሸንጎ አስቀርበው "ከእንዲህ አንታገሥህም ወደ ሃይማኖታችን ከምትገባና ወይም በእሳት ከምናቃጥልህ ምረጥ" አሉት። እርሱም እኔ ከእናንተ ጋራ ለዘላለሙ ዕድል ፈንታ የለኝምና የወደዳችሁን አድርጉ" ብሎ መለሰላቸው። በዚያን ጊዜም እጅግ ተቆጡ ያለ ርኅራኄ ይደበድቡት ዘንድ አዘዙ ያገር ሰዎችም በጫማቸው መቱት አንዲት ሴትም መጥታ በጫማዋ መታችው ወዲያውኑ እጆቿ ደረቁ። ከዚህም በኋላ ባለ ሰይፍ ከመኰንኑ ታዝዞ ወጣ ሰይፉንም መዝዞ ሳያቋርጥ መላልሶ አንገቱን መታው። ምቱም ወደ ጐን ሒዶ ጀሮውን ቆረጠው አመታቱ ክፉ ስለ ሆነ ከሥሮቿ ብዙ ደም ፈሰሰ። ከዚህም ደግሞ ተዉት እምነታቸው ሊአስገቡት እምቢ በአላቸውም ጊዜ ሁለተኛ ሰይፉን መዝዞ ሰያፊው የከበረች አንገቱን ሚያዝያ28 ቆረጠው በመንግሥተ ሰማያትም የምስክርነት አክሊልን ተቀበለ። ሥጋውንም ከእሳት ጨመሩ ግን አልተቃጠለም። ዘመዶቹም መጥተው በድኑን ወደአገሩ ወሰዱ። በቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ ጐን ቀበሩት። የክብር ባለቤት ጌታችንም ብዙ ድንቆች ተአምራትን ከሥጋው ገለጠ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ በከበረ ሰማዕት ጸሎት ለዘለዓለሙ ይቅር ይበለን አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ 28 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ዕብል_ለሚልዮስ_ጻድቅ። እምፍትወተ ሥጋ ርኁቅ። እንዘ ይነድፍዎ ሎቱ በአሕፃሆሙ ውሱቅ። እፎ ኢያኅዘኖሙ ለነዐውተ አርዌ ደቂቅ። ሥእርተ ርእሱ ነዊኀ ወልብሱ ዘሠቅ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_28።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ዕቀበኒ እምሥገርት እንተ ኀብኡ ሊተ። ወእማዕቀፎሙ ለገብርተ ዓመፃ። ለይደቁ ውስተ መሥገርቶሙ ኃጥአን"። መዝ 140፥9-10። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 4፥1-14፣ ያዕ 2፥19-ፍ.ም፣ የሐዋ ሥራ 7፥1-9። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 12፥8-17። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ወይም የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የበዓለ ሃምሳ ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
+5
"ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ፤ እግዚአብሔር በመካከልዋ ነው አትናወጥም" መዝ ፵፮፥፭
ሚያዝያ 27 ቀን 2017 ዓ.ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት እና በብፁዓን አባቶች ተባርከው አገልግሎት የጀምሩት የመድኃኔ ዓለም ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ።
① የካራ አሎ ደብረ ቀርሜሌዎስ መድኃኔዓለምና ጻድቁ አቡነ ገሪማ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን
② የቃሊቲ በርታ ደብረ መንክራት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን
③ በሸገር ከተማ ሀገር ስብከት የቀርሳ ደብረ ሰላም መድኃኔለም ቤተ ክርስቲያን
④ የአሶሳ እንዚ መካነ ገነት መድኃኔዓለም ካቴዴራል
⑤ አምቦ ደብረ መንክራት ቤተ ሰይዳ መድኃኔዓለም እና በዓታ ማርያም ካቴድራል
⑥ በደቡብ ወሎ ዞን በወገልጤና ከተማ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን
+4
"ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ ፤ ይህ ነገር ጥልቅ ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው ፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡" ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሚያዚያ 26 ቀን 2017 ዓ.ም በግራር ደብረ አባይ ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ከወንድማችን ብርሃኑ ሀይሌ ( ሀይለ ማርያም ) ጋር የጋብቻ ሥነ ሥርዓትሽን የፈጸምሺው የሰንበት ት/ቤታችን አገልጋይ ቤተልሔም ጌትነት ( ወለተ ሥላሴ ) እንኳን ደስ ያለሽ እንኳን ደስ ያላችሁ ።
የአብርሃምንና የሣራን ፤ የይሰሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ አንድነታችሁን ይባርክ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ ፤ ቅዱስ ሚካኤል ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ እያለች ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት መልካም የትዳር ሕይወት ትመኝላችኃለች።
" ጋብቻ ንጹሕ ነው የወንድና የሴት አንድ መሆንንም እግዚአብሔር አክብሮታል "
መጽሐፈ ዲድስቅልያ
+9
"ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ ፤ ይህ ነገር ጥልቅ ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው ፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡" ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሚያዚያ 26 ቀን 2017 ዓ.ም በግራር ደብረ አባይ ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ከእህታችን ፌቨን ( ወለተ ተክለሃይማኖት ) ጋር የጋብቻ ሥነ ሥርዓትህን የፈጸምከው የሰንበት ት/ቤታችን አገልጋይ ድንቅነህ ሲሳይ ( ሀብተ ማርያም ) እንኳን ደስ ያለህ እንኳን ደስ ያላችሁ ።
የአብርሃምንና የሣራን ፤ የይሰሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ አንድነታችሁን ይባርክ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ ፤ ቅዱስ ሚካኤል ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ እያለች ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት መልካም የትዳር ሕይወት ትመኝላችኃለች።
" ጋብቻ ንጹሕ ነው የወንድና የሴት አንድ መሆንንም እግዚአብሔር አክብሮታል "
መጽሐፈ ዲድስቅልያ
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ሚያዝያ ፳፯ (27) ቀን።
❤ እንኳን #ለምካየ_ኅዙናን_መድኃኔዓለም_ለዓመታዊ በዓል (በአፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት ፋሽሽት ጣልያን 1928 በድጋሚ ኢትዮጵያን ወሮ 1933 ድጋሚ ተሸንፎ ለወጣበት፤ #ለ84 (ለሰማንያ አራተኛው ዓመት ለርበኞች ቀን መታሰቢያ) ፣ በአባቱ ትዕዛዝ ሰማዕታት ለተቀበለ #ለታላቁ_ሰማዕት_ለቅዱስ_ፊቅጦር ለዕረፍትና በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ #ከቅዱስ_ፊቅጦር እናት #ከቅድስት_ማርታ፣ #ከቅዱሳን_ሲኖዳና_እስጢፋስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ሰማዕቱ_ቅዱስ_ፊቅጦር፦ ለዚህ ቅዱስ የአባቱ ስም ኅርማኖስ ነው እርሱም ለዲዮቅልጥያኖስ የአማካሪዎቹና የሠራዊቱ አለቃ ነው ስለ አምልኮ ጣዖት ሥራ ምክሩና ንግግሩ ሁሉ ከእርሱ ጋራ ነበር የእናቱም ስም ማርታ ይባላል በክርስትናዋ የጸናች ብፅዕት ናት።
❤ ቅዱስ ፊቅጦርም በአደገ ጊዜ አባቱ ወደ ንጉሥ አቀረበው ንጉሡም በመንግሥቱ ውስጥ ሦስተኛ ማዕርግ አድርጎ ሾመው በዚያን ጊዜ ዕድሜው ሃያ ዓመት ነበረ። እርሱም የዚህን ዓለም ክብር ናቀ ሥጋ አይባላም ወይን አይጠጣም ዘወትርም ይጾማል ጸሎትንም ባለማቋረጥ በቀንና በሌሊት ይጸልያል። በክብር ባለቤት ክርስቶስ ስም የታሠሩትን ይጐበኛቸዋል ለድኆችና ለምስኪኖችም ይመጸውታል።
❤ የቅዱስ ቆዝሞስና ድምያኖስ እናት ቅድስት ቴዎዳዳን በገደሉዋት ጊዜ ንጉሡም ስለ መፍራት ሊቀብራት ማንም አልደፈረም። ይህ ቅዱስ ፊቅጦርም መጥቶ ሥጋዋን ወሰደ ከንጉሥ ስለሚመጣው ቅጣት ሳይፈራ ቀበራት። ጣዖት ስለ ማምለኩ አባቱን ዘወትር የሚገሥጸውና ብዙ ጊዜም የሚመክረው ሆነ አባቱም ወደ ንጉሥ ከሰሰው እንጂ አልሰማውም። ተከሶም ወደ ንጉሥ በአቀረቡት ጊዜ "አማልክት ያልሆኑ ርኲሳን ጣዖታትን ለሚያመልክ ሰነፍ ዝንጉ ልብ የለሽ ለሆነ ንጉሥ አላገለግልም። ከዛሬ ጀምሮ ለሕያው ንጉሥ ክርስቶስ እገዛለሁ የሰጠኸኝንም ገንዘብህን ንሣ" ብሎ በፊቱ ትጥቁን ፈትቶ ጣለለት።
❤ አባቱ ኅርማኖስም ወደ እስክንድርያ እንዲልከውና በኄርሜኔዎስ መኰንን ዘንድ በዚያ ፊቅጦር እንዲቀጣ ንጉሡን መከረው። በዚያን ጊዜም ከአደባባይ አወጡት እናቱም በብዙ ልቅሶ ልትሸኘው መጣች። እርሱም ሲመግባቸው ስለ ነበረ የታሠሩ ምዕመናን ስለ ድኆችና ምስኪኖች ስለ ሙት ልጆችና ስለ ባልቴቶች የሚሹትን በመስጠት እንድትጐበኛቸው አዘዛት ከዚያም አፉን ለጉመው ወሰዱት።
❤ በእስክንድርያ አገር ወደ መኰንኑ ኄርሜኔዎስ ዘንድ በደረሰ ጊዜ ታላቅ ሥቃይን አሠቃዩት የእግዚአብሔርም መልአክ ወደ ሰማያት አውጥቶ ስለ ክብራቸው ለመናገር የሚያስጨንቁ የብርሃን ማደሪያዎችን አሳይቶ ወደ መኖሪያው መለሰው። መኰንኑም በእሳት በአፈሉት በዝፍት፣ በዲን ደግሞ አሠቃየው ከዚያም በብረት አልጋ ላይ አስተኝተው ከበታቹ እሳትን አነደዱ። ደግመው ከውሽባ ማንደጃ ውስጥ ጨመሩት በየአይነቱ በሆነ ሥቃይም አሠቃዩት የክብር ባለቤት ጌታችንም ያጸናውና ከሥቃዩ ያስታግሠው መልአኩንም ልኮ ከቊስሉ ይፈውሰው ነበር።
❤ ከዚህም በኋላ ወደ እንዴናው ከተማ ላከው በዚያም ታላቅ ሥቃይን አሠቃዩት ምላሱን ቆረጡ። በእሳት ያጋሉዋቸውን ችንካሮች በጐኖቹ ውስጥ ጨመሩ እግዚአብሔር ግን አጽንቶ አስታግሦ ያለ ጉዳት በደኅና ያነሣዋል። ከዚህም በኋላ በዚያ በረኃብ እንዲሞት ከዱር ባለ ግምብ ውስጥ አሠሩት። እርሱ ግን መጥረብ የሚያውቅ ስለሆነ ላይዳዎችን በመጥረብና በመሸጥ በየጥቂቱ እየተመገበ የቀረውን ለድኆች እየሰጠ ኖረ። አንድ መኰንንም መጥቶ በዚያ ግምብ አቅራቢያ አደረ ስለ ቅዱስ ፊቅጦርም እርሱ የንጉሥ የሠራዊት አለቃ የሆነ የኅርማኖስ ልጅ እንደሆነ ነገሩት። መኰንኑም ወደርሱ አቅርቦ ብዙ ሸነገለው ባልሰማውም ጊዜ ያሠቃዩት ዘንድ አዘዘ ጅማቶቹን መዘዙ አፋን መቱት ቊልቊል ሰቀሉት በእጆቹ ላይ ከባድ ደንጊያ አንጠልጠሉ። ከዚያም ከሚነድ እሳት ውስጥ ጨመሩት ሙጫ፣ አደሮ፣ ማርና ዘይትን አፍልተው በላዩ ደፉበት በማበራያም አበራዩት አፉንም በአሞትና በእሬት አመረሩት ዐይኖቹንም አወለቁት ደግመውም ዘቅዝቀው ሰቀሉት። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጾለት አጸናው አረጋጋው። ሥሮቹንም ሕዋሳቶቹን በቦታቸው መለሰለትና አዳነው።
❤ አንዲት ዓሥራ አምስት ዓመት የሆናት ብላቴና ነበረች ቅዱስ ፊቅጦርን ሲአሠቃዩት በቤቷ መስኮት ታየው ነበር። መላእክትም በእጆቻቸው አክሊሎችን ይዘው እነርሱም በቅዱስ ፊቅጦር ራስ ላይ ሲያኖሩአቸው አይታ እንዴት እንዳየች ለአሕዛብ ነገረቻቸው እጅግም አደነቁ ከእርሳቸውም ብዙዎች በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምነው በሰማዕትነት ዐረፉ። ያቺም ብላቴና በጌታችን አመነች መኰንኑም ራሷን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ። የሕይወት አክሊልንም ተቀበለች ሁለተኛም የአመኑትን ሁሉ ራሳቸውን እንዲቆርጡአቸው አዘዘ የሕይወትንም አክሊል ተቀበሉ።
❤ ከዚህም በኋላ የከበረች የቅዱስ ፊቅጦርን ራስ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ተጋድሎውንም ሚያዝያ27 ፈጽሞ የሕይወትና የድል አክሊል ተቀበለ። ምዕመናን ሰዎችም ሥጋውን ወስደው በከበሩ ልብሶች በድርብ በፍታ ገነዙት። እናቱ ማርታም ከአንጾኪያ እስክትመጣ በንጹሕ ቦታ አኖሩት በመጣችም ጊዜ ከዚያ ወሰደችው። ውብ ቤተ ክርስቲያንም ሠርታ ሥጋውን በውስጥዋ አኖረች ከእርሱም ታላላቅ ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የቅዱስ ፊቅጦር በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ 27 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለፊቅጦር_ተአምራቲሁ_ዘአርአየ። ድኅረ በሰይፍ ተወቅየ። ልብሱ ዘወርቅ አመ ተኀድገ በዝየ። ያሠርጉ ጣዖታቲሁ ሶበ ልበ ንጉሥ ሐለየ። ኀበ ህላዌሁ ተመሥጠ ሰማየ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_27።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ውእተ ጊዜ እቤ ነየ መጻእኩ። ውስተ ርእሰ መጽሐፍ ተጽሕፈ በእንቲአየ። ከመ እንግር ፈቃደከ መከርኩ አምላኪየ"። መዝ 39፥7-8። የሚነበበው ወንጌል ማር 10፥1-12።
✝️ ✝️ ✝️
❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "ወበእግዚአብሔር ተወአልኩ ኢይፈርህ ምንተ ይሬስየኒ ዘሥጋ። ወኵሎ አሚረ ያስቈርሩኒ ዘነበብኩ። ወላዕሌየ ይመክሩ ኵሎ እኩየ"። መዝ 55፥4-5። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ቆሮ 8፥4-10፣ 1ኛ ጴጥ 2፥21-ፍ.ም፣ የሐዋ ሥራ 5፥29-34። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥16-24። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ወይም የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጎድ ቅዳሴ ነው። መልካም የምካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም በዓልና የበዓለ ሃምሳ ጊዜ ለሁላችን ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ሚያዝያ ፳፮ (26) ቀን።
❤ እንኳን በአባቱ እጅ በመጥረብያ አንገቱን ተመቶ ሰማዕትነት ለተቀበለ፤ አባቱን ከዐረፈ በኋላ ለፈወሰው #ለጠራቢ_ልጅ_ለቅዱስ_ዮሐንስ ለዕረፍት ለዕረፍቱ በዓልና #ለሱሴ_ልጅ_ለቅዱስ_ሱስንዮስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ #ከቅዱሳን_ስብስጥራስ_ከአባ_ሠርጋና፣ #ከይድራስ ከምስክርነታቸው መታሰቢያና #ከቅዱስ_ሱስንዮስ ጋራ ሰማዕትነት ከተቀበሉ #ከአንድ_ሺህ_አንድ_መቶ_ዘጠኝ_ሰማዕታት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_ዮሐንስ፦ ይህም ቅዱስ ከነነዌ አገር ነው አባቱ ጣዖትን የሚጠርብና የሚያመልክ ነው። እናቱ ግን ክርስቲያናዊት ናት ልጅ በአጣችም ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ለመነች ጌታም ልመናዋን ተቀብሎ ይህን የተባረከ ልጅ ሰጣት ስሙንም በሥውር ዮሐንስ ብላ ጠራችው። ስምንት ዓመትም በሆነው ጊዜ የጠረበውን ጣዖት እየሸጠለት አባቱን ያገለግል ነበር።
❤ በአንዲት ዕለትም ጣዖቱን ሊሸጥ ሲሔድ የእግዚአብሔር መልአክ ተገናኘውና "ጣዖት የሰይጣን ማደሪያ እንደሆነ ነገረው ጣዖቱንም ከእጁ እንዲጥለው አዘዘው በክብር ባለቤት በክርስቶስ ማመን አስተማረው" ወደ አባቱም በተመለሰም ጊዜ "ሰማይና ምድርን በውስጣቸውም ያለውን ሁሉ ከፈጠረ ከክብር ባለቤት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ሌላ አምላክ የለም እኔ ለሰው እጅ ሥራ አልሰግድም" አለው። አባቱም ሰምቶ በእሥር ቤት አሰረው እናቱም መጥታ በክብር ባለቤት ክርስቶስ ስም ደሙን ያፈስ ዘንድ አጸናችው።
❤ ከዚህም በኋላ በነገራቸው ሊሸነግሉት የአገር ሰዎች መጥተው "የአባትህ አምላኮች ለምን ተውክ" አሉት እርሱም "እኔ የሰው እጅ ለሰራቸው ጣዖቶች አልሰግድም እነርሱም የእርኵሳን አጋንንት ማደርያዎች ናቸውንና" አላቸው። አባቱም ይህንን በሰማ ጊዜ ምሳር አንስቶ አንገቱ ቆረጠው በድኑም አልወደቀም በደሙም እስከተጠመቀ ድረስ በእግሮቹ ቆመ እጅ።
❤ እናቱም በደሞ ተጠምቃ "አቤቱ የክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የአቤል መስዋዕት በምድረ በዳ የተቀበልክ ይህንን መስዋዕት ከእኔ ተቀበል" አለች። በዚያ ጊዜ አባቱ ሰይጣን አደረበትና አበደ ሚስቱን ወደ ልጇ መቃብር ወስዳው ስለ እርሱ ጸለየች ቅዱስ ዮሐንስም በሌሊት ወደ እርሱ መጥቶ አባቱ በጦር ወጋው ሰይጣኑም ከእርሱ ወጣ ከዚህ በኋላ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመነና በስሙ ተጠመቀ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_ሱስንዮስ፦ ይህም ከሀዲው ከዲዮቅልጥያኖስ ወዳጁ ነበረ የእግዚአብሔር መልአክም ተገለጠለትና ሰማዕት እንደሚሆን ነገረው ይህም ነገር በልብ አደረ።
❤ከዚህም በኋላ አምልኮ ጣዖትን እንዲያስፋፋና እንዲያድሱ ከሹመት ደብዳቤ ጋራ ንጉሡ ወደ ኒቆድምያ ላከው ቅዱሱም አይቶ እጅግ አዘነ ወደ እርሱ አንድ ቄስ አምትቶ ክርስትናንን ተምሮ ተጠመቀ። ከዚህ በኋላ ወደ አንጾኪያ ተመለሰ ፍጥረቱ ልዩ የሆነ ልጅ ወልዳ እቱን አገኛት ከዚህ በፊት ሴት ልጅ ወልዳ ገድላ ደሙን ጠጥታለች ሰይጣን አድሮባታልና በወፍና ከይሲ አምሳልም ይገለጣል በአገር ውስጥም ልጅ በሚወለድ ጊዜ ወደርሱ ወርዳ በሥራይም ገድላ ደሙን ትጠጣለች።
❤ ቅዱስ ሱስንዮስም ይህን በአየ ጊዜ ጦሩን አንስቶ ከልጅዋ ጋራ እኅቱን ገደላት ልጅዋ የሰይጣን ልጅ ነውና ሁለተኛም ሥራየኞች ሲሆኑ ባሏንና የባሏን አባቱን ገደላቸው እነርሱ በሥራያቸው ሰውን እያሳመሙ ይድላሉና።
❤ ከዚህም በኋላ ወደ ኒቆድምያ ተመለሰ ወደዚያ ወደ አጠመቀው ቄስ ደርሶ ያደረገውን ሁሉ ነገረው። ወደ አገሩ አንጾኪያም በተመለሰም ጊዜ ከእርሱ የሆነውን አባቱ ሱሲ አወቀ መገደሉንም ወዶ ከንጉሥ ዘንድ ነገር ሠራበት። ያንጊዜም ቅዱስ ሱስንዮስ ወደ ጣዖታት ቤት ሒዶ ወደ ሲዖል ይወልዱ ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አዘዘቸው ያን ጊዜም ምድር አፋን ከፍታ ዋጠቻቸው። አባቱ ዳግመኛ በንጉሡ ዘንድ ከሰሰው ታላቅ ሥቃይም ያሰቃዩት ዘንድ ንጉሥ አዘዘ በብረት ዘንጎችም ደበደቡት፣ በመንኰራኵር አበራዩት፣ በመዶሻም ቀጥቅጠው ሁለተኛ ደግሞ እህል በሚያበራዩበት መሳርያ አበራዩት፣ ከዚያም በከተማ ውስጥ ጎተቱት የክብር ባለቤት ጌታችንም ያጸናውና በስቃዩም ውስጥ ያስታግሰዋል ከቊስሉም የሚፈውሰውን መልአኩንም ልኮ ያለምንም ጉዳት አነሳው ብዙ ሰዎችም አይተው በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምነው በእርሱ ምክንያት ሰማዕት ሆኑ። ንጉሡም ከማሠቃየት በደከመ ጊዜ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለ። በሥቃዩም ወራት በሰማዕትነት የሞቱት ቊጥራቸው አንድ ሺህ አንድ መቶ ዘጠኝ ሆነ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ሰማዕታት ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ 26 ስንክሳር።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ሚያዝያ ፳፭ (25) ቀን።
❤ እንኳን በጡቶቿ ደም ልጆቿን ላጠመቀች #ለቅድስት_ሣራና_ከሁለት+ልጆቿ ጋራ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍት በዓላቸው እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ #ከባሕታዊ_አባ_በብኑዳ፣ ከተጋዳዩ #ቅዱስ_ቴዎድሮስ_ከአባ ዮሐንስ ሊቀ ጳጳሳት በፋርስ መከራን ከመቶ ሰማዕታትና #ከዶራም ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅድስት_ሣራና_ሁለት_ልጆቿ፦ ይቺም ቅድስት ከአንጾኪያ አገር ናት እርስዋም ከዲዮቅልጥያኖስ መኳንንት ለአንዱ ስሙ ስቅራጥስ ለሚባል ሚስቱ ናት እርሱም በፊት ክርስቲያን ነበረ በኋላ ንጉሡን በመፍራት ካደ እርስዋ ግን በክርስትናዋ ጸንታ ኖረች። ባልዋ ስቅራጥስም "እኔ የክርስቲያንን ሃይማኖት እወዳለሁ የንጉሡን ሥቃይ ከመፍራት በቀር ክርስቶስን በልቤ አልካድኩትም" ይላት ነበር። እንደዚህም ስትኖር ሁለት ልጆችንም ወለደች በአንጾኪያም አገር የክርስትና ጥምቀትን ልታስጠምቃቸው አልተቻላትም። አብያተ ክርስቲያናት ተዘግተዋልና ጠፍተዋልምና ሰውን ወዳድ ክርስቶስን ብዙ ስለመውደዷ ልጆቿን ታስጠምቃቸው ዘንድ ታላቅ ተጋድ አደረች ወደ እስክንድርያ ወደ ሊቀ ጳጳሳት አባ ጴጥሮስ ልትሔድ ወዳ አሽከሮቿን አስከትላ ሁለቱን ልጆቿን ይዛ በመርከብ ተሳፈረች።
❤ የክብር ባለቤት ጌታችንም የሃይማኖቷን ልዕልና ለመጪው ትውልድ ሊገልጥ ወዶ ያቺ መርከብ ለመሥጠም እስከምትደርስ በባሕር መካከል ጥልቅ ነፋስን አስነሣ። ይቺ ቅድስትም ልጆቿ ሳይጠመቁ እንዳይሞቱ ፈራች ተነሥታም ጸለየች ከዚያም ምላጭ አንሥታ ጡቷን የቀኙን በጣች ከደሟም ወስዳ ፊታቸውን በመስቀል ምልክት ቀባች በደረታቸውና በጀርባቸውም ላይ እንዲሁ አደረገች በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስም ስም በባሕሩ ውስጥ አጠመቀቻቸው ያን ጊዜም ታላቅ ጸጥታ ሆነ።
❤ ወደ እስክንድርያ አገርም በደረሰች ጊዜ ከአገር ልጆች ጋራ ያጠምቃቸው ዘንድ ወደ ሊቀ ጳጳሳት አባ ጴጥሮስ ልጆቿን አቀረበች በዚያን ጊዜም ከአገር ልጆች አጠመቀ። ወደልጆቿም ደርሶ ሊአጠምቃቸው ወሰዳቸው ያን ጊዜ ውኃው ረጋ እነርሱን ትቶ ከአገር ልጆች አጠመቀ ውኃውም ተፈትቶ ወረደ ደግሞ ሊአጠምቃቸው ወደ ልጆቿ ተመለሰ አሁንም እንደቀድሞው ውኃው ረጋ እንዲሁም ሦስት ጊዜ አደረገ ውኃውም ይረጋል አደነቀ። እናታቸውን አቅርቦ ጠየቃት እርሷም የሆነውን "በባሕር መካከል ዐውሎ ነፋስ እንደተነሣባት ጡቷን በጥታ ደሟን እንደ ቀባቻቸውና በባሕር ውስጥ እንዳጠመቀቻቸው ነገረችው ስለ አደረገችውም በድፍረት በፊቱ ሰግዳ ይቅር ይላት ዘንድ ለመነችው"። አባ ጴጥሮስም " ሴትዮ አትፍሪ ሃይማኖትሽ ፍጹም ነው አንቺ በባሕር ውስጥ በአጠመቅሻቸው ጊዜ በመለኮታዊት እጁ ያጠመቃቸው ባለቤቱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነውና አይዞሽ" አላት። ማጥመቁን በፈጸመ ጊዜ ሥጋውን ደሙን አቀበላቸው።
❤ ይቺም ቅድስት ወደ አንጾኪያ ቤቷ ተመለሰች። ባሏም በአያት ጊዜ ይህን በማድረጓ ተቆጥቶ ወደ ንጉሡ ሒዶ ከሰሳት ያደረገችውንም ነገረው። ንጉሡም ወደርሱ ያቀርቧት ዘንድ አዘዘ ስትቀርብም ወደ "እስክንድርያ ለምን ሔድሽ ከክርስቲያን ወገኖች ጋራ ልታመነዝሪ ነውን" አላት። እርሷም እንዲህ ብላ መለሰችለት "ክርስቲያኖች አያመነዝሩም እንደናንተ የረከሰ ጣዖትን አያመልኩም ከእንግዲህ ደግሞ ከእኔ ቃልን አትሰማም የወደድከውን አድርግ" ሁለተኛም "በእስክንድርያ ካንቺ የሆነውን ንገሪኝ ብሎ ጠየቃት ምንም ምን አልመለሰችለትም።
❤ ንጉሥ ከዲዮቅልጥያኖስም እጆቿን የኋሊት አሥረው ሁለቱን ልጆቿን በሆድዋ ላይ አድርገው ሦስቱንም በእሳት ያቃጥሉአቸው ዘንድ አዘዘ። ፊቷንም ወደ ምሥራቅ መልሳ ወደ ክብር ባለቤት ጌታችን ጸለየች ከዚያም ከልጆቿ ጋራ ሚያዝያ25 አቃጠሉዋት የድልና የሕይወት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለች። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቷ ለዘላለም ይማረን አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ 25 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለሣራ_እምሥርወ_ክርስቲያን_ሙላዳ። ብእሲሃ ዕልው ሶበ ዐውደ ምኵናን ወሰዳ። እምሰሚዐ ቃሉ ርኵስ ሶበ ኢትሠጥወቶ ለአግሪጳዳ። አዘዘ ያውዕይዋ ለእቶነ እሳት በነዳ። አንቢሮሙ በከርሣ ፪ተ ውሉዳ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_25።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወአምላክነሂ መስተሣህል። የዐቅብ ሕፃናት እግዚአብሔር። ተመንደብኩሂ ወአያድኃነኒ"። መዝ 114፥5-6። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 10፥12-22፣ 1ኛ ዮሐ 4፥4-18፣ የሐዋ ሥራ 8፥1-13። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 18፥1-8። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ወይም የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ቅዳሴ ነው። መልካም የበዓለ ሃምሳ ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
+3
#EOTC
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር)፣ ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሎስ (ዶ/ር) እና ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ለመገኘት እንዲችሉ መንግሥት የሚጠበቅበትን ሁሉ እንደሚያደርግ አሳወቀ።
መንግሥት ዛሬ ምሽት ባወጣው መግለጫ ፥ " ከዚህ በፊት አንዳንድ ወገኖች በፈጠሩት ችግር የተነሣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ ጉባኤ ለመሳተፍ ላልቻሉ ሦስት አባቶች ሁኔታዎች መመቻቸታቸውን አሳውቃለሁ " ብሏል።
በመግለጫው ፤ ሀገራዊ ተቋማት ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ያላቸውን የላቀ ሚና በመረዳት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አባቶች መካከል የተፈጠረው መለያየት እንዲፈታ የመሪነቱን ሚና መጫወቱን አስታውሷል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በሀገር ግንባታ የነበራትንና የሚኖራትን ሚና በመገንዘብ አስፈላጊውን ድጋፍ ሲሰጥ መቆየቱን በዚህ አቋሙም እንደሚቀጥል ገልጿል።
" ይሄንን ያልተረዱ አንዳንድ አካላት ችግሮችን ፈጥረው የነበረ ቢሆንም እንኳን፣ መንግሥት ለቤተ ክርስቲያንዋ እና ለምእመንዋ ሲል በሆደ ሰፊነት ለማለፍ ወስኗል " ብሏል።
መግለጫው " አንዳንድ አካላት " ያላቸውን እና የፈጠሩትን ችግሮች በግልጽ ያላብራራ ቢሆንም ችግሩ እንዲፈታ ሲኖዶሱ ጥያቄ ማቅረቡንና ይህንንም ጥያቄ መቀበሉን ይፋ አድርጓል።
" በሂደቱም ተቀራርቦ መነጋገር ከሁሉም የተሻለ የመፍትሔ መንገድ መሆኑ ታይቷል " ብሏል።
ሲኖዶሱ መንግሥት ነገሩን በሆደ ሰፊነት እንዲመለከተው እንደጠየቀና በዚህም ሶስቱ ብፁአን አባቶች ወደ ሀገራቸው ገብተው በቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ለመገኘት እንዲችሉ የሚጠበቅበትን ሁሉ እንደሚያደርግ አሳውቋል።
✝️ #ቋሚ_ሲኖዶስ_የብፁዕ_አቡነ_ገብርኤል ጉዳይ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ ብፁዕነታቸው በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በተአቅቦ እንዲቆዩ ውሳኔ አሳለፈ!
✝️ ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ከቤተክርስቲያናችን የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ በፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር አዳራሽ የሰጡትን ትምህርትና በማኅበሩ ሚዲያ የተላለፈበትን ሁኔታ በተመለከተ #በዛሬው_ሚያዚያ_22_ቀን_2017 ዓ.ም መደበኛ ጉባኤው በሰፊው ተወያይቶ ለመወሰን በያዘው ቀጠሮ መሰረት በጉዳዩ ዙሪያ ጥልቅ ውይይት ካደረገ በኋላ የሚከተሉትን ውሳኔዎችን አስተላልፏል።
1. ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር በተለያዩ ጊዜያት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ውጪ በሚዲያው ያስተላለፈው የስሕተት ትምህርት የቤተክርስቲያናችንን አባቶች፣ሊቃውንቱንና መላው ሕዝበ ክርስቲያኑን ያሳዘነ በመሆኑ በማህበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ በኩል ጊዜያዊ የእገዳ ደብዳቤ እንዲደርሰው እና በመምሪያው በኩል አስፈላጊው ጥብቅ ክትትል እንዲደረግ ሆኖ በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ መስጠት ይቻል ዘንድ አምስት አባላት ያሉት ኮሚቴ እንዲቋቋም አድርጓል።
በዚህም መሰረት ቋማ ሲኖዶስ ያቋቋማቸው አጣሪ ልዑካን አጠቃላይ የማህበሩን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ እና በሚዲያው ያስተላለፋቸውን የስህተት ትምህርቶች በተመለከተ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እና ከማህበራት ምዝገባ፣ ቁጥጥርና ክትትል መምሪያ ጋር በመነጋገር በሚገባ መርምርውና አጣርተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርቡ፣
2. ብፁዕ አቡነ ገብርኤል “ማርያም ቤዛዊተ ዓለም” አትባልም በማለት ከቤተ ክርስቲያናችን የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ የሰጡት ሕጸጽ ያለበት ትምህርት በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚገባ ተመርምሮና ተጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ በአስቸኳይ እንዲቀርብ ብፁዕነታቸውም ጉዳዩ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በተአቅቦ እንዲቆዩ፣
3. ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት እና ብፁዕ አቡነ በርናባስ የደቡብ ካሊፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ያስተላለፏቸው የስሕተት ትምህርቶችና በሌሎችም መምህራን የተላለፉ ነቀፋ ያለባቸው ትምህርቶች ካሉ የሊቃውንት ጉባኤ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ አንጻር በሚገባ መርምሮና አጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጭምር በአጭር ጊዜ ውስጥ ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርብ፣
4. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መገናኝ ብዙኃን ስርጭት ድርጅት ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር ሚዲያ የአየር ሰዓት የሰጠበትን ዝርዝር ሁኔታና ከማኅበሩ ጋር በተያያዘ አየር ላይ ያዋላቸውን ትምህርቶች የሚያሳይ ሪፖርት እንዲያቀርብ ይደረግ በማለት ቋሚ ሲኖዶስ ወስኖ የዕለቱን ጉባኤ በቅዱስነታቸው ጸሎተ ቡራኬ አጠናቋል። መረጃው፦ የሕዝብ ግንኙነት ነው።
❤ በዚያም ጊዜ ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሥራ ነገሥታቱ ሁሉም ደነገጡ ኀፍረት ደግሞ እንዳይጨምርባቸው ከእርሱም እንዲአርፍ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ እንዲጽፍ ንጉሥ ዱድያኖስን መከሩት። ያን ጊዜም የክብር ቅዱስ ጊዮርጊስን ራስ በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ድል አድራጊ ቅዱስ ጊዮርጊስም እጅግ ደስ አለው እሳት ከሰማይ አውርዶ ሰባውን ነገሥታትን ያቃጥላቸው ዘንድ መከራውም ከክርስቲያን ወገን ጸጥ ይል ዘንድ ጌታችንን ለመነው። ወዲያው እሳት ወርዶ ከሠራዊታቸው ጋራ ሰባውን ነገሥታት አቃጠላቸው።
❤ ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተገልጾ ብዙ ቃል ኪዳን ሰጠው። በምድር መታሰቢያህን ለሚያደርግ ሁሉ እኔ ኃጢአቱን ሁሉ እደመስሳለሁ በመከራም ውስጥ ሁኖ በባሕርም ሆነ፣ በየብስ ወይም በደዌ በስምህ የሚለምነኝን እኔ ፈጥኜ ከመከራው አድነዋለሁ ይህንንም ጌታችን ተናግሮ በክብር ወደ ሰማይ ወጣ።
❤ ከዚህም በኋላ ወታደሮቹ የቅዱሳን የከበረች ራሱን ቈረጡት ደም፣ ውኃና ወተት ፈሰሰው፤ ጌታም ቅዱስ ሚካኤልን በብርሃን ልብስ ደሙን እንዲቀበለው አዘዘ። ጌታችንም የኃያሉ የቅዱስ ጊዮርጊስን ነፍስ በእጁ ተቀብሎ ሳማት፤ በሰማያዊ ልብስም አጐናጥፎ ከእርሱ ጋራ ወደ ሰማይ አሳረጋት። አየር በሙሉ ቅዱሳን መላእክትን ተሞላ። ለቸር አባቱና ለመንፈስ ቅዱስ ቊርባን አድርጎ እስኪያቀርበው ድረስ ቅዱሳን ሁሉ በየወገናቸው ያመሰግኑ ነበር። የብርሃን ልብስ አለበሰው። በዕንቈ ባሕርይ ያጌጠ ከጽሩ ወርቅ የተሠሩ መከራ በተቀበለባቸው ሰባት ዓመታት ልክ ከዕፀ ሕይወት አበቦች የተሠሩ አክሊሎች ያሉበትን ዘውድ አቀዳጀው ለዘላለም ከማኅበረ በኵር ጋራ ስሙን ጻፈው። ሰማያውያን መላእክትና ቅዱሳንንም ሁሉ በየወገናቸው በመንበሩ ላይ እንዲአስቀምጡት፤ በኢየሩሳሌም ሰማያዊት በዓል እንዲ ያደርጉለት አዘዛቸው።
❤ ከዚህም በኋላ ከመብረቁ፣ ከነጐድጓድ፣ ከንውጽውጽታው ጽናት፣ ከዝናሙ ብዛት የተነሳ በምድር ላይ ትልቅ ድንጋፄ ሆነ። ምድርም ሦስት ጊዜ ተናወጸች ከዚያ ቆመው የነበሩ ሰዎች ሁሉ ሸሹ ወደ ከተማም ሔዱ ጭፍሮችም ይህንን በአዩ ጊዜ በቅዱስ ጊዮርጊስ አምላክ አመኑ። ነፍሱም ወደ ሰማይ በዐረገች ጊዜ በእግዚአብሔር ፊት ሰገደች። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የምታምን ነፍስ ከሥጋዋ በተለየች ጊዜ አስቀድሞ ለሥሉስ ቅዱስ ትስገድ ከዚህ በኋላ ወደ ወዳጄ ወደ ጊዮርጊስ ይወሰዷት እና ለርሱ እጅ ትንሣ ብሎ አዘዘ፤ በዚህ ሁኔታ የቅዱስ ጊዮርጊስ ምስክርነቱ ሚያዝያ በባተ በሃያ ሦስት ቀን በዕተ ዓርብ ዘጠኝ ሰዓት ተፈጸመ። አገልጋዮቹም ሥጋውን ወስደው በልብስ ጠቀለሉት ወደ ሀገሩ ልዳም ወስደው ቤተክርስቲያን ሰርተው በውስጡ አኖሩት፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን የቅዱስ ጊዮርጊስም በረከትቱ ረድኤቱ ሁላችን የክርስቲያን ወገኖችን ከሥጋና ከነፍስ መከራ ይጠብቀን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ ገድለ ጊዮርጊስ እና የሚያዚያ 23 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_ሮቆ፦ በአንዲት ዕለትም በጸሎት ቁሞ ሳለ የንዳድ ትንኝ ነደፈው ቊስሉን እያሳየ በብዙ ልቅሶ ወደ ጌታችን ለመነ። ያን ጊዜም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደመና ላይ ተገለጠለት በአንጻሩም ቁሞ "ወዳጄ ሮቆ አትፍራ ላድንህ ወደ አንተ መጥቻለሁና ደግሞም የሮቆ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ከንዳድ በሽታ አድነኝ ብሎ በስምህ ለሚለምነኝ የንዳድ በሽታ በላዩ ላላመጣበት ከአንተ ጋራ ቃል ኪዳንን ላጸና መጣሁ" አለው። ይህንንም ብሎ በታላቅ ክብር ወደ ሰማያት ዐረገ።
❤ ቅዱስ ሮቆም በብዙ ገድል ተጠምዶ ኑሮ ሚያዝያ23 በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ጻድቅ ልመና ይማረን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ 23 ስንክሳር።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ይቀጠቅጦሙ ለነገሥት በዕለተ መዐቱ። ወይኴንኖሙ ለአሕዛብ ወያበዝኅ አብድንተ። ወይሰብር አርእስተ ብዙኃን በዲበ ምድር"። መዝ 109፥5-6። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 12፥1-12።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #ዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወይርአዩ አሕዛብ በቅድመ አይንቲነ። በቀለ ደሞሙ ለአግብርቲከ ዘተክዕወ። ይባእ ቅድሜከ ገዓሮሙ ለሙቁሓን"። መዝ 78፥10-11። የሚነበቡት መልዕክታት 2ቆሮ 1፥1-12፣ 1ኛ ጴጥ 1፥6-10 እና የሐዋ ሥራ 14፥1-23። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥16-34። የሚቀደሰው የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ወይም የቅዱስ ዲዮስቆሮ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ጊዮርጊስ የዕረፍት በዐልና የበዐለ ሃምሳ ሶሞን። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ሚያዝያ ፳፫ (23) ቀን።
❤ እንኳን ፀሐይና የአጥብያ ኮከብ ለተባለ #ለፀሐየ_ልዳ_ለኮከበ_ፋርስ ለታላቁና ክቡር ለሆነ #ለሰማዕታት_አለቃ_ለቅዱስ_ጊዮርጊስ ለምስክርነቱ (ለዕረፍቱ) ፍፃሜ ለ1713ኛ ዓመታዊ መታሰቢያ በዓልና ስሙን ለጠራ ጌታችን በንዳድ (በወባ) በሽታ የተያዛ ሰው እንደሚያድነው ቃልኪዳን ለገባለት ተአምራት እሰከ አሳየ ድረስ ለተጋደለ #ቅዱስ_ሮቆ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #ሊቀ_ሰማዕታት_ቅዱስ_ጊዮርጊስ፦ የዚህም ቅዱስ አባቱ መስፍን ነው ስሙም አንስጣስዮስ ይባላል ከቀጰዶቅያ አገር ነው የእናቱም ስም ቴዎብስታ ይባላል ከፍስጥዓዔም አገር ናት ታናሽ ሆኖ ሳለ አባቱ ዐረፈ። ሃያ ዓመትም በሆነው ጊዜ የአባቱን ሹመት ሊቀበል ወደ ንጉሥ ዱድያኖስ ዘንድ ሔደ። ንጉሡም ጣዖት አቁሞ ጣዖትን እንዲአመልኩ ሰዎችን ሁሉ ሲያስገድዳቸው አገኘው። ይህንንም አይቶ ቅዱስ ጊዮርጊስ እጅግ አዘነ በእርሱ ዘንድ ያለውን ገንዘቡን ሁሉ ለድኆች ለምስኪኖች ሰጠ ባሮቹንም ነፃ አወጣቸው።
❤ ከዚህ በኋላ በንጉሥ ፊት ቁሞ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ። ንጉሡም አባበለው ብዙ ቃል ኪዳንም ገባለት እርሱ ግን አልተቀበለውም። ለመስማት እንኳ የሚያስጨንቅ ሥቃይን አሠቃየው ጌታችን ግን ያጸናዋል ቊስሉንም ያድነዋል ሦስት ጊዜም እንደ ሚሞት እርሱም እንደሚአስነሣው በአራተኛውም የምስክርነት አክሊል እንደሚቀበል ነገረው። ቃል ኪዳንም ሰጠው ስሙ በዓለሙ ሁሉ የተገለጠ ይሆን ዘንድ በተጋድሎና መከራ በመቀበልም ጽኑዕ በሆነ ሥቃይም ሰባት ዓመት እንደሚኖር መላእክትም እንደሚአገለግሉት ነገረው።
❤ ንጉሡም ቅዱስ ጊዮርጊስ ባለመታዘዙና ባለመመለሱ እጅግ አዘነ ስለዚህም አትናስዮስ የሚባል ታላቅ ሥራየኛ አመጣ እርሱም መርዝን ቀምሞ በጽዋ መልቶ አስማት ደግሞ እንዲጠጣ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሰጠው። ወዲያውኑ የሚሞት መስሎት ነበር። ቅዱሱም ያንን ጽዋ በመስቀል መልክት አማትቦ ጠጣው ምንም ጉዳት አልደረሰበትም። ያ መሠርይም በክብር ባለቤት በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ በሰማዕትነት ሞተ። ከእርሱ ጋራ ሌሎች ብዙዎች ሰዎች በሰማዕትነት ሙተው የሕይወት አክሊል ተቀበሉ ቊጥራቸውም ሠላሳ ሺህ ሰባት መቶ ነፍስ ነው።
❤ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዱድያኖስና በሰባ ነገሥታት ፊት በቆመ ጊዜ በዚያም የተቀመጡባቸው የዕንጨት ወንበሮች ነበሩ። ቅዱሱንም "እሊህን የተቀመጥንባቸውን ወንበሮች እንዲበቅሉ እንዲአብቡና እንዲአፈሩ ታደርጋቸው ዘንድ ከአንተ እንሻለን" አሉት። በዚያን ጊዜ ጸለየ እንዳሉትም አደረጋቸው ይህንንም ድንቅ ሥራ አይተው ቊጥር የሌላቸው ብዙ አሕዛብ በጌታችን አመኑ።
❤ ከዚህም በኋላ ቅዱሱን ወስደው በጐድጓዳ ብረት ምጣድ ውስጥ አበሰሉት። አቃጥለው አሳርረው ሥጋውንና ዐጥንቱን ፈጭተው አመድ አድርገው ከረጅም ይድራስ ከተባለ ተራራላይ በተኑት። ጌታችንም ነፍሱን ወደ ሥጋው መልሷት ደግሞ አስነሣው። ወደ ነገሥታቱም ተመልሶ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ስም ሰበከ። ቊጥር የሌላቸው አሕዛብ አይተው አደነቁ በጌታችንም አምነው በሰማዕትነት ሞቱ።
❤ ነገሥታቱም ደግመው ሙታኖችን ብታስነሳ አምላክህ ዕውነተኛ አምላክ እንደሆነ እናውቃለን በእርሱም እናምናለን" አሉት። ቅዱሱም ጸለየ ከመቃብር ጒድጓድም ውስጥ ወንዶችና ሴቶችን ጐልማሶችንም አስነሣላቸው እነዚያም በክብር ባለቤት በጌታችን ስም አስተማሩ የገሀነምንም ወሬ ተናገሩ ጥምቀትንም ተቀብለው ተመልሰው ዐረፉ። ከሀድያን ነገሥታት ግን ሙታንን ያስነሣህ አይደለም የረቀቁ ሰይጣናትን አሳየህ እንጂ ብለው ተከራከሩ። ከዚያም ከጭንቀታቸው ብዛት የተነሣ ከአንዲት ድኃ ሴት ዘንድ አስጠበቁት እርሷም እንጀራ ልትለምንለት ወጣች የእግዚአብሔርም መልአክ በላዩ ከበጎ ነገር ሁሉ የተመላ ማዕድን አቀረበለት። የዚያች መበለትም ቤቷ ምሰሶ ቅርጫፍን አበቀለ ታላቅ ዛፍም ሆነ። ያቺም መበለት በተመሰለች ጊዜ የቤቷ ምሰሶ ቅርንጫፍ አብቅሎ ታላቅ ዛፍ እንደሆነ ስለ ማዕዱም ይህን ታላቅ ምልክት አይታ "የክርስቲያኖች አምላክ ሰው ተመስሎ ወደእኔ መጣ" አለች። ቅዱሱም "እኔ አምላክ አይደለሁም የአምላክ ባሪያ ነኝ እንጂ" አላት። እርሷም እንዲህ ብላ ለመነችው "የአምላክ አገልጋይ ከሆንክ ቸርነትህ እንድትደርሰኝ እለምንሃለሁ። ዕውር፣ ደንቆሮ፣ ዲዳ፣ ጐባጣ የሆነ ልጅ አለኝና ታድንልኝ ዘንድ እለምህሃለሁ"። ስለ ጌታችን እምነትም አስተማራትና በመስቀል ምልክት አማተበው ያንጊዜም አየ። ቅዱስም "በሌላ ጊዜ እንዲሰማ እንዲናገርና እንዲሔድ እንዲአገለግለኝም እኔ እሻለሁ" አላት። በዚያን ጊዜ ንጉሡ በአገሩ ሜዳ ውስጥ ሲዘዋወር ያቺን ዛፍ አይቶ አደነቀ ስለ እርሷም ጠየቀ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከእርሷ ዘንድ የተቀመጠባት የዚያች መበለት የቤቷ ምሰሶ እንደሆነ ነገሩት። ንጉሡም ተቆጣ ቅዱሱንም ከዚያ ወስዶ አስገረፈው በመንኰራኵር አበራዩት ሙቶም በከተማ ውጭ ጣሉት ጌታም ከሞት አስነሣው ወደ ነገሥታቱም ተመለሰ ንጉሡም አይቶ ደነገጠ ስለ ሕይወቱም አደነቀ።
❤ ከዚህም በኋላ ይሸነግለው ዘንድ ጀመረ በመንግሥቱ ላይም ሁለተኛ ያደርገው ዘንድ ቃል ገባለት ቅዱስ ጊዮርጊስም እየዘበተበት "ነገ በጥዋት ለአማልክቶችህ መሥዋዕትን አቀርባለሁ አንተም ሕዝቡ እንዲሰበሰቡ እዘዝ እኔ ስሠዋ እንዲአዩ" አለው። ንጉሡም ዕውነት የሚሠዋ መስሎት ደስ አለው ወደ ቤተ መንግሥቱም እልፍኝ አስገብቶ አሳደረው። ለጸሎትም ተነሣ የዳዊትንም መዝሙር አነበበ የዱድያኖስ ሚስቱ እለእስክንድርያ ንግሥት ሰምታ ቃሉ ደስ አሰኛት የሚያነበውንም ይተረጒምላት ዘንድ ለመነችው እርሱም እግዚአብሔር ዓለምን ከፈጠረበት ሰው እንደሆነበት ጊዜ የሆነውን ሁሉ ሊያስረዳትና ሊያስገነዝባት ጀምረ ትምህርቱም በልቡዋ ተቀርጾ በክብር ባለቤት በጌታችን አመነች።
❤ በማግሥቱም ቅዱስ ጊዮርጊስ ለአማልክት ሲሠዋ ለማየት ሰው ሁሉ እንዲሰበሰብ ዐዋጅ ነጋሪ ዞረ የቤቷን ምሰሶ ያበቀለላት ያቺ መበለት ሰምታ ዕውነት መስሏት እጅግ እያዘነች ልጅዋን ተሸክማ እያለቀሰችም ወጣች።
❤ ቅዱስ ጊዮርጊስ በአያት ጊዜ ፈገግ አለ "ልጅሽን በምድር ላይ አኑሪው" አላት ከዚያም ልጅዋን ጠርቶ "ወደ አጵሎን ሒድ ወደእኔም ይመጣ ዘንድ በክብር ባለቤት በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም እዘዘው" አለው። ያን ጊዜ ያ ልጅ ድኖ ቅዱስ ጊዮርጊስ እንዳዘዘው ወደ ጣዖቱ ቦታ ሒዶ አዘዘው። በጣዖቱ ያደረ ያ ርኵስ መንፈስም ከማደሪያው ወጥቶ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ አለበት መጥቶ "እኔ ሰውን ሁሉ የማስት እንጂ አምላክ አይደለሁም" ብሎ በሕዝቡ ሁሉ ፊት አመነ። ቅዱሱም ትውጠው ዘንድ ምድርን አዘዛትና ወዲያውኑ ዋጠችው ጣዖታቱም ከአገልጋዮቻቸው ጋራ አጠፋቸው ከወገኖቹ ጋራ ዐፈረ። ብስጭትና ቁጣንም እንደተመላ ወደ ንግሥት ሚስቱ ዘንድ ገባ። እርሷም "አምላካቸው ጽኑዕና ኃያል ነውና ክርስቲያኖች አትጣላቸው አላልኩህምን" አለችው። ይህንንም ከእርስዋ ሰምቶ በእርሷ ላይ እጅ ተቆጣ ወደ ክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስ እምነት ቅዱስ ጊዮርጊስ እንደአስገባት አወቀ። ከዚህም በኋላ ከከተማ ውጭ እንዲጐትቷትና በመጋዝም እንዲሰነጥቋት አዘዘ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለች።
