Official wz ba
Hy gυyz нow are υ ιғ υ joιn тнιѕ cнannel υ geт poeм📝 мυѕιc🎧 pιc🃏 qυoтeѕ & вιllвoard мυѕιc wнaт do υ eхpecт тнιѕ ιѕ @cukurfam Bay the way Don't expect anything from anyone Expectation is always hurt 😭4any coммenт @nipsay1421
إظهار المزيدلم يتم تحديد البلدلم يتم تحديد اللغةالفئة غير محددة
179
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
معدل نمو المشترك
جاري تحميل البيانات...
😘 ያበደው ፍቅሬ 😘
ክፍል 9⃣
አንዳንዶች ለወደዱት ብቻ ጥሩ ይሆናሉ.... አንዳንዶች ደግሞ እንዲሁ በተፈጥሯቸው ጥሩነትን ይታደሉታል። ቢኒ እንደዛ ነው መልካምነትን የታደለ ጥሩ ልብ ያለው ልጅ ነው። ድሀ ወይም ሀብታም፣ ክርስቲያን ሙስሊም ወይም ሌላ እምነት፣ ቆንጆ ወይም መልከ ጥፉ፣ ቢኒ ጋር መስፈርት አይደሉም። ለሁሉም እኩል ፍቅርና እንክብካቤ ሲሰጥ ታዩታላችሁ..... ግቢ ውስጥም ሆነ ከተማ ውስጥ ያሉ የበጎ አድራጎት ስራዎች አያመልጡትም.....
"ቢኒዬ ግን እርግጠኛ ነህ እዚህ ብሆን አረብሽህም.." እረጅም ሰዓት ተጨቃጭቀን እስከፈለኩ ድረስ ቤቱ እንድኖር ከነገረኝ በኋላ ሀሳቡን ቢቀይር ብዬ ጠየኩት
አጠገቤ መጣና ቁጭ አለ.... እጆቹን ልኮ ሁለት እጆቼን ያዘና አይን አይኔን እያዬ "ሩቴ አንቺ ጓደኛዬ ነሽ... ጓደኝነት ውስጥ ደግሞ እኔ የሚባል ነገር የለም በተለይ እኔ ካንቺ እኔን ላስቀድም አልችልም ምክንያቱም......" ከንፈሮቹ ተንቀጠቀጡ።
"ምክንያቱም ምን ቢኒዬ" እጄን ለቆ ተነሳና ጀርባውን ሰቶኝ ከመስኮት ዳር ቆመ።
"ሩት ጊዜ የነገሮች ጌታ ነው ብዬ አምናለሁ... እናም ሁሉም በጊዜው ሲሆን ደስ ይላል። አሁን ከኔ ምክንያት በላይ ያንቺ ሁኔታዎች ናቸው መስተካከል ያለባቸው...." ክትክት ብዬ ሳቅሁ... የእብደት ሳቅ
ከሳቄ በኋላ
" እስኪ ንገረኝ ምኑን ነው የምታስተካክለው.... እናቴን ልጄን ወይስ ከሀዲው ባሌን ማንን መልሰህ ልታመጣልኝ የምትችል ይመስልሀል..." ድጋሚ አመመኝ... መቋቋም አቃተኝ... በሁለት እጄ ጭንቅላቴን ጥፍንግ አድርጌ ያዝኩት። የሆነ ሽክርክሪት ውስጥ እንዳለሁ ይሰማኛል ዥውውውውውውውው.... ሳቅ ከዛ ደግሞ ዝምምምምታ.... ከዛ ደግሞ ሌላ ሳቅ.... ይሄኛው አለም የተሻለ ይመስለኛል።
የሆነ ሰው አፌ ውስጥ የሆነ ነገር ለማስገባት ታገለኝ አልከለከልኩትም ዋጥኩት ከዛ ሁሉም ነገር ፀጥ አለ።
ምን ሰዓት እንደተኛሁ ባላውቅም ራሴን ጋቢ ለብሼ ሶፋ ላይ ተኝቼ አገኘሁት። ቀና ብዬ ተስተካክዬ ቁጭ ስል ቢኒን ከእግሬ ስር ቁጭ ብሎ መፅሀፍ ቅዱስ ሲያነብ አየሁት።
"ይቅርታ ቢኒ ረበሽኩህ መሰለኝ.." መፅሀፍ ቅዱሱን ዘግቶ ከሳመ በኋላ የኔንም ግንባር ነካ አደረገበትና ተነስቶ አስቀምጦ ተመለሰ።
"ሁለተኛ እንደዚህ እንዳትይኝ ማስቸገር ገለመሌ የሚባል ታሪክ የለም ያራቅሺኝ ነው የሚመስለኝ..."
"እሺ በቃ አይለመደኝም..... ይልቅ እስኪ ንገረኝ የውጪ ቆይታህ እንዴት ነበር የተመለስከውስ መች ነው"
"ቆይታዬን በደፈናው ጥሩ ነበር ልበልሽ መሰለኝ። የተመለስኩት ሁለት ወር አካባቢ ሆነኝ ግን ቀጥታ ቤተሰብ ጋር ክፍለ ሀገር ነው የሄድኩት ከተመለስኩ ገና ሳምንትም አልሞላኝ"
"እና ለምን ልትፈልገኝ ወደ ቤት አልመጣህም..." ክፍት ነው ያለኝ ምንም እንኳን የሱን ስም ሲሰማ ባሌ ቢናደድም ቢኒ ላጣው የማልፈልገው ጓደኛዬ ነው እና እንዴት...
"ወዳንቺ ጋር እየመጣሁ እያለ እኮ ነው መኪና ውስጥ የገባሽብኝ"
"ኦ እሺ እንደዛ ከሆነ"
"አልተዋጠልሽም አይደል ሩቴ ብዙ ጊዜ እንዳልደወልኩልሽ አውቃ..." አቋረጥኩት
"ምን ብዙ ጊዜ ትላለህ ከሄድክ ጀምሮ ሁለቴ ብቻ እኮ ነው የደወልከው.... እናም አልዋሽህም ተቀይሜሀለሁ"
"ምክንያቴን ስታውቂ እንደምትረጂኝ ስለማውቅ ችግር የለውም.... የሆነ ነገር መብላት አለብን ምን ትፈልጊያለሽ..." አለኝ ወደ ኪቺን እየገባ
"ፍላጎትሽን አትናገሪም ካለዛ ዱባ ወጥ ነው የምሰራው ሀ ሀ ሀ" ሽርጡን አገልድሞ ብቅ አለ
" ዱባ ስራና ሶስት ቀን ውጪ አሳድሬ ነው የማበላህ.... አንተ ደግሞ ሼፍ መስለህ የለም እንዴ"
"ነይ አሁን ተነሺ ቢያንስ ዱባውን እንኳን በመክተፍ አግዢኝ" ከስሙ ጭምር እንደምጠላው ስለሚያውቅ እኮ ነው ...ዱባን....
"ሀ ሀ ሀ አንተ እብድ ትቀልድብኛለህ አ" ከረጅም ጊዜ በኋላ ሳቅሁ
......
፨፨፨ ፨፨፨፨ ፨፨፨፨
ጎንደር ዩንቨርስቲ ሁለተኛ አመት
"ቢኒ ዮናታንን እወደዋለሁ ከዚህ በላይ መቋቋም አልችልም እናም እነግረዋለሁ"
"ሩት ዮናታንን ታውቂዋለሽ.... እሺ አለሽ እንበል ከዛ እነኝህን ሁሉ ሴቶች ትቶ ካንቺ ጋር ብቻ የሚሆን ይመስልሻል"
"አላውቅም ግን እድሌን ልሞክር.."
"ተይ ሩት ይቅርብሽ"
"አይሆንም ቢኒ እድሌን እሞክራለሁ" ይሄን ሁሉ የምንጨቃጨቀው ዮናታን የሚያመሽበት ጭፈራ ቤት በር ላይ ሆነን ነው። ወደ ውስጥ ገባሁ... አይኔን ዞር ዞር እያደረኩ ፈለኩት ጥግ ሶፋ ላይ ከአንዲት ሴት ጋር የተሰፋ ያክል ተጣብቋል.... በደንብ ቀረብኳቸው... አንገቱ ስር ስማው ቀና ስትል አይን ለአይን ተገጣጠምን... የትናዬት....
ደንዝዤ አንደቆምኩ የሆነ ሰው እጅ ትከሻዬ ላይ አረፈ "የኔ ቆንጆ በዛኛው በኩል ቦታ አግኝቻለሁ.... እንሂድ አይደል" ውጪ ቆይ አላልኩትም ነበር.... ቢሆንም ግን ወሳኝ ሰዓት ላይ ነው የደረሰው።
"አየሽ አይደል በራስሽ ላይ ምን እያመጣሽ እንደሆነ"
"ሲጀመር እሱን ብቻውን አገኘዋለሁ ብዬ ማሰቤ ነው የኔ ጥፋት..." እርር ድብን ብሽቅቅቅ ብያለሁ እኮ
✎Share አድርጉ።
ይቀጥላል....
ይ🀄️ላ🀄️ሉN
ይ🀄️ላ🀄️ሉን
@getemberedu
የግዕዝ ቁጥሮችን ከ አንድ እስከ ቢሊዮን እነሆ
★ ቤተክርስቲያን ባህረ ጥበባት★
★ አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት★
አልቦ 0
፩ አሐዱ 1
፪ ክልኤቱ 2
፫ ሠለስቱ 3
፬ አርባዕቱ 4
፭ ሐምስቱ 5
፮ ስድስቱ 6
፯ ስብዓቱ 7
፰ ስመንቱ 8
፱ ተሰዓቱ............. 9
፲ አሠርቱ .............10
፲፩ አሠርቱ ወአሐዱ 11
፲፪ አሠርቱ ወክልኤቱ 12
፲፫ አሠርቱ ወሠለስቱ 13
፲፬ አሠርቱ ወአርባዕቱ 14
፲፭ አሠርቱ ወሐምስቱ 15
፲፮ አሠርቱ ወስድስቱ 16
፲፯ አሠርቱ ወሰብዓቱ 17
፲፰ አሠርቱ ወስመንቱ 18
፲፱ አሠርቱ ወተሰዓቱ 19
፳ እስራ 20
፳፩ እስራ ወአሐዱ 21
፳፪ እስራ ወክልኤቱ 22
፳፫ እስራ ወሠለስቱ 23
፳፬ እስራ ወአርባዕቱ 24
፳፭ እስራ ወሐምስቱ 25
፳፮ እስራ ወስድስቱ 26
፳፯ እስራ ወሰብዓቱ 27
፳፰ እስራ ወሰመንቱ 28
፳፱ እስራ ወተሰዓቱ 29
፴ ሠላሳ 30
፴፩ ሠላሳ ወአሐዱ 31
፴፪ ሠላሳ ወክልኤቱ 32
፴፫ ሠላሳ ወሠለስቱ 33
፴፬ ሠላሳ ወአርባዕቱ 34
፴፭ ሠላሳ ወሐምስቱ 35
፴፮ ሠላሳ ወስድስቱ 36
፴፯ ሠላሳ ወሰብዓቱ 37
፴፰ ሠላሳ ወሰመንቱ 38
፴፱ ሠላሳ ወተሰዓቱ 39
፵ አርብዓ 40
፶ ሃምሳ 50
፷ ስድሳ 60
፸ ሰብዓ 70
፹ ሰማንያ 80
፺ ተሰዓ 90
፻ ምዕት 100
፻፩ ምዕት ወአሐዱ 101
፻፪ ምዕት ወክልኤቱ 102
፻፫ ምዕት ወሠለስቱ 103
፻፬ ምዕት ወአርባዕቱ 104
፻፭ መዕት ወሐምስቱ 105
፻፮ ምዕት ወስድስቱ 106
፻፯ ምዕት ወሰብዓቱ 107
፻፰ ምዕት ወስመንቱ 108
፻፱ ምዕት ወተሰዓቱ 109
፻፲ ምዕት ወአሠርቱ 110
፻፲ወ፩ ምዕት አሠርቱ ወአሐዱ 111
፻፲ወ፪ ምዕት አሠርቱ ወክልኤቱ 112
፻፲ወ፫ ምዕት አሠርቱ ወሠለስቱ 113
፻፲ወ፬ ምዕት አሠርቱ ወአርባዕቱ 114
፻፲ወ፭ ምዕት አሠርቱ ወሐምስቱ 115
፻፲ወ፮ ምዕት አሠርቱ ወስድስቱ 116
፻፲ወ፯ ምዕት አሠርቱ ወሰብዓቱ 117
፻፲ወ፰ ምዕት አሠርቱ ወስመንቱ 118
፻፲ወ፱ ምዕት አሠርቱ ወተሰዓቱ 119
፻፳ ምዕት ወእስራ 120
፻፴ ምዕት ወሠላሳ 130
፻፵ ምዕት ወአርብዓ 140
፻፶ ምዕት ወሃምሳ 150
፻፷ ምዕት ወስድሳ 160
፻፸ ምዕት ወሰብዓ 170
፻፹ ምዕት ወሰማንያ 180
፻፺ ምዕት ወተሰዓ 190
፪፻ ክልኤቱ ምዕት 200
፪፻ወ፩ ክልኤቱ ምዕት ወአሐዱ 201
፪፻ወ፪ ክልኤቱ ምዕት ወክልኤቱ 202
፪፻ወ፫ ክልኤቱ ምዕት ወሠለስቱ 203
፪፻ወ፬ ክልኤቱ ምዕት ወአርባዕቱ 204
፪፻ወ፭ ክልኤቱ ምዕት ወሐምስቱ 205
፪፻ወ፮ ክልኤቱ ምዕት ወስድስቱ 206
፪፻ወ፯ ክልኤቱ ምዕት ወሰብዓቱ 207
፪፻ወ፰ ክለኤቱ ምዕት ወስመንቱ 208
፪፻ወ፱ ክልኤቱ ምዕት ወተሰዓቱ 209
፪፻ወ፲ ክልኤቱ ምዕት ወአሠርቱ 210
፪፻፲ወ፩ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወአሐዱ 211
፪፻፲ወ፪ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወክልኤቱ 212
፪፻፲ወ፫ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሠልስቱ 213
፪፻፲ወ፬ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወአርባቱ 214
፪፻፲ወ፭ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሐምስቱ 215
፪፻፲ወ፮ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወስድስቱ 216
፪፻፲ወ፯ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሰብዓቱ 217
፪፻፲ወ፰ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሰመንቱ 218
፪፻፲ወ፱ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወተሰዓቱ 219
፪፻፳ ክልኤቱ ምዕት ወእስራ 220
፪፻፴ ክልኤቱ ምሪዕት ወሠላሳ 230
፪፻፵ ክልኤቱ ምዕት ወአርብዓ 240
፪፻፶ ክልኤቱ ምዕት ወሃምሳ 250
፪፻፷ ክልኤቱ ምዕት ወስድሳ 260
፪፻፸ ክልኤቱ ምዕት ወሰብዓ 270
፪፻፹ ክልኤቱ ምዕት ወሰማንያ 280
፪፻፺ ክልኤቱ ምዕት ወተሰዓ 290
፫፻ ሠለስቱ ምዕት 300
፬፻ አርባዕቱ ምዕት 400
፭፻ ሐምስቱ ምዕት 500
፮፻ ስድስቱ ምዕት 600
፯፻ ስብዓቱ ምዕት 700
፰፻ ስመንቱ ምዕት 800
፱፻ ተሰዓቱ ምዕት 900
፲፻ አሠርቱ ምዕት 1000
፳፻ እስራ ምዕት 2000
፴፻ ሠላሳ ምዕት 3000
፵፻ አርብዓ ምዕት 4000
፶፻ ሃምሳ ምዕት 5000
፷፻ ሳድስ ምዕት 6000
፸፻ ሰብዓ ምዕት 7000
፹፻ ሰማንያ ምዕት 8000
፺፻ ተሰዓ ምዕት 9000
፻፻ እልፍ 10,000
፪፻፻ ክልኤቱ እልፍ 20,000
፫፻፻ ሠለስቱ እልፍ 30,000
፬፻፻ አርባዕቱ እልፍ 40,000
፭፻፻ ሐምስቱ እልፍ 50,000
፮፻፻ ስድስቱ እልፍ 60,000
፯፻፻ ሰብዓቱ እልፍ 70,000
፰፻፻ ስመንቱ እልፍ 80,000
፱፻፻ ተሰዓቱ እልፍ 90,000
፲፻፻ አሠርቱ እልፍ 100,000
፳፻፻ እስራ እልፍ 200,000
፴፻፻ ሠላሳ እልፍ 300,000
፵፻፻ አርብዓ እልፍ 400,000
፶፻፻ ሃምሳ እልፍ 500,000
፷፻፻ ስድሳ እልፍ 600,000
፸፻፻ ሰብዓ እልፍ 700,000
፹፻፻ ሰማንያ እልፍ 800,000
፺፻፻ ተሰዓ እልፍ 900,000
፻፻፻ አእላፋት 1,000,000
፲፻፻፻ ትእልፊት 10,000,000
፻፻፻፻ ትልፊታት 100,000,000
፲፻፻፻፻ ምእልፊት 1,000,000,000
✍የኛ ቤተክርስቲያን የሌላት
የለም እነዚህን ቁጥሮች እየተረሱ ነው ተጠቀሙባቸው ሀብታችን ናቸው፡፡
★ቤተ ክርስቲያን ባህረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት
🖇Share with friend
@yegetemkalat
😔ሀጥያት እየሰራን ጀነት እንገባለን😜
መንገዱ በዛና
የእግራችን ዳና ለየቅል ተሳለ
ማርከሻው ጠፋና
ውስጣችን በፍቅር ደዌ ያለቅጥ ከሰለ
ለማምነው ታምኜ ለምታምኚው ታምነሽ
እኔም ባይማኖቴ አንቺም ባይማኖትሽ
ዘፋኙ እንዳለው ለሱ እንደታየው
ለኔም ላንቺም ታይቶን ፍቅርን የጀመርነው
እስኪ መልሺልኝ...
እንደዘፈኑ እድሜ ለአፍታ ብቻ ነው?
ወኔሽን የሰራው የዘፋኙ ቃል ነው?
ከሆነ ረገምኩት
እናቱን ዘፋኙ
እናቱን ግጥሙ
እናቱ ያ ዜማ
ከልቤ ረገምኩት ውስጤን ስላደማ
ጆሮሽም እናቱን እሱን ስለሰማ::
ባልቆሸሸ ህሊና እውቀት በጎደለው
ባልጎደፈው ዳና ክፋት ባልረገጠው
በንጹህ ልባችን ክፉ ደግ ባለየው
ነበር የቆረስነው የፍቅር ገበታ
እንኳን ለሃይማኖት ለእምነታችንም አልነበረን ቦታ
እኔና አንቺኮ...
ፍቅርን ስንጀምር
ዘፋኙም ዘፈኑን አልዘፈነም ነበር።
እኔና አንቺኮ በፊት ልጅ እያለን
መሰጂድሽ መጣና አሊፍ ባ ታ እያልን
በአንድ ጊቢ ውስጥ በቦታ ተከፋለን
ኡስታዙ ያሉንን በንጹ ልባችን ካፋቸው እየለቀምን
ቅዱሱን ቁርአን በዜማ እንቀራለን።
እኔና አንቺኮ በለጋው እድሚያችን
በቤተስኪያን ደጃፈ ስናልፍ ተቃቅፈን
አንቺም በኢጃብሽ እኔም በማተቤ
በጃችን አማትበን ግንባር አስነክተን
ከወገብ ዝቅ ብለን በሩን እስማለን
እንሳለማለን
አምነት በውስጣችን ሀይማኖት በጋራ
እግዜሩም ሳይከፋው አላህም ሳይኮራ
ከፋ አርገውን ነበር በፍቅር ተራራ
ቀኖናውን ሽረን ሀራሙን ሳንፈራ
ያለምንም ቅስፈት በፍቅር ኖረናል በሰላም በጋራ።
ዛሬ ምን ጎሎሽ ነው ምን አተሽ ምን ፈርተሽ
አውላላ ሜዳ ላይ ጥለሺኝ የሄድሺው ሀይማኖትን መርጠሽ
ነው ወይስ...
ዛሬ ከፍ ስንል የነፍስስና ስጋ አስተምሮው ገብቶሽ
ስጋሽ ከሌላ ሀይማኖት በፍቅር ከተዳራች
ነብስ ሲኦል ገብታ ምትሰቃይ መስሎሽ
ነው ወይስ..
የስጋ ኩናኔን የሰው ወሬን ፈርተሽ?
ከሆነ የኔ አለም ይሄንን ልንገርሽ...
ልጅ እያለን ያኔ
በእውቀተቢስ ወኔ
የፈጸመነው ግብር ተሽሮልን ዛሬ
እኔም ሀይማኖቴን ዶግማውን አክብሬ
ባላየ ባልሰማ የድሮውን ትተን
አንቺም ሙስሊም አጭተሽ ገነት እንገባለን።
ጀነት መግባት ሽተሽ ከሆነ የራቅሺኝ
አዛው እንገናኝ
አኔም ባይማኖቴ ክርስቲያን ሴት ላጭ ነው
የአንቺን ብልጥነት እኔም ልሞኝ ነው።
@estofun 17/10/2014ec
#እሱባለው_ይታየው 🔥🔥
#ቻው_ቻው_ትልና 🔥🔥🔊🔊
4.15 KB
በናፍቆት ተይዤ ሲደክም ጉልበቴ 🙄
ደሞ ይባስ ብሎ ታሰረ አንደበቴ😒
ስብር ያለ ለታ ስሜም እንደቅስሜ😔
እፅናናለው ሳይሽ እንኳንስ ተስሜ😘
ብክንክን ስል አደብ ሲያሳጣኝ🥺
ትዝታሽ ደርሶ ከጭንቅ አወጣኝ🤩
አወይ መታደል አወይ መገፋት 💏
ከሞት ያስጥላል እንኳን ከዕንቅፋት 🖤
ሀኪሜ ነሽ መዳኒቴ 🤎
@Broken_heartssssss
4_5895453151951062708.ogg9.46 KB
😘 ያበደው ፍቅሬ 😘
ክፍል 8⃣
ህይወት ልክ በምኞታችን ውስጥ እንዳሰብናት ቀላልና ጣፋጭ አይደለችም። ልንመራት ያወጣነውን እቅድ አስጥላ በራሷ ምህዋር ላይ ታሽከረክረናለች። እምቢ ብለን ብናስቸግራት እንኳን ወይ ከራሳችን እቅድ ወይም ሽክርክሪቱ ከሚያመጣው ነገር ሳንቋደስ ሜዳ ላይ እንቀራለን።
ዩንቨርስቲ መግባትን ሳስብ የሚታየኝ ጠንክሮ መማርና መማር ብቻ ነበር። ግቢ ውስጥ ሆኜ ከትምህርቴ የበለጠ ቦታ እሰጠዋለሁ ብዬ የማስበው ምንም ነገር አልነበረም። የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ እያለሁ የሆነ ሰው መጥቶ ይህን ጥያቄ ቢጠይቀኝ በመጠየቁ ልናደድበት እችል ነበር። ዛሬ ግን ያን እምነቴን የትላንት እቅዴን ሊያከሽፍ የሚችል ፍቅር ያዘኝ። ያውም ውድድር የበዛበት ፍቅር.....
አብሬው ልሁን ብዬ ባስብ እንኳን ከሱ እኔን አለማፍቀር ውጪ ከደርዘን በላይ ሴቶች ጋር መጋፈጥ ይኖርብኛል..... ያውም እኔ የማውቃቸው ብቻ።
ያለኝ አማራጭ አንድ ብቻ ነው ቢከብደኝም ስሜቴን አምቄ መያዝ እና በሰላም ትምህርቴን መቀጠል። ምንም ሳይተነፍሱ ሁሉንም በልብ መያዝ ከምንም በላይ ህመም ነው.... በተለይ ደግሞ ፍቅር ሲሆን...
ብዙ ጊዜ ይሄን አስባለሁ ለእናቴ ይሄ አይገባትም አይደል? ... ስኬቴን ለምትናፍቅ እናቴ ስል ከመጋፈጥ ይልቅ መሸሽን መርጫለሁ። የምሸሽበት ምክንያት ዋናው ቁም ነገሩ እኮ ማፍቀሬ አይደለም ፍቅር በየትኛውም ጊዜ እና ሁኔታ ውስጥ ሊከሰት የሚችል ስሜት ነው። ችግሩ ለዚህ ፍቅር ስል ብፋለም ለትምህርት የሚሆን ነፃ አይምሮ ላገኝ እችላለው ወይ? የበለጠው ችግር ደግሞ ያፈቀርኩት ሰው ሁሉንም ቀማሽ መሆኑ ነው።
፧፧፧፧፧፧ ፧፧፧፧፧፧፧ ፧፧፧፧፧ ፨፨፨፨ ፨፨፨፨
ከዛን ቀን ጀምሮ ማለትም ከመጀመሪያ የትምህርት ቀናችን ጀምሮ በዮኒ ፍቅር ተለክፊያለሁ። ፍቅር እንደያዘኝ እንኳን እያወኩ ላለማመን ከራሴ ጋር ለወራት ተከራክሪያለሁ። የትናዬት በየቀኑ እኔን ማስበርገግ ስራዬ ብላ ከያዘች ቆይታለች። በተለይ ዮናታን አስተምሮን ሲወጣ ወይ ከጎኔ ናት ወይም ከፊት ለፊቴ.... እልፍ ጊዜ እኮ አብረው አይቻቸዋለሁ... ብዙ ጊዜ ቢሮው ስትገባ ያዩዋት ነግረውኛል...... እኔ ደግሞ በተቃራኒው ከሱ ጋር የሚያገናኘን ድልድይ ሁላ ላፈርስ የምሞክር ሰው ነኝ። ለምን ይሄን ያክል የቤት ስራ እንደሆንኩባት አላውቅም። አሁን ግን መሮኛል ፀብ ላለመፍጠር እያልኩ እንደፈሪ መታየት መሮኛል።
ዛሬም እንደለመደችው ከጥሩ ትወና ጋር የአሽሙር ንግግሯን ተናግራኝ ከክፍሉ ወጣች። ብሽቅ ብዬ ወረቀቶቼን ሰብስቤ ተከትያት እየወጣሁ እያለ አንድ ሰው ከኋላዬ ያዘኝ። ዞር ስል ቢኒ ነው ከተማሪዎች ሁሉ የተለየው ዝምተኛ ልጅ።
"አቤት ቢኒ" አልኩት ኮስተር ብዬ... ግንባሬን አይቶ እጁን ከክንዴ ላይ አነሳ እና
"ይቅርታ ሩት.... ጣልቃ ልገባ ፈልጌ አይደለም ግን እኔ የታየኝን አንድ ነገር ልበልሽ..."
"ምን"
"የትናየት ካንቺ የምትፈልገው ይህንን ነው... ማለትም ፀብ.... ከሷ የተሻልኩ ነኝ ብለሽ ካሰብሽ እቅዷን ቀድመሽ አክሽፊባት...."
"ማለት..... እንዴት አድርጌ"
"እኔ አግዝሻለሁ..." እንስማማ አይነት እጁን ዘረጋልኝ። ሳላወላውል ጨበጥኩት.... ተገኝቶ ነው ይቺን የሰው ቆንጥር ከአጠገቤ የሚያርቅልኝ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧ ፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧ ፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧ ፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧ ፧፧፧፧፧፧፧፧፧ ፧፧፧፧፧፧፧፧፧ ፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ወደ መነሻ
አስታወሳችሁ መነሻዬን እንጂ መድረሻዬን ሳላውቅ እግሬ ወደመራኝ እየሄድኩ ነው ብያችሁ ነበር። አዎ መንገዴን አላቋረጥኩም። ከእርምጃዬ እኩል ትዝታዬ በልቤ ውስጥ ይፈሳል በአይምሮዬም ውስጥ ይመላለሳል።
ከተማውን ሙሉ ለሙሉ መልቀቄን ያስተዋልኩት ከፊት ለፊቴ ያለው ሰፊ የግጦሽ ሜዳ ላይ የእረኛዎችን ድምፅ ስሰማ ነው።
ድንገት እኔን አልፎ ሲጥጥ ብሎ የቆመ መኪና ከሀሳቤ አንቅቶ አስበረገገኝ። ቅድም ሳይገጨኝ ያለፈው መኪና.... ከውስጡ አንድ ሰው ወረደና ወደኔ መጣ። በድንጋጤ ደርቄ ነው የቀረሁት
"ሩት በዚህ መልኩ አገኝሻለሁ ብዬ አልጠበኩም ነበር" አጠገቤ መጥቶ ክንዴን ያዘኝ ልክ እንደመጀመሪያው ቀን ልዩነቱ ያኔ ከኋላ አሁን ግን ከፊት ለፊት መሆኑ ነው
"ቅድም አንተ ነበርክ"
"አዎ ግን አንቺ መሆንሽን ለመለየት ጊዜ ወሰደብኝ ሩቴ በጣም ተጎሳቁለሻል አንቺ እንደሆንሽ ያወኩት "ዞር በሉልኝ አስማሳዮች" ብለሽ ስትናገሪ በሰማውት ድምፅሽ ነው አረማመድሽ ደግሞ አረጋገጠለኝ። እናም ተከተልኩሽ.... የምትሄጅበትን መድረሻሽን ለማወቅ ተከተልኩሽ ግን እንደማየው.......
"ቢኒ እኔ...." ቃላቶቼ አፌ ላይ ተንገዋለሉ። ወደራሱ አስጠግቶ እቅፍ አደረገኝ።
"እሽሽሽሽሽሽሽ ይገባኛል ምንም አታስረጂኝ"
በህይወት መንገድ ላይ ለሁለተኛ ጊዜ ተገናኘን..... እኔና ቢኒ
Share አድርጉ።
ይቀጥላል....
ይ🀄️ላ🀄️ሉን
ይ🀄️ላ🀄️ሉን
@getemberedu