AAU Tutorial
الذهاب إلى القناة على Telegram
This channel is designed to share information and to support AAU students. For any comment or suggestion use: @haile_my
إظهار المزيد7 665
المشتركون
+224 ساعات
+297 أيام
+3430 أيام
أرشيف المشاركات
7 664
David_S_Kidwell,_David_W_Blackwell,_David_A_Whidbee_Financial_Economics.pdf13.76 MB
7 664
ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሴት ተማሪዎች በሙሉ !!!
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሴቶች ቮሊቦል ክለብ በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ በመወዳደር ላይ ይገኛል፡፡
በመሆኑም ምርጥና ተወዳዳሪ ሴት ተጨዋቾችን አወዳድሮ መቅጠርና ቡድናችንን ማጠናከር ስለምንፈልግ፣ ቮሊ ቦል መጫወት የምትችሉ ሴት ተማሪዎች (ስፖርተኞች) ከየካቲት 01 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምራችሁ በተማሪዎች ዲን ጽ/ቤት የክበባትና ስፖርት ማስተባበሪያ ቢሮ በመምጣት እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡
መስፈርት፡-
1. ቁመቷ 1.70 እና በላይ የሆነ፣
2. በግቢው ውስጥ ምንም አይነት የሥነ-ምግባር ችግር የሌለባትና ለስፖርት ህግ ተገዥ (ዲስፕሊንድ) የሆነች፣
3. ክለቡ በሚያደርጋቸው ልምምዶች ላይ ለመገኘት የምትችል መሆን ይጠበቅባታል።
ማንኛዋም የመጫወት ብቃት ያላት ሴት ተጨዋች መሳተፍ የምትችል መሆኗን እንገልጻለን፡፡
7 664
Anyone who interested to participate in Hult Prize of this year, but didn't create a group yet send your full name, email, and phone number via @kalleo until 9:35 PM (3:35 LT).
7 664
Anyone who wants to participate in Hult Prize of this year, but didn't create a group yet send your full name, email, and phone number via @kalleo until 9: 35 PM (3:35 LT).
7 664
የከፍተኛ ትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ለሁሉም የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና እንደሚሰጥ ተገለፀ።
-----------------------------------------
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዚዳንቶች ጋር ተወያዩ፡፡
ውይይቱም በተቋማት ተጠያቂነትና የመረጃ ፍሰትን ለመዘርጋት እንዲሁም ውጤታማ እና ቀልጣፋ ሥራ እንዲያከናወኑ ያስችላል በተባለ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ረቂቅ መዋቅር ላይ ያተኮረ ነው።
በመንግስትም ሆነ በግል የከፍተኛ ትምህርት ጥራትን ወደሚፈለገው ደረጃ ከፍ ለማድረግ በቀጣይ የትምህርት ዘመን የመውጫ ፈተና ለሁሉም የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ሊሰጥ መሆኑን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲዎች የትምህርቱ ማህበረሰብ ከፖለቲካ ነፃ ሆነው ሃሳባቸውን የሚያንሸራሸሩባቸው ተቋማት መሆን እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡
ፕሮፌሰር ብርሃኑ አክለውም ዩኒቨርሲቲዎች የእውቀት፣ የምርምርና የአዳዲስ ሃሳቦች መፍለቂያ ከመሆናቸው አንፃር ተልዕኳቸውን በብቃትና በውጤታማነት ለመፈፀም ይችሉ ዘንድ የተጀመረው የመዋቅር ሪፎርም ሥራ አንዱና ወሳኝ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲዎች የአካባቢውን ማህበረሰብ ሕይወት ሊቀይሩ በሚቻሉበት መልኩ ከተልዕኳቸው ጋር አጠናክረው የሚሄዱበትን ጉዳይ ለይተው መሥራት እንደሚገባቸውም ገልፀዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ በተዘጋጀው የዩኒቨርሲቲዎች ረቂቅ መዋቅር ሰነድ ቀርቦ በተሳታፊዎች ውይይት ተደርጎበታል፡፡
©MoE
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
